Latest Posts from አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን (@ayatmekaneyesus) on Telegram

አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን Telegram Posts

አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን
ፕሮግራሞች
👉🏽እሁድ ከ 3 - 5 ሰዐት የፀሎትና የአምልኮ ኘሮግራም።
👉🏽ማክሰኞ ከ 4 - 8 ሰዐት ፆም አና ፀሎት።
👉🏽እሮብ 12:00 - 1:30ተከታታይ ትምህርት።
👉🏽ቅዳሜ ከ 9 -11 ሰዐት የአዳጊ ወጣቶች ፕሮግራም
👉🏽ቅዳሜ ከ 9 - 12 ሰዐት የወጣቶች ፕሮግራም።
2,743 Subscribers
5,606 Photos
33 Videos
Last Updated 01.03.2025 14:01

Similar Channels

EvaSUE |ኢቫሱ
11,035 Subscribers
EQUIP Media/Mamusha Fenta
10,173 Subscribers
GRACE_TUBE ™✍
6,717 Subscribers

The latest content shared by አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን on Telegram


የካቲት/9/17
(February/16/25)
የመልዕክት አቅራቢ: ቄስ መንግስቱ ገ/ሚካኤል
የመልዕክት ክፍል:(2ነገ 2:19-22)
ርዕስ: ከእንግዲህ ወዲያ ሞትና ጭንገፋ አይሆንም
መግቢያ: ኤልያስ እና ኤልሳዕን አሁን ከጠቀስነው ክፍል ከፍ ብለን ስናነብ እናገኛቸዋለን። የኤልያስ ወደ ሰማይ ማረግ ለነብያት ልጆች ተገልጦ ነበር። ለኤልሳዕም ሲነግሩት እናያለን። የመነጠቂያው ሰዓት በደረሰ ጊዜ የእሳት ሰረገላ መጣና ሁለቱን ነጠላቸው። በኤልሳዕም ላይ የእግዚአብሔር መንፈስ ሁለት እጥፍ ሆኖ ወረደበት።
-የኤልሳዕ አገልግሎት የጀመረው ዮርዳኖስን በመክፈል ነበር። ኤልያስ በአገልግሎቱ መጨረሻ ዮርዳኖስን ከፈለ። ኤልሳዕ ግን በአገልግሎቱ መጀመሪያ ዮርዳኖስን ከፈለ። መንፈሱ በእጥፍ በእርሱ ላይ እንዳለ በዚ እንረዳለን።
-ከዚህም ቀጥሎ ነበር የኢያሪኮ ሕዝብ ወደ ኤልሳዕ ተሰብስበው የመጡት። ከተማዋ መልካም ብትሆንም ውኃዋ ግን ክፉ ነበር። ፍሬዎቿም ይጨነግፋሉ።
         ጭንገፋ ምን ማለት ነው?
-ጨነገፈ ማለት የማይጠቅም፣ የማይረባ ሆነ ማለት ነው። ዋጋ የተከፈለበትን ነገር ማጣት ማለት ነው። ይህ ከባድ ነገር ነው።
-የኢያሪኮ ከተማ ከተገነባች በኋላ ሀያ ጊዜ እንደፈረሰች ታሪክ ያመለክተናል። ለምን? ያልተሰበረ መርገም ነበረ። ከተማይቱ በሞት እና ጭንገፋ እርግማን ተቸግራ ነበር።
-ለዚህ እርግማን የመጣባቸው ባለመታዘዝ ምክንያት ነበር። ይህ የሆነው ምድር በአዳም እና ኃጥያት ምክንያት የተረገመች ስለነበር ነው። አለመታዘዝ በእርግማን ስር ይጥላል። ነህምያም ኢያሪኮን የሚገነባ ሰው የተረገመ እንዲሆን በሕዝብ ፊት ተናገሮ ነበር።
           ይህ ጭንገፋ እንዴት ቆመ?
የእግዚአብሔር ሰው በመካከላቸው ሲገኝ ጭንገፋ እና ሞት ቆመ።
-አዲስ ማሰሮን አስመጣ፣ ጨውንም አድርጎ ውኃው ወዳለበት ምንጭ ጨመረው። ከዛች ደቂቃ ጀምሮ ውኃው ተፈወሰ፣ ጭንገፋ እና ሞት ቆመ። ምደሪቱም ፍሬዋ ተፈወሰ።
-ለእኛም ሰላም ይሆንልናል። ታሪካችንን ይቀይርልናል፣ ሞት ይሰበርልናል፣ መከራ ይሰበርልናል፣ የድሮ መጠሪያችን ይቀየርልናል፣ አይቶ ማጣት ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፣ ሸክም ተሸክሞ መኖር ያበቃል። እግዚአብሔር ዛሬ በሕይወታችን ጣልቃ ይገባልናል። ባደከመን ነገር፣ ከእንግዲህ ምን ቀረን ባልንበት ጉዳይ እርሱ ጣልቃ ይገባልናል!
                      ማጠቃለያ
እግዚአብሔር ማንንም ፈፅሞ አይጥልም። በጨነገፈብን ነገር እርሱ ጣልቃ ይገባል። ከእንግዲህ ወዲህ ሞት እና ጭንገፋ አይሆንም! አሜን!

የእሑድ አምልኮ የካቲት 9 - 2017 ዓ.ም የአያት መካነ ኢየሱስ ማ/ም የእሑድ መደበኛ አምልኮ ፕሮግራም 👇 የማምለኪያ ስፍራ አድራሻ 👇
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8

የእሑድ አምልኮ የካቲት 9 - 2017 ዓ.ም የአያት መካነ ኢየሱስ ማ/ም የእሑድ መደበኛ አምልኮ ፕሮግራም 👇 የማምለኪያ ስፍራ አድራሻ 👇
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8

አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን pinned «https://youtu.be/ZQiQJNAmK9g»

https://youtu.be/ZQiQJNAmK9g

https://youtu.be/TyhLNh4UBcw

የረቡዕ ጥር 28 - 2017 ዓ.ም የአያት መካነ ኢየሱስ ማ/ም የረቡዕ መደበኛ ትምሕርት ፕሮግራም የፎቶ ምልከታ 👇 የ ማለኪያ ስፍራ አድራሻ 👇
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8

የረቡዕ ጥር 28 - 2017 ዓ.ም የአያት መካነ ኢየሱስ ማ/ም የረቡዕ መደበኛ ትምሕርት ፕሮግራም የፎቶ ምልከታ 👇 የ ማለኪያ ስፍራ አድራሻ 👇
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3KjBLn8

25/5/17
(Feb /2/25)
የመልዕክት አቅራቢ :ዶ/ር ግርማ በቀለ
የመልዕክት ክፍል:(ማቴ 28:18-20)
ርዕሰ : ስልጣን ሁሉ ተሰቶኛል
መግቢያ: ጌታ ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ላይ ለመጨረሻ ጊዜ ሲሰናበት "ስልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ" በማለት የስልጣን ሁሉ ባለቤት እንደሆነ ያሳየናል። በእርግጥ ስልጣኑ የት ነበር? ማን ነው የሰጠው? ከመስጠቱስ በፊት ስልጣኑ በማን እጅ ነበር? የሚሉትን ጥያቄዎች ልንጠይቅ እንችላለን።
-ስልጣን የሰጠው እግዚአብሔር ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ በምድር ሲመላለስ ባለ ሙሉ ስልጣን ነበር። በብዙ ነገሮች ላይ ስልጣን ተሰቶት ነበር። የኢየሱስ ክርስቶስ ስልጣን እንዴት እንደተገለጡ ከታች እናያለን።

  ስልጣኑ የተገለጠባቸው ሰባት(7)ነገሮች
ክርስቶስ ኢየሱስ ስልጣን ሁሉ ተሰጥቶኛል ወደ አለም ሁሉ ሂዱ ያለው በዚህ ስልጣን ነው።

1) የሁሉ ፈጣሪ ነው: እግዚአብሔር አምላክ ፈጣሪ ነው። ሰማይንና ምድርን ያፀና እርሱ ነው። ጌታችን ኢየሱስም በምድር ሲመላለስ ፈጣሪነቱን አሳይቷል። ሰዎችን ከህመማቸው በሚፈውስበት ጊዜ አይን ለሌለው ዓይንን ይሰጥ ነበር፣ ጤና ላልነበረው ጤናን ይሰጣል። ይህ በሰው እና ተፈጥሮ ላይ ያለውን ስልጣን ያሳያል።
2) ፍጥረትን ደግፎ ይይዛል: እግዚአብሔር ፍጥረትን ሁሉ ደግፎ የያዘ አምላክ ነው። አእዋፋትን የሚመግብ፣ የሚያኖር እርሱ መሆኑን ጌታ ኢየሱስ በትምህርቱ ላይ አሳይቶናል። ለምድር በወቅቱ ዝናብን የሚሰጥ አምላክ መሆኑ ስልጣኑን ጌታ ኢየሱስ ብዙዎችን በመመገብ እግዚአብሔር ሰውን እንደሚያስብ አሳይቷል።
3) በተፈጥሮ ላይ ስልጣን አለው: የፍጥረት ጌታና ገዢ ነው።ፀሀይን ከዋክብትን ሁሉ ስርአታቸውን ጠብቀው ይኖራሉ ።
4) በሀጥያት ላይ ገዢ ነው: ሀጥያታችንን ሁሉ ተሸክሞ አንፅቶናል ።ክርስቶስ ኢየሱስ ከፍለን የማንጨርሰውን እዳ ከፍሎልናል ።የዘለዓለም ሞታችንን ወሰዶልናል ።
                   ማጠቃለያ!
ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ሂዱ ያለው በዚህ ስልጣን ነው ስለዚህ የሚያቆማት ፣የሚቋቋማት ማንም የለም! አሜን!

የእሑድ አምልኮ ጥር 25 - 2017 ዓ.ም የአያት መካነ ኢየሱስ ማ/ም የስጦታ ጊዜ አምልኮ ፕሮግራም 👇 የማምለኪያ ስፍራ አድራሻ 👇
https://maps.app.goo.gl/H4Wc2TxN7W3Kj...