Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau @cib_ethiopiafederalpolice Channel on Telegram

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

@cib_ethiopiafederalpolice


Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau (English)

Welcome to the Ethiopian Federal Police Crime Investigation Bureau's Telegram channel, where we provide the latest updates on crime investigations, safety tips, and community alerts. Our channel, @cib_ethiopiafederalpolice, is dedicated to keeping the citizens of Ethiopia informed and safe. The Ethiopian Federal Police Crime Investigation Bureau is a specialized unit that focuses on solving crimes, ensuring justice is served, and maintaining law and order in the country. Our team of skilled investigators works tirelessly to uncover the truth behind criminal activities and bring perpetrators to justice. By following our channel, you will have access to important information that can help protect you and your loved ones from harm. Stay updated on crime trends, learn about crime prevention strategies, and report any suspicious activities to help us keep Ethiopia safe. Join us on @cib_ethiopiafederalpolice and be a part of our mission to create a safer and more secure community for all.

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

01 Feb, 17:37


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የስትራቴጂክ እና የከፍተኛ አመራር የፖሊስ መኮንኖች ስብሰባ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል
******
ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
ክቡር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው በሰጡት የሥራ መመሪያ በዚህ በሪፎርም ጊዜ ሕዝቡ የሚፈልገው ፖሊስ፤ በጣም ዲሲፕሊን የሆነ፣ የማይሰርቅ፣ አለባበሱ የሚያምር፣ ሥርዓት ያለው፣ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የሚችል እና የትም ቦታ ሄዶ ወንጀል መከላከል የሚችል ብቃት ያለው፣ በዘር የማያምን፣ ከፖለቲካና ከሀይማኖት ወገንተኝነት የፀዳ ፖሊስ ነው ብለዋል።

ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል የስትራቴጅክ እና ከፍተኛ አመራሮች የአመራር መርሆዎችን (leadership principles) በትክክል ተገንዝበው ሥራ ላይ እንዲያውሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም ሰጥተዋል።

የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትም ቀርቦ በክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ከተሰጡ በኋላ ተጠናቋል።

ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል አያይዘውም ጠንካራና ከችግር ፈጥኖ የሚወጣ ፖሊስ ለመፍጠር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የጀመረውን የአቅም ግንባታ አጠናክሮ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥተዋል።

በቀጣይ በተቋሙ የተፈጠሩ የድሮን እና የሌሎች የቴክኖሎጂ አቅሞች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

አመራር ሁሌም እየተማረና የቡድን ሥራ አጠናክሮ የሚሰራ ከሆነ የማንሻገረው ምንም አይነት ችግር የለም ያሉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጌቱ ተ/ዮሐንስ ናቸው።

አመራሮቹ ውይይት ሲያካሄዱ የቆዩት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተዘጋጀው ''የፖሊስ የመነሳት ዘመን'' በሚል ሰነድ ላይ ነው።

አመራሮቹ ስብሰባውን ካጠናቀቁ በኋላ የፎረንሲክ ሳይንስ ኢንስቲትዩት የምርመራ ልህቀት ማዕከልን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

31 Jan, 13:20


በሩዋንዳ ኪጋሊ ሲካሄድ የቆየው 26ኛው  የEAPCCO ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ
****
ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም
በሩዋንዳ ኪጋሊ ሲካሄድ የቆየው 26ኛው  የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት (EAPCCO) ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በ24ኛው የኅብረቱ የሚኒስትሮች ካውንስል ጠቅላላ ስብሰባ በሩዋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር በክቡር ኤዶዋርድ ንጊሬንቴ (ዶ/ር) ተዘግቷል።

የቀጠናው አባል ሀገራት የፖሊስ አዛዦች ያቀረቧቸው ውሳኔዎች እና ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በካውንስሉ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ያነሷቸው ሃሳቦችም በውሳኔው ተካተው በሚኒስቴሮች ካውንስል ፀድቀዋል።

ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴም ኢትዮጵያን ወክለው በማጠቃለያው ፕሮግራም ላይ ተሳትፎዋል።

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

29 Jan, 12:25


ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በሩዋንዳ ኪጋሊ እየተካሄደ በሚገኘው 26ኛው የEAPCCO ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፋ ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም
ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በሩዋንዳ ኪጋሊ እየተካሄደ በሚገኘው 26ኛው የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት (EAPCCO) ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፋ ይገኛሉ።

የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት 26ኛው ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቀጠናው ከሚገኙ የፖሊስ ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል ወሳኝ ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል።

የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት በቀጠናው የሚገኙ የፖሊስ ተቋማትን በማስተሳሰር በተባበረ ክንድ የተደራጁ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ታውቋል።

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

27 Jan, 17:55


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 26ኛውን የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ ዋና ዋና ዋና ዋና ተራድኦ ድርጅትን (EAPCCO) ዓመታዊ ስብሰባ በሩዋንዳ ኪጋሊ ከተማ ተቀላቀለ
****
ጥር፣ 27 ቀን 2025
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 26ኛውን የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አበላት ተራድኦ ድርጅትን (ኢአፕሲኮ) አጠቃላይ ዓመታዊ ስብሰባ በሩዋንዳ ኪጋሊ ተቀላቀለ፡፡ 26ኛው ኢአፓኮ የክልል ህግ አስከባሪ አመራሮችን በማሰባሰብ የፀጥታ ችግሮችን ለመቋቋም ያስችላል ክልላዊ የህግ ማስከበር ትብብርን ማጠናከር ሽብርተኝነት፣ ተሻጋሪ፣ የተደራጀ እና ወንጀሎችን ማጠናከር በሚል መሪ ቃል ተካሄደ፡፡ ”

H. የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ 26ኛው የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አበላት ተራድኦ ድርጅት (EAPCCO) አጠቃላይ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ነው። ከምስራቅ አፍሪካ ቀጠና አቻዎቹ ጋር በንቃት እየተወያየ ይገኛል፤ ትብብርን ማጎልበት ላይ በማተኮር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተሞክሮዎችንና ምርጥ ልምዶችን አካፍሏል

ስብሰባው ለአባል ሀገራት የደህንነት ተግዳሮቶችን ሆን ብለው ለመፈታት፣ የጋራ ስልቶችን በመቅረጽ እና የወንጀል ድርጊቶችን ለማስተካከል የትብብር ማዕቀፎችን ለማጠናከር ወሳኝ መድረክ ሆኖ ያገለግላል።

የኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ በኢኤፕሲኮ፤ ለቀጠናዊ ደህንነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት እና በምስራቅ አፍሪካ መረጋጋት እንዲፈጠር ያላትን ሚና ያሳያል። የዚህ ስብሰባ ውጤቶች ወንጀልን በመከላከልና የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የጋራ ጥረቶችን ያስቀምጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

24 Jan, 15:30


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የ2017 ዓ.ም የ6ወር የሥራ አፈፃፀም የማጠቃለያ ግምገማ እያካሄደ ነው
***
ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የ2017 ዓ.ም የ6ወር የሥራ አፈፃፀም የማጠቃለያ ግምገማ እያካሄደ ይገኛል።

የበጀት አመቱን የ6 ወር የሥራ አፈፃጸም ግምገማ የመሩት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ ተቋማዊ ዕቅዱን ለማሳካት ሁሉንም አመራርና አባል በማሳተፍ የተሰጠውን ተልዕኮ ግብ ለማድረስ የፍትህ ስርዓቱን ታማኝና ግልፅ በማድረግ የተጀመሩ ውጤታማ የምርመራ ሥራዎችን በታክቲክ፣ በፎረንሲክና በድጋፍ ዉጤት የተገኘባቸውን ሥራዎችን አጠናክረን ማስቀጠል አለብን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አያይዘውም በ2017 ዓ.ም ግማሽ ዓመት የተሻለ የመዝገብ አፈፃፀም የተመዘገበበት መሆኑን አንስተው በተለይም በድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በሕገ-ወጥ የሰዎች እና በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር እንዲሁም በተለያዩ የኢኮኖሚ ወንጀሎች በመንግስትና በሕዝብ ሀብት ላይ የደረሰ ጉዳት ለማዳን የሚያስችል በርካታ የምርመራ መዝገቦችን ማጣራት መቻሉን ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም በዛሬው ዕለት የተጀመረው የ2017 ዓ.ም የ6ወር የሥራ አፈፃፀም የማጠቃለያ ግምገማው ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

06 Jan, 09:53


🌲🌲🌲
🌲🌲🌲🌲
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
#እንኳን_ለእየሱስ_ክርስቶስ_የልደት_በዓል_በሠላም_አደረሳችሁ። 🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት እንድሆንልዎ መልካም ምኞቱን ይገኝፃል።
#የኢትዮጵያ_ፈዴራል_ፖሊስ_ወንጀል_ምርመራ_ቢሮ
መልካም የገና በዓል !!🌲🌲🌲🌲🌲🌲
#MERRY_CHRISTMAS
Ethiopian federal police crime investigation Bureau 🌲🌲🌲

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

27 Dec, 14:27


አደገኛ ዕፅ በማዘዋወር የተጠረጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገለፀ
********
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
አደገኛ ዕፅ በማዘዋወር የተጠረጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

ሀገራችንን የአደገኛ ዕፅ ዝውውር መዳረሻ ለማድረግ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው በአዲስ አበባ ከተማ ቤት ተከራይተው አደገኛ ዕፅ ሲያዘዋውሩ የነበሩ፡-

1. ችነዱ ቫሊነቲኒ ችኩዋማ ዜግነት ናይጄሪያዊ አዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፊጋ አካባቢ በቁጥጥር ሥር የዋለ፣

2. ሮባ ዋሲሊዋ ዜግነት ኬኒያዊት አዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋለች፣

3. ጀስቲኒ ላዉራንት ኦንጉዌኔ ዜግነት:ካሜሮናዊ ቦታ: አዲስ አበባ 22 አካባቢ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ሕብረተሰቡ ተመሳሳይ የወንጀል ተግባራትን ሲመለከት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (EFPApp) ወይም በነፃ የስልክ መስመር 991 በመደወል ጥቆማ በመስጠት ወይም መረጃውን በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት በአካል በማድረስ የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

27 Dec, 14:18


በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንትሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ
**************************************
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
በታክስ ስወራ፣ የተጨማሪ ታክስ አለመክፈል፣ በኮንትሮባንድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር ምርመራ ሲያጣራ ቆይቶ ክስ መስርቶባቸዋል።

ግለሰቦቹ የተከሰሱት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1)(ሀ)(ለ)፣ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ አዋጅ 285/94፣ የፌዴራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 116(2)፣ 125(1) እና 132 እንዲሁም ሽብርተኝነትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29(1)(ሀ)(ለ)(ሐ) እና አንቀጽ 2(መ)(ሠ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ተከሳሽ የዌብ ስፕሪክስ አይቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ብርሃኑ አምባዬ 51 ሚሊየን 892 ሺህ 321 ብር የንግድ ትርፍ ፍሬ የታክስ ስወራ ወንጀል በመፈጸም በ2010 ዓ.ም ባለአክስዮን በመሆን በትርፍ ክፍፍል ወቅት 1 መቶ 49 ሺህ 56 ብር ከ73 ሳንቲም ፣ በ2011 ዓ.ም ብር 52 ሚሊየን 2 መቶ 48 ሺህ፣ በ2012 ዓ.ም ብር 593 ሺህ 174 ብር ከ19 ሳንቲም የትርፍ ተካፋይ በመሆን ጥቅም ያገኘ፣ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆኖ ድርጅቱን እየመራ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ያልተፈፀመባቸውን ሶፍትዌሮች ከውጭ ድርጅቶች ጋር የግዥ ውል በመፈረም ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ጥቅም ላይ እንዲውሉ በማድረግ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ተከሳሽ አቶ መቅደስ አክሊሉ ተመስገን ሽብርተኝነትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29(1) (ሀ) (ለ)(ሐ) እና አንቀጽ 2(መ) (ሠ) ሥር የተደነገገውን በመተላለፍ አሸባሪዎችን በገንዘብ በመርዳትና በታክስ ስወራ ወንጀሎች ምክንያት የተገኘውን ገንዘብ ምንጩ እንዲደበቅና ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ባለአክሲዮን እና የቦርድ ሰብሳቢ ሆኖ በትርፍ ክፍፍል ወቅት በ2014 ዓ.ም የደረሰውን ብር 2 ሚሊየን 552 ሺህ 279 ብር ከ47 ሳንቲም በድርጅቱ ውስጥ ያለውን የአክስዮን ድርሻ በማሳደግ እና በ2015 ዓ.ም የደረሰውን 43 ሺህ 110 ብር ከ 90 ሳንቲም ለግል ጥቅሙ በማዋል ክስ የተመሰረተበት መሆኑ ታውቋል።

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

12 Nov, 10:32


Zhongbao Hua'an Group Co., Ltd. የቻይና ካምፓኒ ለፎረንሲክ ሳይንስ ኢኒስቲትዩት ላብራቶሪ በርካታ ማቴሪያሎችን ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በድጋፍ ሰጠ
***************
ህዳር 03 ቀን 2017 ዓ.ም
Zhongbao Hua'an Group Co., Ltd. የቻይና ካምፓኒ ለፎረንሲክ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ላብራቶሪ አገልግሎት የሚውሉ በርካታ ማቴሪያሎችን በድጋፍ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል አስረክቧል።

ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ማቴሪያሎችን ተረክበው ለካንፓኒው ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

የካምፓኒው ማኔጀር ሚስተር Kong Xianming ማቴሪያሉን ድጋፍ ባደረጉበት ወቅት ሰላምና ደኅንነት የአንድ ሀገር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ጉዳይ ስለሆነ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በወንጀል መከላከልና በምርመራ የሚያደረገውን ተግባር በመደገፋችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል ካሉ በኋላ በቀጣይም ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

05 Nov, 13:06


ኢትዮጵያ በ92ኛው የኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው
*****************************
ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
ኢትዮጵያ በ92ኛው የኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች።

በክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ልዑካን ቡድን በእንግሊዝ ግላስኮ ከተማ ከጥቅምት 25 እስከ 28 ቀን 2017 ዓ.ም እየተካሄደ በሚገኘው 92ኛው የኢንተርፖል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በልኡካን ቡድኑ ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ እና የብሔራዊ ኢንተርፖል መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ደጀኔ በቀለ ይገኙበታል።

በጠቅላላ ጉባኤው ላይ ሀገራችንን ጨምሮ የድርጅቱ አባል ሀገራት የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና የተለያዩ ከፖሊስ ጋር በአጋርነት የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒሰትር ኬይር ስታርመር የድርጅቱ አባል ሀገራት ለዓለም ሰላም መስፈን በትብብር በመስራት እያደረጉ ያሉትን ጥረት አድንቀው ሀገራቸው እንግሊዝ ለኢንተርፖል እያደረገች ያለውን ድጋፍ አጠናክራ እንምትቀጥል ገልጸዋል፡፡

በዓታዊው ጠቅላላ ጉባኤ ያለፈው ዓመት የድርጅቱ ሥራ አፈፃጸም እና እየተከናወኑ ስላሉ ተግባራት እንዲሁም በቀጣይ ለማከናወን ስለታቀዱ ተግባራት የተለያዩ አጀንዳዎች ተይዘው ውይይት የሚደረግባቸውና ልዩ ልዩ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉ ይጠበቃል፡፡

ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሸነር ጀነራል ኢትዮጵያ የድርጅቱን ዓመታዊ ጉባዔ ለማዘጋጀት ከሚመለከታቸው የኢንተርፖል ኃላፊዎች ጋር ውይይት በማድረግ ጥያቄ ያቅረቡ ሲሆን የድርጅቱ ኃላፊዎችም በቀጣይ ዓመታት የሚከናወኑ የኢንተርፖል ጉባኤዎች ለአፍሪካ ወይም የድርጅቱን ጠቅላላ ጉባኤ ኢትዮጵያ እንድታዘጋጅ እንደሚያመቻቹ ገልፀዋል፡፡

ልዑካን ቡድኑ ፖሊስ የሚገለገልባቸው ማቴሪያል እና ፖሊስ የሚጠቀምባቸውን ቴክኖሎጂ አምራች ከሆኑ እና ምርታቸውን በጉባኤው ላይ ካቀረቡ ድርጅቶች ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን በቀጣይ ቀናትም ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የሁለትዮሽ ስብሰባ በማድረግ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

02 Nov, 12:32


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ጀነሬተር ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል በድጋፍ ሰጠ፡፡
********************
ጥቅምት 23 ቀን 2017 ዓ ም

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የዋጋ ግምቱ ብር 5,000,000(አምስት ሚሊዮን) የሚያወጣ ጀነሬተር ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል በድጋፍ ሰጥቷል።

ጀነሬተሩ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል ሆነው ከጉዳታቸው እያገገሙ ላሉት ጀግኖች የፖሊስ አመራርና አባላት አገልግሎት እንደሚውል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥና የማዕከሉ የቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር ም/ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ በርክክቡ ወቅት ገልፀዋል። አያይዘውም ጀነሬተሩ ክብደቱ 2700 ኪ.ግራም፣ 200 KV እንዲሁም የዋጋ ግምቱ ብር 5,000,000(አምስት ሚሊዮን) የሚያወጣ ትልቅ አቅም ያለውና በመብራት መቆራረጥ ምክንያት በማዕከሉ የሚከሰቱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያገለግል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በቀጣይም ለማእከሉ የሚደረጉ ድጋፎች በተለያዩ የውስጥና የውጭ አካላት ቀጣይነት ያላቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በድጋፍ የተሰጠውን ጀነሬተርም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የጤና አገልግሎት ዋና መምሪያ ሃላፊ የሆኑት ክቡር ኮ/ር ዶ/ር አብርሐም ተፈራ ተረክበው በማእከሉ ስም ስለተደረገው ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

Ethiopian Federal police Crime Investigation Bureau

24 Oct, 06:44


በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ
*****
ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም
በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 525 ንዑስ አንቀፅ 1(ለ)ሥር የተደነገገውን በመተላለፍ በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ግለሰቦች ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት መቀጣታቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ እንዳስታወቀው በ2016 በጀት አመት በዕፅ ዝውውር ከደረሱ ጥቆማዎች መካከል ጠቅላይ መምሪያው የምርመራ መዝገቦችን በሰውና በሰነድ ማስረጃ አጣርቶ ለዓቃቤ ሕግ ከላከው መዝገቦች ውስጥ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ናቸው ብሎ ውሳኔ ያስተላለፈባቸው፡-
1. ሚ/ር ቺቡኬ ዳንኤል፡- 12 አመት ፅኑ አስራት እና 4,000 ብር መቀጮ፣
2. ሚ/ር ኢጎር ዲማቶስ ዱትራ፡-3 አመት ከ9 ወር ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣
3. ሚ/ር ሉዊስ ሚጎል ኮናሮጂ፡- 4 አመት ፅኑ አስራት እና 4,000 ብር መቀጮ ፣
4. ሚ/ር ኬብሮም ሙንዲሀኪ ፡- 4 አመት ፅኑ አስራት እና 2,000 ብር መቀጮ፣
5. ሚ/ር ሳንጀብ ሙክርጂ ፡-6 አመት ከ6 ወር ፅኑ አስራት  እና 7,000 ብርመቀጮ፣
6. ሚ/ር ሚስ ጊርሊዬ አሚ፡- 3 አመት ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣
7. ሚስ ሄልቪ አልቫላ ፡- 5 አመት ከ6 ወር ፅኑ አስራት እና 5,000 ብር መቀጮ፣
8. ራሄል ለገሰ ፡-3 አመት ፅኑ አስራት  3,000ብር መቀጮ፣                                   
9. ተስፋነሽ አለንሳ፡- 3 አመት ብር ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ ፣
10. ሚስስ ፑርናማ ጊታ፡-15 አመት ብር ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣ 
11. ሚስ ናፈትፓት ኑአመንሮም፡- 4 አመት ከ 5 ወር ፅኑ አስራት እና 5,000 ብር መቀጮ፣
12. ሚስ ዚቱየትነህ፡- 5 አመት ፅኑ አስራት እና በብር 3,000 ብር መቀጮ፣
13. ሚ/ር ማርክ ፖወሊኮወ፡-5 አመት ከ 6 ወር ፅኑ አስራት እና 5,000 ብር መቀጮ፣ 
14. ሚ/ር ኢማኑኤል ኡዙቸክው፡-6 አመት ፅኑ አስራት እና 8,000 ብር መቀጮ፣
15. ባህሩ ወልዴ፡- 12 አመት ፅኑ አስራት፣
16. ሚ/ር አስዋልደረፋይል ሄርና፡- 4 አመት ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ ፣
17. ታምሩ ፍቅሬ፡-12 ዓመት ፅኑ አስራት እና 4,0000 ብር መቀጮ፣
18. ግሬስ አዋርድር፡- 2 አመት ከ9 ወር ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣
19. ሚስ ዜመዬ አዩን፡-5 አመት ከ6 ወር ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣
20. ሚ/ር ሞሀመድ ሳሉሞኪላማ፡- 6 አመት ፅኑ አስራት እና  5,000 ብር መቀጮ፣
21. ሚ/ር ሩአንደርሰደ ሰመዝ፡- 3 አመት እስራት ፅኑ አስራት እና 3,000 ብር መቀጮ፣
22. ሚ/ር አሊዬ አቡዋ፡-4 አመት ፅኑ አስራት  እና 2000 ብር መቀጮ፣
23. ሚስ ቻኒካን ቡናሙኤን፡- 3 አመት ፅኑ አስራት  እና 3,000 ብር መቀጮ፣
24. ሚስስ ቱርናማ ጊታ ሳሪ፡-4 ዓመት ፅኑ አስራት እና 5,000 ብር መቀጮ ናቸው።

የተያዙ ኢግዚቢቶች በአይነት እና በመጠን በአጠቃላይ 176,881.61ግራ ምኮኬን፣ 924,450 ግራም ካናቢስ፣ 32,100.89 ግራም ሄሮይን፣ 5,089 ግራም ሄሮይን እና ሞርፊም መሆናቸው ታውቋል።

ግለሰቦቹ ዕፁን ለማዘዋወር የሚጠቀሙባቸው መንገዶች በሆድ/በሰው አካል ውስጥ/ በማህፀን/ ኮንዶም በመጠቀም፣ በሻንጣ ውስጥ፣ በጫማ ሶል፣ ወፍራም ልብስ በማስመሰል በመልበስ፣ በተለያየ የመኪና አካል ውስጥ፣ በሻንጣ መጎተቻ ብረት ውስጥ በመበየድ እንደሆነ የወንጀል ምርመራ ቡድኑ አረጋግጧል።

የዕፅ የአዘዋዋሪዎቹ ሀገራት:- ናይጀሪያ፣ ኢትዮጵያ ፣ ብራዚል፣ ታይላንድ፣ አንጎላ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ቨንዙዋላ፣ ቢኒን፣ ካሜሮን፣ ናሚቢያ፣ ኮንጎ፣ ኡጋንዳ፣ ኬኒያ፣ ቦሊቪያ፣ ፖላንድ፣ ጀርመን፣ ሴንትራል አፍሪካ፣ ህንድ፣ ቱኒዚያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማላዊ፣ ጅቡቲ፣ ካናዳ፣ ሞዛምቢክ እና ቱርክዬ መሆኑ ታውቋል።

የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋወሪዎቹ መነሻ ብራዚል (ሳኦፖውሎ)፣ ደቡብ አፍሪካ (ጆሃንስበርግ)፣ አዲስ አበባ፣ አንጎላ፣ ታንዛኒያ፣ ኬኒያ እና ሌሎች ሀገራት ሲሆን መዳረሻቸው ደግሞ ናይጀሪያ (ሌጎስ)፣ ደቡብ አፍሪካ (ጆሃንስበርግ)፣ ህንድ፣ ዱባይ፣ አዲስ አበባ እና ታይላንድ ሀገራት ናቸው።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ችሎት 24 የምርመራ መዝገቦችን መርምሮ  በሕግ የተከለከሉ ዕጾችን የማዘዋወር ወንጀል የፈፀሙ  ተከሳሾችን ያርማል፤ ሌሎችን ያስተምራል በማለት ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲሁም  ከ2 ሺህ ብር እስከ 8000 ብር የገንዘብ መቀጮ ወስኖባቸዋል።

በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው  በቁጥጥር ሥር በዋሉት ላይም ምርመራው ተጠናክሮ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።