አርበኛ መከታው የሚመራው ዕዝ እና ኮማንደር አሰግድ የሚመራው ወደ አንድ እንዲመጡ ለወራት ዕንቅልፍ እያጣን ስንለፋ ከቆየን በኋላ እንደ "ዋን አማራ" ባሉ ተልእኮ ያላቸው ሰርጎ ገቦችና ሌሎች ጣልቃ ገቦች ምክንያት ይህ በመሆኑ ማዘናችን እሙን ነው። ጠላት ደስ ቢለውም የአማራው ትግል በዚህ አይሰናከልም። ደፍርሶም ቢሆን ይጠራል። አማራ አንድነቱን አጽንቶ ያሸንፋል። መላው የሸዋ አማራ ፋኖ [ከፍ ሲልም መላው የአማራ ፋኖ] የልዩነት ምክንያቶችን ንቆ ሕዝብን በማስቀደምና ወደ አንድ በመምጣት ጠላትን (አገዛዙን) ያሳፍር ዘንድ ጥሪ አቀርባለሁ። አሉ የሚባሉ የመርሕ ጥያቄዎችና የርእዮተ ዓለም ጉዳዮች በውይይትና በሙግት፣ በጥበብና በምሁራዊ ክሕሎት፣ ብሎም በሠለጠነ መንገድና በአማራዊ ባህል ይፈታሉ። መሪዎችም ዘለዓለማዊ አይደሉም።
ድል ለአማራ ሕዝብ።