የብልጽግና ምርኩዝ አቀባይ የሆነው ምክክር ኮሚሽን ከዐማራ ሕዝብ አንፃር ገና ከጅምሩ ምኅዳራዊ እገዳ አድርጓል።
1) የዐማራ ሕዝብ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ በመሆኑ!
2) ጦርነት ላይ በመሆኑ የፖለቲካ ጥያቄዎች ለመፍታት ተኩስ አቁም አለመደረጉ!
3) የሕዝብ ጥያቄዎች የያዙት ምሁራን ፖለቲከኞች ጋዜጠኞች የወጣቶች ተወካዮች መታሰራቸው!
4) በሕዝብ ጥያቄዎች እና በአጀንዳ ቀረፃ ሊሳተፉ የሚችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ፈርሰዋል። የሲቪክ ተቋማት እንዳይንቀሳቀሱ ተደርገዋል!
5) በሲቪል በወታደራዊ ተቋማት ያሉ የዐማራ ምሁራን አንገት እንዲደፉ ተደርገዋል!
6) በሃገረ መንግሥት ግንባታ የላቀ ሚና በሚጫወቱ የእምነት ተቋማት ያሉ ልሂቃን እንዲበተኑ ሃገራዊ አጀንዳ እና ተሳትፎ እንዳይኖራቸው ተደርጓል!
7) አጀንዳ ቀረፃ ላይ የሕዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ ሁሉም የመገናኛ ዘዴዎች ዝግ ተደርገዋል!
8) መዋቅራዊ ተሳትፎ የሚደረግበት ምንም ዓይነት አደረጃጀት እና ተዋረድ የለውም!
ከላይ በተዘረዘሩት እና ባልተጠቀሱት ምክንያቶች ምክክር ኮሚሽኑ ከአገሪቱ ግማሽ የሚሆነውን ሕዝብ ምህዳር (space) እንዳይኖረው አድርጓል!
ስለዚህ ምህዳር የተከለከለ ሕዝብ በሁለተኛው ሂደት አጀንዳ ቀረፃ ላይ ሊሳተፍ የሚችልበት ዕድል የለውም። አለውም ከተባለ የሕዝብ መሠረታዊ ተሳትፎ ያልተደረገበት በመሆን ይመዘገባል!
እውነተኛ አካታች አሳታፊ የሽግግር ፍትህ እና ምክክር ይደረግ ከተባለ በተለይ ለዐማራው የተዘጋው ምህዳር መከፈት አለበት።
1) የዐማራ ሕዝብ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ በመሆኑ!
2) ጦርነት ላይ በመሆኑ የፖለቲካ ጥያቄዎች ለመፍታት ተኩስ አቁም አለመደረጉ!
3) የሕዝብ ጥያቄዎች የያዙት ምሁራን ፖለቲከኞች ጋዜጠኞች የወጣቶች ተወካዮች መታሰራቸው!
4) በሕዝብ ጥያቄዎች እና በአጀንዳ ቀረፃ ሊሳተፉ የሚችሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ፈርሰዋል። የሲቪክ ተቋማት እንዳይንቀሳቀሱ ተደርገዋል!
5) በሲቪል በወታደራዊ ተቋማት ያሉ የዐማራ ምሁራን አንገት እንዲደፉ ተደርገዋል!
6) በሃገረ መንግሥት ግንባታ የላቀ ሚና በሚጫወቱ የእምነት ተቋማት ያሉ ልሂቃን እንዲበተኑ ሃገራዊ አጀንዳ እና ተሳትፎ እንዳይኖራቸው ተደርጓል!
7) አጀንዳ ቀረፃ ላይ የሕዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ ሁሉም የመገናኛ ዘዴዎች ዝግ ተደርገዋል!
8) መዋቅራዊ ተሳትፎ የሚደረግበት ምንም ዓይነት አደረጃጀት እና ተዋረድ የለውም!
ከላይ በተዘረዘሩት እና ባልተጠቀሱት ምክንያቶች ምክክር ኮሚሽኑ ከአገሪቱ ግማሽ የሚሆነውን ሕዝብ ምህዳር (space) እንዳይኖረው አድርጓል!
ስለዚህ ምህዳር የተከለከለ ሕዝብ በሁለተኛው ሂደት አጀንዳ ቀረፃ ላይ ሊሳተፍ የሚችልበት ዕድል የለውም። አለውም ከተባለ የሕዝብ መሠረታዊ ተሳትፎ ያልተደረገበት በመሆን ይመዘገባል!
እውነተኛ አካታች አሳታፊ የሽግግር ፍትህ እና ምክክር ይደረግ ከተባለ በተለይ ለዐማራው የተዘጋው ምህዳር መከፈት አለበት።