ዲማስ DIMASE ديماس

@officialdemas


ይህ ቻናል በአህለል ሱና ወልጀማዓ የተደረጉ ዳእዋዎችና በዲናዊ አዝናኝ ግጥሞች ፤ሀዲሶች ታሪኮች እናንተን ማዝናናት ነው። በተጨማሪም የተደበቁ የጴንጤዎች ተንኮልና አደጋዎች ወደ ህዝበ ሙስሊሙ ያደርሳል። በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የተጋረጠ ወቅታዊ አደጋም ካለ እየመረመረ ያደርሳል። ይህ ሁሉ የሚሆነው በአሏህ ፈቃድ ነው። ይግቡ ይቀመጡ ይዝናኑ ይማሩ የናንተ ሚድያ ነው።
#ይህ #የዲማስ #ቴሌግራም #ነው

ዲማስ DIMASE ديماس

22 Oct, 17:28


አጂብ❗️የመርካቶው እሳትና ሙስሊሙ ሰውዬ በአሏህ ቀደር የማመኑ ልኬት❗️

ይህ ሰው በመርካቶ ንብረታቸው ከወደመባቸው ሰዎች አንዱ ነው።

እንዲ ሲል ተናግሯል።

አልሀምዱሊላህ! በውሳኔህ ተሳስተህ አታውቅም

ብዙ ሰተኸኝ ነበር ጥቂት ወስደህብኛል ክብርና ልቅና ላንተ የተገባ ይሁን!

አሁንም ቢሆን የጉዳት መጠናችን በውል አልታወቀም ቢሆንም  የብዙዎች ወንድሞቼ ንብረት በአጠቃላይ በሚባል መልኩ ወድሟል አላህ ለሁላችንም መፅናናትን ይስጠን የተሻለውን አላህ ይተካልን!!

ሲቀጥል ብዙዎቻችሁ CBE account እየተቀባበላችሁ ልታግዙኝ እየሞከራችሁ ነው!!! በጣም አመሰግናለው!! ግን እኔ ከብዙ አላህ ከሰጠኝ ፀጋ በጥቂቱ ስለሆነ የነካኝ ለኔ የምታረጉትን ገቢ  ለወንድሞቼ እንድታረጉ በትህትና እጠይቃለው!!! እንዲሁም የኔን የለጠፋችሁትን እንድትሰርዙት በአክብሮት እጠይቃለው!!!!(ሸገር ፕረስ)

Via: ሐሩን ሰዒድ

አንተና እኔ ብንሆንስ ምንድን ነበር የምንለው????

የኔን ለኔው ተውት ሁሉም እራሱን ይፈትሽ ትዕግስት! ትዕግስት! ትዕግስት!

ስንቶቻችን ሀዲስና ቁርአንን እናነበንበዋልን እስከ ወበሺሪ አሷቢሪን ድረስ ነገር ግን
ስራ የለም
ስራ ቀዝቅዟል
ወይኔ ልጆቼ ምን ላበላቸው ነው?

አንድ ቀን እንኳን አሏህን በስርአቱ ሳናመስግን ውለን እንገባለን።

ይህ ሰው ግን ንብረቱ ወድሞበትም ያለው ቃል ቢኖር (ኧልሐምዱሊላህ በውሳኔህ ተሳስተህ አታውቅም ብዙ ሰጥተኸኝ ትንሽ ወሰድክብኝ)

ያአሏህ አንተም በመልካሙና በበላጩ ተካለት!!!!አሚን

ዲማስ DIMASE ديماس

22 Oct, 13:25


🗳«መርካቶ ላይ በተከሰተው እሳት ሙሲባ ለደረሰባቸው ወንድሞች ማፅናኛ እና ምክር»

📌 በሚል ርዕስ መደመጥ ያለበት እጥር ምጥን ያለ ገሳጭ እና መካሪ የሆነ ነሲሃ።

🎙 በሸህ:-አቡ ቀታዳ አብደላህ አለህ ይጠብቀው።

🕌 በመርከዘ አስ ሱና ቂልጦ ጎሞሮ አለህ ይጠብቃት

ـــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ
📲አጠቃላይ ፕሮግራሞቻችን ለመከታተል:-

🖥️ በ Telegram~Channel
📎
https://t.me/merkezassunnah/12048

ዲማስ DIMASE ديماس

22 Oct, 05:16


ቪድዮ⁉️የመርካቶ አሁናዊ ሁኔታ ትላንት ማራኪ የነበረችው መርካቶ ዛሬ ላይ እንዲህ ሆናለች።

وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَيْءٍ مِّنَ الْخَوْفِ وَالْجُوعِ وَنَقْصٍ مِّنَ الْأَمْوَالِ وَالْأَنفُسِ وَالثَّمَرَاتِ ۗ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ

ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በገነት) አብስር፡፡

ዲማስ DIMASE ديماس

22 Oct, 03:13


⚠️ ተውበት ማድረግ በሚል ርዕስ ወቅታዊ ቆየት ያለ የኹጥባ ትርጉም!

🎙 ኡስታዝ ሙሀመድሰዒድ ቢን በድሩ حفظه الله

📎 https://t.me/mesjidalsunnah/15712

ዲማስ DIMASE ديماس

22 Oct, 02:41


⭕️#መርካቶ

" እኔ የመርካቶ ልጅ ነኝ፤ እዛውም ነው የምሰራው።

ዛሬ በአይኔ ያየሁት የእሳት አደጋ እጅግ አስከፊ ነው።

በጣም ብዙ ንብረት ወድሟል። የአላህ ጥበቃ ሆኖ እኔ በአካባቢዬ ላይ የሰው ህይወት አልተጎዳም።

ነገር ግን በእሳት አደጋው እጅግ በጣም አዝነን እያለ ተጨማሪ ሃዘን የፈጠረብን ብዙ አለ።

አንዱ የተለያዩ አካላት ለዝርፊያ ያደረጉት እንቅስቃሴ ነው።

አንዳንድ ሰው በዚህ የከፋ ጊዜ አብሮ ተጋግዞ እሳቱን ማጥፋት ሲገባው የራሱ ያልሆነን ንብረት ለመዝረፍ ሲሯሯጥ ማየት እጅግ ያሳዝናል።

ሌላው በየማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተከታይ ለማፍራት ሲባል ያልተባለውን በማለት፣ ያልተደረገውን ተደርጓል በማለት ' ላይክ ፣ ሼር ፣ ፎሎው ' አድርጉን እያሉ በዚህ የችግር ወቅት ያልተገባ ነገር የሚያደርጉ ሰዎችን መመልከቴ አሳስዝኖኛል።

አንዳንዶቻችን ህሊናችንን በዚህ ልክ ማጣታችን እጅግ አሳፋሪ ነው። ነገ እኛን ምን እንደሚገጥም እኮ አናውቅም።

ይህ ከባድ አደጋ እውነተኛ መንስኤው እና የጉዳቱ መጠን በፍጥነት እንዲጣራልን እንፈልጋለን።

ብዙ ለፍቶ አዳሪ ዜጋ እጅግ የደከመበት ፣ የለፋበት ንብረቱ በአንድ ምሽት ወደ አመድነት ተቀይሯል። " - ሃሚ (መርካቶ)


ቲክፋ

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 20:52


⁉️በእሳቱ ጉዳይ አጭር መልእክት⁉️
ጠርጣሪ ተጠርጣሪውን እንዲጠረጥር ጠርጥሮ ማስጠርጠር እንደሚያስጠረጥር ተጠርጣሪውን ይዞ ይጠረጥራል ይጣራል።


መልእክቱ ከገባችሁ በኮመንት አስቀምጡልን

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 20:47


ሌቦች አስቸግረው ነበር።ሙሉ መረጃ ሲኖረኝ አደርስላችኋለሁ።

ሀገር ሲወድም የሰው ህይወት ሲጠፋ ሌቦች ግን ታዘብናችሁ......

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 20:41


⭕️እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል❗️
መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል።

መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል፡፡

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ የእሳት አደጋዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ርብርብ ላደረጉ፤ በርካታ ሎጀስትክ በማቅረብ የደገፉ እና ከዚህ በላይ ሊደርስ የነበረዉን ጉዳት የቀነሱ አካላትን አመስግነዋል፡፡

በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳትና መንስኤዉን በማጣራት ቀጣይ ለህብረተሰቡ የምናሳዉቅ ይሆናልም ብለዋል፡፡

ህብረተሰቡ መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም  አሳስበዋል፡፡

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 20:19


ምሽት 1 ሰዓት አካባቢ በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳውን እሳት እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር ማዋል አልተቻለም።

ርብርቡ ግን እንደቀጠለ መሆኑ ተሰምቷል።

የአዲስ አበባ እሣትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍቅሬ ግዛው ምን አሉ ?

- የእሳት አደጋው የተከሰተው 1 ሰዓት ገደማ ነው።

- እሳት መነሳቱን በሰማን ጊዜ አብዛኛዎቹ የእሳት ማጥፊያ መኪናዎች ርብርብ እንዲያደርጉ አሰማርተናል።

- መኪናዎች በወቅቱ ነበር የደረሱት፤ ከደረሱ በኃላ የእሳቱ ባህሪና ሁኔታ ሲታይ ለሌሎች አጋዥ አካላት ፦
° አየር መንገድ
° ፌዴራል ፖሊስ
° ሌሎች ከተማ ውስጥ ያሉ ውሃ አቅራቢ ተቋማት በሙሉ እንዲረባረቡ ተደርጎ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት እያደረግን ነው።

- ቦታው በጣም አስቸጋሪ ነው።

- በሁሉም አቅጣጫ በኩል መኪና ገብቶ እሳቱን ለማጥፋት በጣም ፈትኖናል። በተለይ በዙሪያ የሚቀመጡ እቃዎች ቶሎ ተገብቶ የእሳቱን መሰረት እንዳይመታ አድርጓል።

- አካባቢው በቆርቆሮ የተያያዘ ነው። መንገዱ በጣም ጠባብ ነው። ገብተን ለማጥፋት ተቸግረናል።

- በአጋጣሚ ባለሱቆች፣ ነጋዴዎች ዘግተው ወጥተው ነበር። የቆሙ መኪኖችንም ለማስነሳት ችግር ሆኖብን ነበር።

- አሁን ላይ ከቅድሙ እየተሻሻለ ነው። የመቀነስ እና የመጥፋት አዝማሚያ አለው። በተለይ ከዚህ እንዳይሰፋ ወደታች ከወረደ በጣም ሰፊ ቦታ ነው ያለው ቆርቆሮ በቆርቆሮ እሱ ጋር እንዳይደርስ ከበን ለመያዝ ሞክረናል።

- አጋዦች ከመጡ በኃላ እሳቱ ባህሪው እንዳይሰፋ ተሞክሯል። አሁንም ህብረተሰቡ አግዞን ለማጥፋት እየሞከርን ነው። እናጠፋዋለን ብለን እናምናለን።


ከሚድያ

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 20:15


እሳቱን መቆጣጠር አልተቻለም።

በሄሊኮፕተር እየተምከረ ነው

መርካቶ ሸማ ተራ

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “ አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት ነው ። በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው “ ሲሉ ገልጸዋል።

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 19:57


#መርካቶ🚨

በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳው እሳት እስካሁን ሊቆም አልቻለም።

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 19:45


አይ ዱኒያ…

እሳቱ በተነሳበት ወቅት ንብረታቸውን ሊያድኑ የገቡ ሰዎች ተመልሰው  መውጣት ባለመቻላቸው ከ4ኛ እና 5ኛ ፎቅ ራሳቸውን ወርውረው ህይወታቸውን አጥተዋል ተብሏል። አላህ ይዘንላቸው።

ሌሎቻችሁ ቢያንስ ተረጋጉ፤ እናንተ ኑሩ እንጂ ንብረት ይተካል።
ምንም እንኳ አንድት ምሽት የነበረን ወዳልነበር ብትቀይረውም። አላህ የተሻለ አለው። አይዞን በአላህ!

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 18:50


በሄሊኮፕተር ማጥፋት ያስፈለገው እሳቱ ከባድ እና አስቸጋሪ ስለሆነ ነው።


وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَيْءٍ مِّنَ الْخَوْفِ وَالْجُوعِ وَنَقْصٍ مِّنَ الْأَمْوَالِ وَالْأَنفُسِ وَالثَّمَرَاتِ ۗ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ

ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በገነት) አብስር፡፡

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 18:36


በሂሊኮፕተር ለማጥፋት⁉️

መርካቶ ' ሸማ ተራ ' የተነሳው ከባድ የእሳት አደጋ እስካሁን አልቆመም።

እሳቱን መቆጣጠር አልተቻለም።

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ " አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት ነው " ብለዋል።

አሁን ላይ " በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 17:33


⭕️መርካቶ እሳት ተነሳ🩸

መርካቶ ሸማ ተራ እሳት ስለተነሳ የሚመለከታችሁ አካላት ቶሎ ለመቆጣጥር ሞክሩ። አላህ ይድረስላችሁ እዛ ንብረት ያላችሁ ወንድምና እህቶች። አብሽር! ሰው ደህና ይሁን እንጂ ንብረት ይተካል። ለኸይር ነው።

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 16:42


⭕️በሀገራችን የሞት ቅጣት ተወሰነባቸው❗️
ኮንትራት በመጥራት ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላለፈባቸው

በተለያዩ ጊዜያት አሽከርካሪዎችን  ራቅ ወዳለ ስፍራ እየወሰዱ በመግደል ተሽከርካሪዎችን ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር  ስር ውለው በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

በአዲስ አበባ ገላን ክፍለ ከተማ፣ በሳሪስ እንዲሁም በቢሾፍቱ መኖሪያቸውን ያደረጉት ቴዎድሮስ ብርሃኔ እና  እዩኤል ቴዎድሮስ እንዲሁም በሌላ በኩል ተፈሪ ተስፋዬ እና ዩሃንስ አረፋ  የተባሉት ግለሰቦች  ከአዲስ አበባ ቢሾፍቱ በመመላለስ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር  የሸገር ከተማ አስተዳደር  ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤት የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ ዓቃቢ ህግ አቶ ሚዴቅሳ አጋሩ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አራት ግለሰቦች ከግል ተበዳዮች በኮንትራት በመውሰድ ከዋናው መንገድ ውጪ በማስውጣት የአሽከርካሪዎቹን ህይወት በማጣፋት ተሽከርካሪዎቹን ይዞ በመሰወር  ለተለያዩ ጋራዦች እና  ግለሰቦች በመሸጥ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር ተገልጿል። ቴዎድሮስ እና እዮኤል የተባሉት ተከሳሾች   ሰለሞን አሊ የተባለ  የጭነት ተሽከርካሪ   አይሱዚ አሽከርካሪን ከዱከም ከተማ እንጨት ትጭንልናለህ  በማለት በኮንትራት ዋጋ  ተስማምተው ወደ ቢሾፍቱ ከተማ ያቀናሉ።

በመቀጠል ወደ ሰንዳፋ  መስመር እንዲሄድ በጦር መሳሪያ በማስገደድ ጨፌዶሳ የተባለ ቦታ  ሲደርስ በሽጉጥ በመምታት ጥለውት ተሽከርካሪውን  ይዘው ተሰውረው ቆይተው እንደሸጡት ተገልጿል ። በሌላ በኩል ተፈሪ ተስፋዬ እና ዩሃንስ አረፋ  የተባሉት የሁለተኛው የወንጀል ቡድን አባላት ደግሞ አቶ  ከበደ በለው የተባሉ ነዋሪነታቸው  አዲስ አበባ  አቃቂ አካባቢ  የሆኑ እና ሃይሩፍ የህዝብ ማመላለሻ  ሚኒባስ  ከአዲስ አበባ አሰላ በማሽከርከር የሚተዳደሩ ሲሆን  ከቦሌ አውሮፕላን  ማረፊያ  ሰው እናመጣለን በማለት  ከወሰዷቸው በኋላ በመሳሪያ በማስገደድ  ወደ ገላን ከተማ በመውሰድ በገመድ አንቀው በመግደል ተሽከርካሪውን  በጎሮ በኩል  ገላን ከተማ በመውሰድ አንዶዴ የተባለው ቦታ  አስከሬኑን ጥለው መሰወራቸውን ዓቃቢ ህጉ ገልፀዋል።በተመሳሳይ  የሜትር ታክሲ አሽከርካሪው ሚኪያስ ተስፋዬ የተባለ የ28 ዓመት ወጣት   እየኤል ቴዎድሮስ የተባለው ማታ ላይ  ደውሎለት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ  የምንቀበለው  እንግዳ አለ  በማለት ምሽት ላይ ቢሾፍቱ ከተማ በተከራዩበት ቤት በመውሰድ በሽጉጥ መግደላቸውን  የፖሊስ ማስረጃ አረጋግጧል።

ፖሊስ ባደረገው ክትትል ቴዎድሮስ ብርሃኔ  እና  እዮኤል ቴዎድሮስ በቁጥጥር  ስር  በማዋል  የምርመራ ሂደቱ ሲያጣራ የቆየ ሲሆን በዚህም ሰለሞን የተባለው አሽከርሪውን ገለው ጫካ ውስጥ መጣላቸውን  የጭነት  ተሽከርካሪውን በ700ሺህ ብር  መሸጣቸውን  ለፖሊስ መርተው  አሳይተዋል። በመቀጠል  ሚኪያስ  ተስፋየ የተባለውን አሽከርካሪ ገድለው እንደጣሉት እና  ኮሮላ ተሽከርካሪውን   የደበቁበትን ቦታ ለፖሊስ ይጠቁማሉ። ፖሊስ ምርመራውን በመቀጠል  የአቶ ከበደ ገዳዮችን ለመያዝ  ባደረገው  ክትትል አዲስ አበባ ሳሪስ  ዶሮ ተራ ከሚባል ስፍራ በመያዝ  በሁለቱም ግለሰቦች ላይ ጥልቅ ምርመራ በማድረግ ሃይሩፍ ተሽከርካሪውን እንዲፈታታ በማድረግ  ለመሸጥ ሲሞከር  በቁጥጥር  ስር ለማዋለወ ተችሏል ።  በመሆኑም  ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በማጠናቀቅ  ለዓቃቢ ህግ ይልካል።

ዓቃቢ ህግ ከፖሊስ የደረሰውን የምርመራ መዝገብ  በመመልከት  ተከሳሾች በመደራጀት የጦር መሳሪያ  በመታጠቅ በአሰቃቂ ሁኔታ  የሰው መግደል ወንጀል  መፈጸማቸውን በመጥቀስ  በወንጀል ህግ 530 መሰረት ክስ መስርቷል። በዓቃቢ ህግ የተመሰረተውን  ክስ የተመለከተው የሸገር  ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራቱም ተከሳሾች  የፈጸሙት የወንጀል  ድርጊት  በመመልከት  ከባድ እና አደገኛ  በመሆኑ  የቅጣት ማክበጃ በመጥቀስ  በአራቱም ተከሳሾች ላይ በሞት እንዲቀጡ  ውሳኔ አስተላልፏል። በተጨማሪም ተሽከርካሪዎች  የደበቁ  አራት ግለሰቦች  በእስራት እና  በገንዘብ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ማስተላለፉን የሸገር ከተማ አስተዳደር  ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤት የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ ዓቃቢ ህግ  አቶ ሚዴቅሳ አጋሩ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ማቅለያ ማካካሻ መካሻ ተብሎ ካልተሻረ ከተረጋገጠ አሪፍ እርምጃ ይሆናል።

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 13:21


ተአምራዊው ሚሳኤል⁉️የጀርመን፣ የብሪታንያ እና የአሜሪካ መንግስታት ይህንን ሚሳኤል ለአሸባሪው የጽዮናውያን ወራሪ ሀይል በጋዛ ውስጥ ያልታጠቁ ፍልስጤማውያንን ለመግደል ቢልኩትም ሚሳኤሉ ግን ቤት ላይ ወድቆ ሳይፈነዳ ቀረ። የፍልስጤም ተዋጊዎች እንደገና ተጠቅመውበት የአሸባሪው የጽዮናውያን ታንኮች አፈነዱበት።

🇵🇸

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 13:19


እስከወዲያኛው አስወግደውታል⭕️

ዲማስ DIMASE ديماس

21 Oct, 04:08


ምስክርነት ከራሳቸው አፍ⁉️ይህ ክርስቲያን የነበረ ሰው መሰረታዊ በክርስትና ውስጥ ያሉ አወዛጋቢ የሆኑ ርእሶችን አንስቶ ያወጋናል።

አዳምጡትና ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር በአኽላቅ ተወያዩባቸው።

ማንኛውም ሰው 100% ማሰብ ከቻለ ሙስሊም ይሆናል።

6,299

subscribers

958

photos

526

videos