Latest Posts from Diredawa Adminstration Electric Utility (@eeudiredawa) on Telegram

Diredawa Adminstration Electric Utility Telegram Posts

Diredawa Adminstration Electric Utility
Officail Telegram channel of EEU Diredawa Region.
1,507 Subscribers
606 Photos
4 Videos
Last Updated 06.03.2025 11:30

The latest content shared by Diredawa Adminstration Electric Utility on Telegram

Diredawa Adminstration Electric Utility

16 Oct, 17:22

2,387

ከሁለት ሳምንት በኋላ መስመሩ ዳግም ተገናኝቷል
………///……….
በስርቆት ምክንያት ላለፉት ሁለት ሳምንታት አገልግሎቱ ተስተጓጉሎ የነበረው የቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ማምሻውን አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት የተቋረጠውን መስመር መልሶ ለማገናኘት ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል።

ከሪጅኑ በተጨማሪ የሦስት ሪጅኖች ባለሙያዎችን በቅንጅት በማሳተፍ የተከናወነው የጥገና ሥራ የምስራቅ ኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ከፈረቃ ወጥተው ኃይል እንዲያገኙ ማስቻሉን ዳይሬከረተሩ ገልፀዋል።

በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ሁሉንም ባለሙያዎችና የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደርን አመስግነዋል።

የአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ተደጋጋሚ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት ከሚፈፀምባቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ ነው።

💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም
Diredawa Adminstration Electric Utility

14 Oct, 10:45

2,299

ተቋርጦ የነበረው ነፃ የጥሪ ማዕከል ወደ አገልግሎት ተመልሷል

ከጥቅምት 02 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ጀምሮ የመረጃ ማዕከል ማሻሻያ ስራ ለማከናወን ሲባል ተቋርጦ የነበረው ነፃ የጥሪ ማዕከል ወደ አገልግሎት ተመልሷል፡፡

በመሆኑም ውድ ደንበኞቻችን በነፃ የጥሪ ማዕከሎቻችን በመደወል እንደተለመደው ማንኛውም መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በዚህ አጋጣሚ በተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

13 Oct, 06:10

2,477

ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው
………///……….
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ከቆቃ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው ስርቆት በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል።

ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መልሶ ለማቆም የወደቀውን ምሰሶ የመፈታታት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ጎሳዬ ምሰሶውን መልሶ በማቆም በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የሪጅኑ 12 ባለሙያዎች በጥገና ሥራው ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከማዕከላዊ አንድ እና ሦስት ሪጅን እንዲሁም ከምስራቅ አንድ ሪጅን ተጨማሪ ባለሙያዎች ቡድኑን እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡

የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ የማድረግ ሥራው እንደሚቀጥል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

ለጥገና ሥራው የቅርብ ድጋፍ እያደረገ ያለውን የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደር እና ከንቲባውን በሪጅኑ ስም አመስግነዋል፡፡

በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለመሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም
Diredawa Adminstration Electric Utility

11 Oct, 13:58

1,619

የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እሑድ ጥቅምት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ከ ማለዳ 12፡00 እስከ ምሽት 12፡00 ድረስ ጥገና ስራ ስለሚያከናውን በድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ፊቅ፣ ጅግጂጋ፣ ደገሐቡርና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጦ ይቆያል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

10 Oct, 08:13

1,585

በጥሪ ማዕከሎቻችን ይሰጥ የነበረው አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል

ከትላንት መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 1 ስዓት ጀምሮ ባጋጠመ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎቻችን አገልግሎት መስጠት አቁመዋል፡፡

ውድ ደንበኞቻችን ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እየጠየቅን፤ ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስከሚመለስ ድረስ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
Diredawa Adminstration Electric Utility

07 Oct, 14:53

1,930

በኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መውደቅ ምክንያት አገልግሎት መቋረጡን ስለማሳወቅ

*******************

ዛሬ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም በመልካ ጀብዱ አካባቢ የኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች በመውደቃቸው ምክንያት መልካ ጀብዱ ሙሉ በሙሉ፣ ገንደ ሪጌ፣ አዲሱ ባቡር ጣቢያ፣ ደረቅ ወደብ እና አካባቢዎቸቸው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጥገና ቡድን አገልግሎቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ ጥረት እያደረገ መሆኑን እየገለፅን፤ ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞች የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ ወደ ነበረበት እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡



#የድሬዳዋአስተዳደርኤሌክትሪክአገልግሎት



ወቅታዊና ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት የትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ:-

ፌስ ቡክ፡https://www.facebook.com/diredawaelectric2011
ቴሌግራም፡ https://t.me/eeudiredawa
Diredawa Adminstration Electric Utility

07 Oct, 06:31

1,367

ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ፍጆታዎ በስልክዎ!
ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

03 Oct, 09:11

1,744

ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው ከፍተኛ መስመር ላይ በደረሰ ጉዳት በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል

ከቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አዋሽ ፓርክ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

በዚህም በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል በሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች፣ ለአዲስ አበባ- ጅቡቲ የባቡር መስመር እንዲሁም ለጅቡቲ የሚሄደው የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋጧል።

ስርቆት የተፈፀመበት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጥምር የኤሌክትሪክ መስመሮችን የያዘ በመሆኑ የጥገና ሥራው ከ20 ቀን ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል የተጠቀሰ ሲሆን ፤ የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረቶች ይደረጋሉ ተብሏል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመተሃራ - አዋሽ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የባቡር መስመር ላይ በሚገኙ ዘጠኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ታውቋል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡሯን ደንበኖቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ጥገናው እስኪጠናቀቅ ድተስ በትዕግስት እንድትጠባበቁን እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

02 Oct, 17:44

1,648

ለስራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

*******

የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት አርብ መስከረም 24 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ኃይል የማገናኘት ስራ ለማከናወን ከጠዋቱ 1:00 እስከ ቀኑ 7:00 ድረስ አዲስ ከተማ፣ ለገሀሬ፣ ቀፊራ፣ ግንፍሌ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

ስለሆነም ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ከወዲሁ እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡

#የድሬዳዋአስተዳደርኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት የትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ:-

ፌስ ቡክ፡https://www.facebook.com/diredawaelectric2011
ቴሌግራም፡ https://t.me/eeudiredawa
Diredawa Adminstration Electric Utility

02 Oct, 10:49

1,222

ቆጣሪ በወቅቱ አለመነበብ በደንበኞች ላይ ምን ያህል ጫና እንደሚያሳድር ያውቃሉ? እንግዲያውስ እናሳውቅዎ የሚጠቀሙበት ቆጣሪ ካልተነበበ ቢል ስለማይዘጋጅልዎ ለተጨማሪ ወጪ ይዳረጋሉ፡፡ ስለሆነም ወድ #የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞችን የሚጠቀሙበትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ በተቀመጠለት የማንበቢያ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በየወሩ መነበቡን ይከታተሉ፤ካልተነበበልዎትም ወዲያውኑ አገልሎት ወደሚያገሀኙበት ማዕከል በመሄድ ያሳውቁ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት