• በአደባባይ ምላሽ ሰጥውበታል፤
• ደጋፊም፣ ተቃዋሚም ቀርቦ የልቡን ተናግሮበታል፡፡
እኔም ይህን እንደ ዕድል በመቁጠር የእግዚአብሔር የሆነውን ስራ በትህትና ለመግለጥ ጥረት አድርጌያለሁ፤ በሙገቱ መካከል በርካቶችን ምላሽ በመስጠት ለእውነቱ እንዲቆሙ እና አንዲተባበሩ ጠብቄያቸዋለሁ፤በተለይም፡-
• ዳግም የተወለደ ክርስትያን የዘላለም ዋስትና አለው፤
• ሰው ዳግም ከተወለድ አይጠፋም፤
• ONCE SAVED ALWAYS SAVE፤
የሚሉት በኢትዮጵያ ያሉ ባፕትሲቶች፡-
• ወይ አላነበቡትም ወይም
• እንዳለዬ አይተው ትተዋል፤
• አልያም እምነታቸው በአሉታዊ (በአፍራሽ) ትርክት ተሞልቶ ከሜዳው ውጭ ሆነው ጉስቁልናን ያስከተለ ምድራዊ ሕይወታቸውን እየመሩ ይሆናል፤
• ወይም በመንታ መንገድ ላይ ራሳቸውን አግኝተው እያነከሱይሁን አይሁን ባለውቅም ከ ከመኮንን ታደሰ እና ከዚክ ኑሩ በቀር ማንም መልስ አልሰጠም፡፡እርግጥ ታምሬ ፈቃዱ ‹‹መጥፋትን ያመላክታሉ ለተባሉት ክፍል ምንባቦች ግሩም ምላሽ ለማቀበል ዝግጅቱን በወጉ እያጠናቀቀ እንደሆነ ነግሮኛል፡፡
ወገኖቼ ከሶስት ቀናት በኋላ 2017 የምህረት አመትን እንቀበላለን፡፡በሚሰጡን 365 ቀናት መካከል፡-
• አገርን ሊያጎሳቅሉ የሚችሉትን፣
• ሕብረታችንን ሊያደፈርሱ የሚችሉትን፣
• ለግድያ ለመጠፋፋት ምክንያት በሆኑት አፍራሽ ትርክቶች ላይ ለመስራት ምን ያህል ዝግጁ ነን፡፡
• ታዲያ ራሳችሁንስ በአሉታዊ ተፅዕኖ አድራሽ ትርክቶች ተፅኖ ስር መሆን አለመሆናችሁን እንዴት አያችሁት?
--ይልቅኑ፡-
• ክርስትናችሁን በሚመለከት፣
• የክርሰቶስ መሆናቸሁን በሚመለከት፣
• መሰረታዊ የምትሉዋቸውን የአስተምህሮ ዘውግ በተመለከተ
• በጥቅሉ ቅዱስ ቃሉን በሚመለከት
• ልትኖሩ የወሰናችሁበት የእምነት አካሄድ በረከትን ወይስ መርግምን በሚያመጣው የኑሮ ዘይቤ ውስጥ አላችሁ?
‹‹…15 መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ፤ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።… እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም።
27 በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ፤ እኔም አውቃቸዋለሁ፤ ይከተሉኝማል፤
28 እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
30 እኔና አብ አንድ ነን።(ዮሐንስ 10:15,26-30)
እንግዲህ ዳግም የተወለደ ሰው የተሰጠው የዘላለም ሕይወት የተጠበቀ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ በመሆን ራሱን የሚያኖር አማኝ ከማህበሩ በመለየት ስሙን ሊፍቅ ይገባል፤ እኒህ አይነት ሰዎች ከመነሻውም ክርስትን የሆኑ መስሏቸው የገቡ እንጂ ከጌታ የተወለዱ አይልነበሩም፤ ቁጥር 15 እኒህን አይነት ሰዎች በጎች እንዳልሆኑ ደምፁንም መለየትም ሆነ መስማት እንደማይችሉ ‹‹… እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም።››በማለቱ ልንደመም ይገባል፡፡
ማጠቃልያ
ሊታወሱ የተገባቸው ሁነኛ ነጥቦች፡-
የሀሰተኛ ትርክቶች መለያ
• ከላቀው ጌታ ጋር ተካክሎ ተመሳስሎ ለመቆም ይጥራል፤
• በልዑል እግዚአብሔር ብቻ የሚከናወኑትን በራሱ በመፈፀም ሌላ አቻ ልዩ አግዚአብሔርን በሰው ውስጥ ለመፍጠር ይጥራል፡፡
• የሰውን ፍጥር መሆን እና በእንከን ውስጥ ያለ መሆኑን አስረስቶ አቅመኛ አድርጎ ያሳየዋል፡፡
• የኢየሱስን የትንሳኤውን ሐይል በእርሱ መንፈሰ ሙትነት ላይ ትንሳኤን በዳግም ልደት አማካኝነት ሊመጣ እንደሚችል አያምንም፡፡
• የእምነቱን እና የምግባሩን የመጨረሻ ባለስልጣን ቃሉ ነው ያለለትን በተግባር(በኑሮው) ይክዳል፡፡
• በሐጢያት የረከሰ ስብዕና ራስን በገዛ አቅም ሕያው ማድረግ አለማስቻሉን ለመረዳት ብርሀን ሰጪ ለሆነው ለመንፈስ ቅዱስ ራሱን አይሰጥም፡፡