M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

@mormediumtaxpayersbranchoffice


This is official Telegram Channel of M.o.R Medium Tax payers No 1 Branch office
Join the channel.

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

22 Oct, 10:48


የመመዘኛ ፈተና ተሠጠ፡፡

ጥቅምት 12/2017 ዓ/ም

በገቢዎች ሚኒስቴር በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር አንድ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት ክፍል አንድን ላጠናቀቁ ሁለተኛ ዙር የምጁላር ሥልጠና ተከታታዮች የመመዘኛ ፈተና ተሠጠ፡፡

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

21 Oct, 08:01


የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት አገልግሎት ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች

  እንዲሰጠው በጽሑፍ ጥያቄ ማቅረብ፤
  ውዝፍ የታክስ ዕዳ /ወቅታዊ የታክስ ክፍያ የፈፀመ ወይም ለመክፈል የክፍያ ስምምነት የገባና በውሉ መሠረት እየተከፈለ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ፤
  በደረሰው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ላይ ቅሬታ ያለው ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ ክፍል ወይም ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን ወይም በየደረጃው ለሚገኝ ፍርድ ቤት ቅሬታውን አቅርቦ በመታየት ላይ የሚገኝ ስለመሆኑ የጽሑፍ ማስረጃ ማቅረብ አለበት፡፡
  ታክስ ከፋዩ የታክስ ነጻ መብት ያለው ወይም በግብር እፎይታ ጊዜ ላይ ያለ ስለመሆኑ የጽሑፍ ማስረጃ፤
  በግብር ዓመቱ በታክስ ከፋይነት ያልተመዘገበ ከሆነ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር አለመውሰዱ እና የታክስ ፋይል በስሙ አለመከፈቱ አስኪረጋገጥ፤
  በንግድ ሥራ ፍቃዱ ምንም ዓይነት ሥራ አለመሥራቱን የገለጸ ታክስ ከፋይ አለመሥራቱ እስኪረጋገጥ፤
  በኮንስትራክሽን ማሽነሪ ማከራየት ዘርፍ የተሠማራ ታክስ ከፋይ፣ በታክስ ጊዜው ታክስ ያልከፈለው ማሽነሪው በመበላሸቱ ምክንያት መሆኑንና ይህንኑ በታክስ ሕጉ መሠረት ማስታወቁን እና ለዚሁም በ3ኛ ወገን የተረጋገጠ ማስረጃ እስኪያቀርብ፤
  ታክስ ከፋዩ ቦሎ ለማደስ የኮንስትራክሽን ማሽን በመበላሸቱ ምክንያት ያለመስራቱን በ30 ቀናት ውስጥ ማስታወቁ እስኪረጋገጥ፤
  የኮንስትራንሽን ማሽነሪ ለመሸጥ ከሆነ ማሽነሪው ከቆየበት ቦታ (ጋራዥ) ወይም ከቆመበት ቀበሌ አስተዳደር ማረጋገጫ ማስረጃ እስኪያቀርብና እስኪረጋገጥ፤
  በታክስ ጊዜው ታክስ ያልከፈለው የተሽከርካሪው ሊብሬ እና ታርጋ ለመንገድ ትራንስፖርት በመመለሱ/መድን ድርጅት ቅሪት አካልን በመረከቡ ምክንያት ስለመሆኑ ማስረጃ እስኪያቀርብ፤
  የወጪ መጋራት አገልግሎት/ክፍያ ተጠቃሎ እስኪፈጽም ድረስ፤
  ከታክስ ከፋዩ የሚፈልገው ታክስ የሚሰበሰብ ስለመሆኑ ስጋት ሲኖረውና ታክሱ በአስቸኳይ መሰብሰብ ያለበት ሆኖ ሲገኝ ታክሱ ሳይሰበሰብ የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት አይሰጥም፡፡

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

19 Oct, 13:40


👉 በሥራ ሰዓት ብቻ ሳይሆን (በሳምንት 7 ቀን በእያንዳንዱ ቀን ለ24 ሰዓት ወይም 365 ቀን) ግብርን ማስታወቅ ያስችላል፡፡
👉 ፈጣን፣ ዘመናዊና ከፍተኛ ጥራት ያለው አገልግሎት ያስገኛል፡፡
👉 አላስፈላጊ የጊዜ፣ የሰው ሃይል እና የገንዘብ ወጪዎች ይቀንሳል፡፡
👉 በየጊዜው የሚሰወሩና የሚጠፉ ሰነዶችን በቀላል መንገድ መቆጣጠር ያስችላል፡፡
👉 ግብር ከፋዮች ክፍያን ለመፈፀም ወደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መሄድና ወረፋ መያዝ ሳይጠበቅባቸው በየትኛውም ቦታ ሆነው ግብራቸውን አስታዉቀው መክፈል ያስችላቸዋል፡፡
👉 አደጋን/የገንዘብ መጥፋትን ይቀንሳል፡፡

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

18 Oct, 07:46


ማንኛውም አሰሪ፡-

1. የቀጠራቸውን ተጠቃሚዎች ዝርዝር ለባለሥልጣኑ ወይም ለሚመወክለው የማስታወቅ፣
2. በገንዘብ ለመክፈል ግዴታ ከገቡ ተጠቃሚዎች የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳይ ማስረጃ ከተጠቃሚዎቹ በመቀበልና ስለ ትክክለኛነቱ ከሚኒስቴሩ በማረጋገጥ በየወሩ ከጥቅል ደመወዛቸው ቢያንስ 10% እየቀነሰ ከእያንዳንዱ ወር መጨረሻ አንስቶ ባሉት ሰላሳ ቀናት ውስጥ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የመክፈል፣
3. ተጠቃሚዎች ከተቋሙ የተሰጣቸውንና የሚፈለግባቸውን እዳ የሚያሳየውን ማስረጃ ለመስጠት ፍቃደኛ ካልሆኑ የጥቅል ደመወዛቸው አንድ ሶስተኛ እየቀነሰ ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው ገቢ የማድረግ፣
4. ገንዘብ በመክፈልም ሆነ አገልግሎት በመስጠት እዳቸውን ከፍለው ያጠናቀቁ ተጠቃሚዎችን ዝርዝር ክፍያው በተጠናቀቀበት ወር ለሚኒስቴሩ ወይም ለሚወክለው የማሳወቅ፣
5. አገልግሎት በመስጠት እንደሚከፍሉ ተገልጾ የተመደቡለትን ተጠቃሚዎች ተገቢውን ክትትል በማድረግ ማሰራትና አገልግሎት ካቋረጡ ሙሉ ለሙሉ ማቋረጣቸውን በማረጋገጥ ወዲያውኑ ለሚኒስቴሩ፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ለመደባቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

17 Oct, 13:04


የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ ስምምነት የማይፈቃድባቸው ሁኔታዎች:-

- በታክስ ማስታወቂያ(በራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያ) ማቅረቢያ ጊዜ መከፈል ያለበት የታክስ ዕዳ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ወይም ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ተቀንሶ ገቢ መደረግ ያለበት ሲሆን፣
  - ታክስ ከፋዩ አስቀድሞ የክፍያ ጊዜ ስምምነት የተሰጠው ሆኖ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ሳይኖር ዕዳዉን ያልከፈለ ሆኖ ሲገኝ፣
   - የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የተጠየቀበት የታክስ ዕዳ መጠን እንደ ታክስ ከፋዩ አመዳደብ ከተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በታች ከሆነ፣
   ታክስ ከፋዩ፡-
  ለዕዳው ማስከፈያ ሃብቱ እንዲያዝ የዕግድ ትዕዛዝ የተላለፈበት ከሆነ፣
  በዕዳው የተያዘበትን ንብረት ለመሸጥ የጨረታ ማስታወቂያ የወጣበት ከሆነ፣ የክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ የሚሰጠው ለዕዳው ተመጣጣኝ የሆነ የባንክ ወይም የንብረት ዋስትና ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል፡፡

M.O.R. Medium Tax Payers No 1 Branch Office

17 Oct, 12:16


ምዕራፍ ሁለት ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ጥቅምት 07/2017 ዓ.ም

በገቢዎች ሚኒስቴር በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር አንድ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በክፍል ሁለት ለሁለተኛ ዙር የምጁላር ሥልጠና ተከታታዮች የሚሰጠው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

ሥልጠናው ቀጥተኛ ባልሆኑ ታክሶች ማለትም Turn Over Tax(የሽያጭ ታክስ)፣ የቴምብር ቀረጥ እና ሱር ታክስ ዙሪያ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ በሆኑት አቶ ታምራት ጅግሳ ተሰጥቷል::

3,892

subscribers

1,977

photos

4

videos