መዝሙር 150
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤ በኃይሉ ጠፈር አመስግኑት።
² በችሎቱ አመስግኑት፤ በታላቅነቱ ብዛት አመስግኑት።
³ በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።
⁴ በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት።
⁵ ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት።
⁶ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን፦ ሃሌ ሉያ።