መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

@menfesawigetmoch


ለሀሳብ ለአስትያየት >>>> @Tazena291

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

30 Aug, 16:42


https://t.me/AbaGebrekida

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

30 Aug, 16:25


ተአምር ምንድነው?
+++
ፅድቃችሁ የታለ
ተአምር የታለ
እኛስ ሙሴ……
በበትሩ ባህር ከፍሎልናል
ድንጋይ ተሸክመን በመሀሉ አልፈናል
ደመና ከልሎን ከነዓንን ወርሰናል
ከሰማይ ላይ መና ወርዶልን በልተናል
ከራፍዲም አለት ውሀ ጠጥተናል

አንተ አይሁዳዊ
ተአምር ምንድን ነው ትለኝ እንደ ሆነ
የትኛው ይደንቃል ትለኝ እንደሆነ
በል እንግዲህ ስማ እኔም አለኝ ድንቅ
እጅግ የሚጎላ እጅግ የሚረቅ
:
በሙሴ በትር ባህር መከፈሉ
ድንጋይ ተሸክሞ ማለፍ በመሀሉ
እርግጥ ነው ይደንቃል
ይሄ ግን ይጎላል ይሄ ግን ይረቃል
በመስቀሉ በትር ማለፍ ከሞት እሳት
በደሙ ማህተም ወደ ርስትህ መግባት

አንተ አይሁዳዊ
ፅድቃችሁ ወዴት ነው ትለኝ እንደሆነ
ተአምሩ የታለ ትለኝ እንደሆነ 
በል እንግዲህ ስማ
በህቱም ድንግልና አምላክን መፀነስ
የቃል ሰጋ በመሆን የአለም መፈውስ
በእናቱ ደመና ከልሎን መሻገር
የእዳ ፅህፈት ቀዶ ሲኦልን መበርበር
:
አንተ አይሁዳዊ….
ከነዓን ስትሻገር ፀሀይ ከከለለህ ከሰማይ ደመና
ታምሬ ማርያም ነች
ያቺ መሶበወርቅ በውስጧ ያለባት የህይወቴ መና
ሙሴ ከከፈለው የኤርትራ ባህር
እኔን የሚደንቀኝ
በመስቀሉ በትር ገሀነምን ማለፍ ሲዖልን መሻገር
ሰዎች ከገነቡት ከኢያሪኮ መፍረስ
እኔን ይደንቀኛል
በመስቀሉ ጉልበት የእዳ ደብዳቤዬ የሀጢያቴ መደምሰስ
አንተን ከሚደንቅህ ከበረሀው መና
እኔስ የሚገርመኝ
አምላክን መወለዷ በህቱም ድንግልና
:
ተአምርስ በለኝ የክርስቶስ መስቀል
ሞትን ለዘላለም ከሰንኮፉ ሚነቅል
:
ተአምርስ በለኝ
ምጥ ሳይሰማት ወለዳ ድንግል እናት ሆነች
ያለዘር ፀንሳ አምላክን ታቀፈች
 ይቀጥላል...
+++
"ተአምር ምንድነው"
ሀይማኖተ አበው
 ዘ ቅዱስ ኤራቅሊስ 
ም፵፱-ቁጥር ፵፭ 
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን እንዳስተማሩት
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

13 Aug, 19:27


ቀን....
አንዳንድ ቀን አለ፥ ሚያልፍ ማይመስል፤
ልብን 'ሚሰብር፥ተስፋን የሚያቆስል።
የእድሜ መጨረሻ፥ የሞት ቀን የሚያስመኝ፤
"ብንሄድ ይሻለናል"፥ በቅቶኛል የሚያሰኝ።

የቀን ክፉ አለ፥ ከአዙሪት የባሰ፤
ከመከራ ሚዘፍቅ፥ እየመላለሰ።
ዘላለም 'ሚመስል፥ አለ አስጨናቂ ቀን፤
አመትም ወራትም፥  ይዞ የማይለቀን።

ሲጨንቀው ሲጠበው፥ ሲጠፋው መድረሻ፤
መጠጊያ ሲያጣለት፥ ለሀዘኑ መርሻ።
ዛሬ ምን ልሆን ነው? ነገ ምን ይመጣል?
በጭንቀት ተዘፍቆ፥በሀሳብ ይሰምጣል።
መከራ ሲከበው፥ መልሶ መልሶ፤
ሀዘን ይቀመጣል፥ ሰው በራሱ ለቅሶ።

የሀጢያት ተራራ፥ ከቤቱ ቢያርቅህ፤
ዛሬ ቁራሽ ባይኖር፥ ባይሞላ መሶብህ።
የሰው እጅ ማየት፥ ሲያሳቅቅ ሲያደክምህ፤
እንደዚህ ሲሰማህ፥ አይሸበር ልብህ።

በሰው እጅ ከምትወድቅ፤
በእግዚአብሄር እጅ ውደቅ።
ከአምላክ አትጣላ፥ ከአምላክ አትኳረፍ፤
የማታውቀውን ቀን፥ ያውቃል ብለህ እለፍ፤

የተተወን የተረሳውን ሰው፥እግዚአብሔር ሲያስታውሰው፤
የተናቀን የተጣለውን ሰው፥እግዚአብሔር ሲያነሳው።
ወደ ቤትህ ስትመጣ፥የጠፋው ልጁ ስትገኝ፤
የሰው ፊት አይገርፍህም ፥ፍርፋሪም አትመኝ።
ከአባትህ ቤት ስትገባ፥ከአምላክ ስትታረቅ፤
የሰው ፊት አይፈጅህም፥ፀሀይህ መቼም አይጠልቅ።

አባታችን ሆይ፥
የምትኖር በሰማይ።
አትተወን እንጂ አንተ፥ የሰውስ አይደንቀንም፤
ያንተ ፀሀይ አትጥለቅ፥ የሰው እሳት አይሞቀንም።

ቀን ለጨለመበት፥ የደግ ቀን አንተ ስጥ፤
በወዳጄ ልብ ላይ፥ ፍቅርን ብቻ አስቀምጥ።
++++++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
  t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

08 Aug, 09:42


https://youtu.be/BoOoyRS8BT8?si=wBklB93AnZM_fzY6

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

15 Jul, 07:27


https://youtu.be/AWQj5SPgg8k?si=fm3AaFB0Opu4INyb

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

06 Jul, 16:07


ደሀውን መኖሪያ አትከልክል፤
የተራበን ቸል እንዳትል።
ያዘነ ከቶ አይደንግጥ፤
ለጠየቀህ ያለህን ስጥ።
ለተራበ ለተጠማ፤
እዘንለት ልብህ ይድማ።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

02 Jul, 02:47


መርቆርዮስ/ፒሉፓዴር/

ፒሉፓዴር ና መርቆርዮስ፣
ከበሮ ስንመታ ድረስ በፈረስ 
መርቆርዮስ የአብ ወዳጅ ነህ
ሰማዕት ሆነሀል ጣዖትን ሰብረህ

በብረት አልጋ በቆዳ ጅራፍ፤
ደምህ ቢነጥብ ጀርባህ ሲገረፍ።
የነደደ እሳት አንተን ሊያጠፋ፤
የሚጠብሱበት በደምህ ጠፋ።

የአብ ወዳጁ ሙያህ ወታደር፤
ለአምላክህ ፍቅር የሌለህ ወደር።
ስልጣኑ ክብሩ ይቅርብኝ ብለህ፤
ተቀላህ በሰይፍ ትጥቅህን ፈተህ፥

የንጉስ ክብር ርስቱ ጉልቱ፤
ሳያታልልክ ክብር ሹመቱ።
አልሰግድም አልከው ዳኬዎስን፤
በደም ታመንከው አምላክህን።

ውጊያ ቢሰለፍ ጠላት ሰይፍ መዞ፤
ድል አደረገ አምላኩን ይዞ።
የተዋጋውን ድል አድርጎታል፤
ገጸ ከለባት ታዘውለታል።

ስዕልህ ይዝለል ከበሮ እንምታ፤
በፈተና አጽናው ወጣት ይበርታ።
መርቆርዮስ ሆይ በፈረስ ናና፤
ወጣቱን ጠብቅ ወጣት ነህና።
++++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

03 May, 06:32


+++++++++++++++++++
ነፍሱን ሰጠ…
የአለምን ንጉስ ፣የፍጥረትን ጌታ፤
የኋሊት አሰሩት፣ ፊቱ እየተመታ፡፡
ህጋቸው ጨክኖ፣ አይሁድ በምክራቸው፤
የሚሰቀል መግረፍ፣ ባይፈቅድም ህጋቸው፡፡
አምላካችንን ግን፣ ፍርድ እያጓደሉ፤
በጅራፍ ገረፉት፣ ለአርባ እያጎደሉ፡፡
በዙ እንደበደለ፣ እንደ ጢያተኛ ሰው፤
ተቆጠረ አጥንቱ፣ ስጋውን ጨርሰው ፡፡

የአዳምን ሞት ሊወስድ፣ መከራን ታገሰ፤
ለሚጠይቁትም፣ አንዳች አልመለሰ፤
ወድቆ እየተነሳ፣ አይኑ እያለቀሰ፤
ደም ግባት አሳጡት፣ ደሙ እየፈሰሰ፡
አይን የሚፈጥረውን፣ በምራቁ አቡክቶ፤
ጉንጮቹ ተፀፉ፣ በፊቱ ተተፍቶ፡፡
የዘመንን ደዌ፣ በቃል የሚፈታ፤
በመጻጉዕ እጆች፣ በጥፊ ተመታ፡፡
አንዳች በደል እንኳ፣ የሌለውን ንጉስ፤
በፍርድ አደባባይ፣ አቆሙት በመክሰስ፡፡
ጲላጦስ ሆይ ፍረድ፣ በርባንን ፍታልን፤
ወንበዴውን ለቀህ፣ ጌታን ስቀልልን፡፡
በሚፈርደው አምላክ፣ ፍርድ እያስፈረዱ፤
መስቀል አሸክመው፣ ሊሰቅሉት ወሰዱ፡፡
የራስ ቅል በሚባል፣ ጎልጎታ ሰቀሉት፤
በሰፍነጉ ሞልተው፣ ሀሞትን አጠጡት፡፡

ከመስቀሉ በታች፣ ሲዘብቱ አይቷቸው፤
የሚያደርጉትንም፣ አያውቁም አላቸው፤
አባት ሆይ ስለዚህ፣ ይቅርም በላቸው፡፡
የአዳምን የሞት ሞት፣ በህይወት የለወጠ፤
በገዛ ስለጣኑ ጌታ፣ ነፍሱን ሰጠ፡፡
+++++++++++++++++++
" ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ።
ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 19:30)
©ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

28 Apr, 02:31


++++++++++++++++++++
ሆሣዕና....
ወደ ኢየሩሳሌም፥ ቤተ ፋጌ ሲደርስ፤
የታሰረች አህያ፥
ፈተው እንዲያመጡ፥ ላካቸው ክርስቶስ።
እነዚህ ለጌታ፥ ያስፈልጋሉና፤
የታሰረችውን፥ አምጡልኝ ፍቱና።
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ላሳየሽ በጎነት ላሳየሽ ትህትና፤
እልል በይ ዘምሪ፥ እያልሽ ሆሣዕና።

አዳኝና ትሁት፥ ፃድቅ ንጉስሽ፤
በውርንጫ ጀርባ፥ መቷል አዳኝሽ።
ዘንባባ አንጥፉ፥ ህፃናትም ውጡ፤
አሁን አድን በሉት፥ ምስጋናችሁን ስጡ።
ሆሣዕና....
ደግሞም በዚያችው ቀን፥ ከመቅደስ ገባና፤
የሻጮችን ዙፋን፥ ገለበጠውና።
የወንበዴዎች ዋሻ፥ ያረጉትን ቤቱን፤
ርግብ ሻጩን ሰዶ፥ አፀዳ መቅደሱን።
የገንዘብ ለዋጩን፥ ወንበር ገለበጠ፤
በመቅደሱ ዙፋን፥ ጌታ ተቀመጠ።

ከሚጠቡትም አፍ፥ ምስጋና አዘጋጀ፤
አምላክነቱንም፥ ለአለም አወጀ።
የምትቀድሙ የምትከተሉ፥ ሆሣዕና እያላችሁ፤
በአርያም ይሰማ፥ መዝሙር እልልታችሁ።

አቤቱ ጌታ ሆይ፥ አሁን አድን በሉት፤
ልብሳችሁን ዘርጉ፥ ዘምባባ አንጥፉለት።
አሁን አድን ብለን፥ ወተናል በመንፈስ፤
በውርንጫ ጀርባ፥ አምላካችን ሲደርስ።
የዘካርያስ ትንቢት፥ አልቀረም ተፈቷል፤
በውርንጫ ጀርባ ፥ንጉሳችን መቷል።
+++++++++++++++++++++
@Menfesawigetmoch
©ታዜና
" የሚቀድሙትም የሚከተሉትም። ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤"
(የማርቆስ ወንጌል 11:9)

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

28 Apr, 02:29


https://youtu.be/rQduW-pY3H0?si=Gll3fj7GQ1VKHnFL

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

04 Mar, 15:41


ክንዴ አይዝልም ምርኩዜ ነህ
በምንኩስና ብርታቴ በእርጅናዬ ጉልበቴ ነህ
መከራ መስቀልህ ምልክቴ ሆኖልኛል
ድካሜን ስትደክምልኝ ቀራንዮን ያሳየኛል
+++©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

29 Feb, 08:54


በማንም ላይ ከቶ አትፍረድ፥
የማይመጥንህ ቦታ አትውረድ።
ልብህ በሰው አይነሳሳ፥
እጅ እንዳትሰጥ እጅ ንሳ።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

24 Feb, 07:04


፲፮ ኪዳነ ምህረት ፲፮

ያከበረሽ ሊከብር ፥ኪዳን አለሽና፤
አይቆምም ለስምሽ፥ እልልታ ምስጋና።
የጠሩሽ ቢበዙ፥ አንቺ ባርከሻቸው፤
የወደዱሽ ሁሉ፥ ቀና መንገዳቸው።

፲፮ ፲፮ ፲፮

ልጆችሽ ስለሆን፥ እናቴ እንላለን፤
እስከ ዘለአለም፥ ገና እንወድሻለን።
ከወዴት ይገኛል፥ እንዳንቺ ያለ እናት፤
ዘውትር እንላለን፥ ኪዳነ ምህረት።

፲፮ ፲፮ ፲፮

ከአምላክ መታረቂያ፥ የምህረት ኪዳን ነሽ፤
እንኳን ለወደደሽ፥ ለጠላሽ እናት ነሽ።
"ኪዳነምህረት፥ ኪዳንኪ ኮነ፤
በልጅሽ ቤዛነት፥ ፍጥረት ሁሉ ዳነ።"
+++++++++++++++++++++++
#መንፈሳዊ_ግጥሞች ©ታዜና
@Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

22 Feb, 09:05


"ይህችን ዓመት ተወኝ!"

ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ
ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም
የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ
የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!

አውቃለሁ ታውቃለህ - ቀጠሮን ሰጥቼ - እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ - ብዙ ጊዜ ዝቼ - በወሬ እንደምቀር
‹ዘንድሮስ…!› እንዳልኩኝ - አምና ይሄን ጊዜ - ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ - ‹ዘንድሮዬ› አልፎ - በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ - እኔን በመኮትኮት - እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ - ዛሬም አልበቃኝም - በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውኃ - በድንጋይ ልጅህ ላይ - ሳትታክት ስታፈስስ -
ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ - ሕይወቴን ሳይለውጥ - እንዲያው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ - እያገሳሁት ነው - ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን - አልያዝህ አለኝ - ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ - ከቅዱስ መጽሐፍህ - ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ - አንድ ጥቅስ አጣሁኝ - በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ - ትምህርት የማይሠርጸኝ - ተማሪ ብሆንም
ይህችን ዓመት ተወኝ - ደግሞ ትንሽ ልማር - ታገሠኝ አሁንም!

እባክህ አልቆረጥ - በቅዱስ መሬትህ - ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን - የፍሬያቸው ሽታ - መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ - ዛሬም ተሸከመኝ - አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሠኛል - ጠላት እየሆንኩት - አይሠሩ ስሠራ!
አታውጣኝ ከቤትህ - ብዙ ቦታ አልይዝም - ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ - ቤት የማላጣብብ - ፍሬ አልባ በለስ ነኝ!
ቦታስ የሚይዙት - ባለ ምግባሮቹ - ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ - የተንዠረገገ - ተጋድሎ ጽድቃቸው!
ከሊባኖስ ዝግባ - እጅጉን የበዛ - ገድል ትሩፋታቸው!
እኔ አይደለሁም - ቦታስ የምትይዘው - የአንተው እናት ናት
ሥሮቿ በምድር - ጫፎቿ በሰማይ - ሲደርሱ ያየናት
ይሀችን ዓመት ተወኝ - ከሥርዋ እሆናለሁ - ባፈራ ምናልባት!..
ይህችን ዓመት ተወኝ - እባክህ አምላኬ - አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺህ ዓመት አንድ ቀን - አይደለም ወይ ለአንተ - ዓመት ኢምንት ናት!
ይሄ ዓመት አልፎ - ዳግም ‹ዓመት ሥጠኝ› - እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ - ይህችን ዓመት ተወኝ - የወጉን እንዳደርስ!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

---

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

20 Feb, 18:38


እንደ ኒቆዲሞስ በለሊት ባልመጣም
አረጀሁኝ ብዬ ከቤትህ አልወጣም
አሸበሽባለሁ ስለ በጎ እድሌ
ሰንበት ተማሪ ነኝ ያውም ሽማግሌ
+++
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

20 Feb, 12:33


እንደ ኒቆዲሞስ በሌሊት ባልመጣም

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

17 Feb, 14:09


ደሀውን መኖሪያ አትከልክል፤
የተራበን ቸል እንዳትል።
ያዘነ ከቶ አይደንግጥ፤
ለጠየቀህ ያለህን ስጥ።
ለተራበ ለተጠማ፤
እዘንለት ልብህ ይድማ።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

15 Feb, 11:58


ጎልያድን ብጥል፥ ባንተ ክንድ ወርውሬ፤
ሲሳራን ብመታ፥ ባንተ ቀስት ወጥሬ።
ከኔ አንዳች አልሆነም፥ የሆነው ካንተ ነው፤
ታግሎ የሚጥልልኝ፥ ስምህ ጉልበቴ ነው።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

06 Feb, 11:35


ኢታምልክ ከኔ ሌላ፤
ኢትቅትል ነፍስ አትብላ።
ኢትዘሙ በአይንህ ጭምር፥
ኢትምሐል በስመ አምላክ፤
አትጥራ በከንቱ  ስሙን በሰርክ።
ተዘከር ዕለተ ሰንበት፤
ኢትስርቅ የሰው ንብረት፤
አትመስክር በሀሰት።
አክብር እናት አባትህን፥
እንደራስ ውደድ ባልእንጀራህን፥
ሚስቱን አትመኝ የወዳጅህን።

አይምሮ ጠባይን ፥በልቤ ያኖርከው፤
በምግባር እንድኖር፥ዘመኔንም ባርከው።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   t.me/Menfesawigetmoch

10,600

subscribers

115

photos

2

videos