ወሎ ቤተ- አምሃራ
የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው ተጋድሎ
በአርበኛ ፋኖ ጌታሁን ሲሳይ የሚመራው አሳምነው ክፍለጦር ወልድያ ዙሪያ እያደረገ ያለው ተጋድሎ የቀጠለ ሲሆን ባህር ዳር መውጫ አፍሪኬር አካባቢ ጠላት ኬላ የሚያደርግበት ቦታ ላይ ደፈጣ በማድረግ የተለመደዉን ክንዳቸዉን አቅምሰዉታል::
በጥቃቱ ጠላት አምስት ሙትና ስድስት ቁስለኛ ያነሳ ሲሆን በወልድያና በሳንቃ በኩል ሁለት ዙ23 በማምጣት በዘፈቀደ እየተኮሰ ሲሆን ቃሊም መግቢያ አቦ ቤተ-ክርቲያን አካባቢ ሁለት እናቶችን በከባድ ሁኔታ አቁስሎ የነበረ ሲሆን አንደኛዋ እናታችን አርፋለች::
አሁን ላይ ወደመጣበት የሸሸ ሲሆን ወልድያ ከተማ ተረጋግቶ መቀመጥና ስራ መስራት ስላልቻለ ራያ አላማጣ ያስቀመጠዉን ተጠባባቂ ቀይ ቆብ ለባሽ ፈርጣጭ ሰራዊቱን ዛሬ ያስገባ መሆኑን አረጋግጠናል:: ተጋድሎዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ምንጭ፦ የአማራ ፋኖ በወሎ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
###
መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
የቴሌግራም 👉https://t.me/MerebMedia24
ፌስቡክ👉https://www.facebook.com/profile.php?id=61564373210803