HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

@hailegebriel2021


❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️

👇👇👇
http://www.youtube.com/@haileG2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

22 Oct, 12:55


«ሰዎች የምንናገረውን በማዳመጥ ይወዱናል፤ የምናስበውን ግን አያውቁም፡ ቢያውቁ ይጠሉን ነበር። አውቆ የወደደን ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው። (የዕለቱ መና)
«ሁል ጊዜም በዚህ ዓለም ሕይወትህ ያለ ዛሬ በስተቀር ሌላ ቀን እንደሌለ አስብ እንዲህ ብታደርግ ኃጢአትን አትሠራም።» (የዕለቱ መና)
«እግዚአብሔርን በመከራህም በተድላህም ሁልጊዜም አስበው መከራ በደረሰብህ ጊዜ ያስብህ ዘንድ።» (ማር ይስሐቅ)
«በሰው ስህተት ውስጥ ለመደበቅና እፎይታ ለማግኘት አትሞክር። በእርሱና ባንተ መካከል ያለው ልዩነት እርሱ መናገሩ አንተ ዝም ማለትህ ወይም አንተ ድራማውን ችለህ በድብቅ ማድረግህ ነው።»

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

22 Oct, 11:11


የጸሎት መጽሐፍትን ከማንበባችን በፍት ይሄንን እናድርግ! || የጸሎት መጽሐፍትን ከመናፍስት ውጊያ አንጻር እንዴት እናንብብ? የጸሎት መጽሐፍትና አጋንንት 😱😭💥 https://youtu.be/CsLjBsOHY9Q

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

21 Oct, 11:45


«ትውልዱን የገደለ፣ ያደነዘዘ፤ ዕድሜውን የጨረሰ አደንዛዥ መጽሐፍት መስለው ትውልዱን ለመናፍስት በማለዳው የገበሩ መጽሐፍቶች እግዚአብሔር ይገስጸው በእውነት። እነዚህን መጽሐፍቶች ያነበባችሁ ወይም የሚያነብ ወዳጅ ካላችሁ መልዕክቱን አስተላልፉ። ንቁ በማለዳው በእውነት ጥበብና ዕውቀትን ይሰጣል ብለን ሳናውቀው ያነበብናቸው የፍልስፍና መጽሐፍቶች ኑሯችንን ሕይወታችንን ዕድሜያችንን በልቶብናልና እንንቃ።»

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

21 Oct, 10:52


"ኤናይም" = "የዓይን መክፈቻ በር"

ብዙ ዘመዶች፣ ወዳጆች እያሉን ብቸኛ የምንሆንበት ምክንያቱ፦

1ኛ፡ ባሕሪያችን ከሌላው ሰው ሰለማይገጥም
2ኛ፡ በመናፍስት እጅጉን ስለተጎዳን እንዲሁ ደግሞ ስላላወቅነው!
3ኛ፡ ብዙ የተጠጋነውና ያየነው ሰው ለራሳችን ጠላት ሆኖ ስላገኘነው፣ መቅረባችንን ተከትለው የመጡ ችግሮች፣ ጉዳትን ስላስከተሉብን ነው።

=> ወዳጆቼ በዚህም የተነሳ የብቸኝነት ልብስ ለብሰን እንኖራለን። አንዳንድ ጊዜ እንዲህ አይነቱ ጉዳይ በቤተሰብ ውስጥ ጎልቶ ይታያል፤ እየሆነም ይገኛል። ሚስት ከባል፣ ልጅ ከአባት ከእናት፣ ወንድም ከወንድም ወዘተ ብቻ ለብቻ ሆነው ኑሯቸውን ይመራሉ። ዕቅዳቸውን ለየብቻቸው ስለሚያዘጋጁና በምክክር ስለማያጠነክሩት፤ የአባት ችግር ወይም የሚስት አሊያም ደግሞ የልጅ ችግር፤ በጠቅላላው ለቤተሰቡ መጥፎ መዘዝ ሊያተርፍ የሚችል ይሆናል።

=> አስተውሉ! በአንድ ጣሪያ ሥር እስካሉ ድረስ አየንዱ ችግር ሁሉንም ይነካል ማለት ነው። በዚህም መካከል የመንፈስ ውጊያ ሲታከልበት፤ አደጋው የከፋ ይሆናል። ትዕማር ሁለት ባሎቿ ከሞቱ በኋላ፤ በውሸት አገር (በከዚብ) የተወለደውን ሶስተኛውን የይሁዳ ልጅ ሴሎምን ለማግባት እየጠበቀች ነበር። ይሁን እንጂ፣ የውሸት አገር ልጅ ዘሯ ወይም ባሏ ሊሆን አይችልም። እኛም ቢንሆን ከሰማያዊ ተስፋዎቻችን ወጥተን እግዚአብሔር ከሰጠን ሃይማኖት መንፈሳዊ በረከት ርቀን ያተረፍነው ኑሮና ቁልቁል እየወረድን ያፈራናቸውን ልጆች ምን እንደገጠማቸው እናውቃለን።

=> ዛሬ ለብዙዎቻችን ውሸት የዕለት እንጀራችን ሆኗል። ሐሜትና ተንኮል ከውሸት ጋር ተደባልቀው ካልተገኙ ወዳጅ ማፍራት አልተቻለም። ምክንያቱም ውሸታሙ የሚፈልገው የራሱን ቢጤ ውሸታም ነው። ትዕማር የብቸኝነት ካባዋን ብታወልቅም ከውሸት አገር ሰው ጋር ግን ሕይወት አይኖራትም። (ከዚብ ማለት የውሸት ሀገር ማለት ነው) ይሁዳ በስደተኞችና በውሸት አገር ከኖረና በዚያም ልጆች ወልዶ ካጣ ከአምሳ አንድ ዓመት በኋላ ወ ደተምና ወጣ። በፍት ግን ዘፍ.38፡1 ላይ እንደተጠቀሰው ይሁዳ "ወረደ" ነበር የሚለው። ወደ ተምና ለሜድ ደግሞ የሚያልፈው "በኤናይም" በኩል ነው። ሌላ መተላለፊያ መንገድ የለም። "ኤናይም" ማለት "የዓይን መክፈቻ በር" ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ የቁልቁሊትን ዓይነጥላ ማስወገጃ በር ማለት ነው።

=> ትዕማር በረከቷን የምትጀምረው በኤናይም ደጅ ላይ ነው። ዓይኗ የሚገለጠው ኤናይም ላይ ነው። ይሁዳም ሥጋዊ ልምምዶቹ የሚቀሩበት የወደፊቱ የተስፋው ጎዳና ምን ሊመስል እንደሚችል የሚቀረጽበት ኤናይም ደጅ ላይ ነው። የይሁዳ የተስፋው ራዕይ ከአምሳ አንድ ዓመት በኋላ አንድ ብሎ የሚጀምርበትና ዳግም የሚያንሰራራበት የዓይን መክፈቻ (ኤናይም) በር ላይ ነው።

=> እስቲ እኛስ ዓይኖቻችንን በምን በምን ከፍተናል? እናቶቻችን ቡና ካልጠጡ ዓይናቸው አይከፈትም። ዛሬ ብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጫት ካልቃሙ፣ ቡና ካልጠጡ አይናቸው አይገለጥም። ዛሬ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር ትምህርታቸውን በደንብ ለመከታተልና ለማጥናት የግድ የጫትና ሌሎች የማነቃቂያ ዕጾች እርዳታና እገዛ አስፈልጓል። አእምሮአችን በሱስ ጥገኛ መንፈስ ውስጥ ከገባ ዘመናት አልፏል ነገር ግን አሁንም ብዙዎቻችን አልነቃንም መንቃትም አንፈልግም።

=> ይህች ቅድስት ቤተክርስቲያን ለብዙ አገልጋዮችና ክርስቲያኖች የዓይናቸው መክፈቻ ሆና ሳለ፣ ውለታዋን በልዩነት መለወጣችንን ቆም ብለን እንደ ትውልድ ልንገነዘበው አልቻልንም። ኤናይም የመውጫው መንገድ እንጂ፤ የመውረጃው አይደለም። አዶሎም የመውረጃው፡ የመሰደጃው፡ ክፉ ልጆች የመውለጃውና ሞተው የመቀበሪያ መንገድ ነበር። ከአዶሎም በታች ያለው ደግሞ ከዚብ ወይም የውሸት አገር ነው። በዚያም እርግማን አለ!

=> በመጨረሻም የእግዚአብሔር ሕዝብ በተሰደደ ቁጥር ውሸት ውስጥ ነው የሚደበቀው። እንዴ ከወረድክ ደግሞ እየባሰብህና ትውልዱም እየዘቀጠ ይመጣል። ይህንን ከልብህ ውስጥ ፈልገው። ይቆየን!

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

21 Oct, 07:55


"መሲሕ (יֵשׁוּעַ) ላይ ሁሉም ተባበሩ!"

=> ከፊቱ የሚቆሙት ሁሉ በራሳቸው ላይ እየፈረዱ እውነትን ብቻ የሚናገሩበት አስፈሪ ጉባኤ ያለው ታማኝ ዳኛ፤ በካህናትና በመኳንንት የሐሰት ክስ ሕዝብ አደባባይ ቆሞ ከጲላጦስ ደጅ ብያኔን ሊቀበል ተሰየመ። አስተዳዳሪው ጲላጦስም በክርስቶስ የታሪክ መዝገብ ላይ ምንም አይነት ስሕተት ስላላገኘ፤ "ይህ ሰው ንጹሕ ነው፥ እነሆስ ለሞት የሚዳርገውን አላጠፋምና [እንዳይከፋችሁ ሲባል] ቀጥቼ እፈታዋለሁ" ሲል ፍርዱን ሰጠ፡፡ ነገር ግን ሁሉም በአንድነት የተላለፈው ውሳኔ ፍላጎታቸውን የሚጋፋ እንደሆነ በማሳወቅ፤ ይልቅስ ይህን ሰው[ሎቱ ስብሐት] አሰወግዶ፥ በርባንን እንዲፈታላቸው ወደ ገዢው ጮኹ፡፡

=> ከተወለደባት ቅጽበተ ቤተልሔም አንስቶ እስከ ተሰቀለባት ጎለጎታ አንዳችም የበደል ሽራፊ ያልፈጸመ ቅዱስ ክርስቶስ ላይ ሁሉም አደሙ፡፡ ኃጢአት ከዋጣቸው፣ ሰው ከረሳቸው፣ ሐብት ከከዳቸው፣ ደዌ ከያዛቸው፣ ግራ ከገባቸው፣ መሄጃ ከሌላቸው፣ ዘመን ከጣላቸው፣ ሞት ከገደላቸው ሚስኪኖች ጋር ከመዋል ውጪ አንዳች ሲሠራ ያልተገኘው መሲሕ ላይ ሁሉም ተባበሩ፡፡ "ሁሉም ደግመው። በርባንን እንጂ ይህን አይደለም እያሉ ጮኹ። በርባን ግን ወንበዴ ነበረ።" (የዮሐንስ ወንጌል 18፥40)

=> በኢየሱስ የሸንጎ አደባባይ የታየው በአንድነት ወንበዴን የመደገፍ ጩኸት፤ ከውስጥ በኩል ያለ የክፉ መናፍስቶች ደጉን የማፍረስ መናበብ ምሳሌ ነው፡፡ አስታውሱ! ጌታ ለሚጮኹበት ካህናትና አይሁዳውያን አስቀድሞ እንዲህ ብሏቸው ነበረ፤ "እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ" (የዮሐንስ ወንጌል 8፥44) በነዚህ ሰዎች አድፍጦ ያለው የዲያቢሎስ መንፈስ፤ ዘር ሆኖ እየተወራረሰ አብሮ በመወለድ፤ እንደ አባት እየመራ ለክፋት አሳድጎ ለክፋት በማኖር፤ ምቹ ጊዜና ቦታን ባገኘበት ዕድል ላይ፤ መልካም ክርስቶስን ለማስወገድ በከሳሾቹ ሕሊና እጅ ለእጅ በመያያዝ፤ በአንድ ጫና የተገፋ የአንደበት ድምፅን በሁከት አሰማ፡፡

=> መናፍስት አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ባልተለየ ጽኑ ሃይማኖታዊ አኗኗር ሲመላለስ፤ ጥብቅ የቅድስና ሰንሰለት ከመለኮት ኃይል ጋር እንደሚኖረው ያውቃሉ፡፡ ስለሆነ ግለሰቡን በግል ፈተና በማሰናከል የጽደቅ ትስስሩን ለመቁረጥ ካልቻሉ፤ በሥጋ ዓለም ባለ የእርስ በእርስ መናበብ አንድ ሆኖ በመምጣት፤ የሰዎችን ብዙ ቁጥርነት ምሽግ ያደረገ መልካሙን አፍራሽ የተንኮል ተኩስ ይተኩሳሉ፡፡ ዲያቢሎስ ላይ ንቃተ ሕሊና አግኝታችሁ በተግባራዊ መረጃ በመታገዝ የእምነት ኃይል ላይ በመቆም፤ ብርቱ የዕለት አምልኮተ እግዚአብሔርን የጀመራችሁ ሰዎች በብዙ የምትቸገሩበት አንደኛው ጉዳይ፤ አስቀድሞ በጌታችን ላይ የደረሰው የክፉ መናፍስት መልካሙን ለመቃወም መናበብ የሚባለው ጉዳይ ነው፡፡

(በመልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ)

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

18 Oct, 11:12


ለሀብትና ለፍቅር የሚደገሙ ጸሎቶች! || ግራ የተጋባው ጥበበኛ ነኝ ባይ ደብተራ || ልማዳዊ ንግግሮችና የመናፍስቱ ሴራ || የመቃብሩ ቦታ መናፍስት መዋረሻ!! https://youtu.be/4WhkcvN_8ks

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

17 Oct, 14:33


ልጆች እንዲዋሹ፣ እንዲሰርቁ የሚያደርግ አብሮ የሚወለድ ክፉ መንፈስ || ምህረትን የሚያዘገዩ አብቶች በዘመናችን || አጋንንት የለብኝም ብሎ መደምደም!! 😱😭💥 https://youtu.be/t0zhgpR9gWg

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

16 Oct, 19:01


😭 እባክህን ጌታ ሆይ ኢትዮጵያ ሀገራችንና ሕዝቦቿን አስባት! እናቶች ለብሰው ደምቀው የሚማጸኑበት፣ የሚለምኑበት ነገር ግን ውስጣቸው የተጨነቀ፣ በረሃብ የጠወለገ ፍት፣ የተጠማ ጉሮሮ በእናቶችና አባቶች በሕጻናቱ ላይ ይሄንን ማየት በተለይም በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የተለመደ ሀገር ያወቀው ጉዳይ ሆኗል በእውነት። በጭንብል ፍታቸውን ሸፍነው ኑሮው መከራ ሆኖባቸው እንዳይታዩ ብለው ተደብቀው የሰዎችን ፍት የሚመለከቱና የሚለምኑ ወገኖችን ማየት እጅጉን ያሳዝናል። 😭

😭 በእውነት እንመለስ ወደ ቀልባችን! በየቀኑ የኑሮው ሁኔታ ትውልዱን እያደቀቀ፣ ራስ ምታት ሆኖበት 😭 አራስ እናት የወለደችውን መመገብና እራሷንም ጭምር መመገብ አቅቷት በየመንገዱ መንታ ልጆቿን ታቅፋ ይዛ የምትማጸን፣ የምለምኑ እናቶችን ማየት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የተለመደ ነገር ግን ማንም ትኩረት ያልሰጠው የገሀድ ሀቅ ነው። እግዚአብሔር በእውነት ይርዳን። እንተጋገዝ 🙏

😭 የምገርመው! አዲስ አበባ እንደ ሰሟ መሆን አቅቷት በየመንገዱ የተጨነቁ፣ ያዘኑ፣ የጠቆሩና የከፋቸውን እናቶችና አባቶችን ማየት በእጅጉን አንጄት ይበላል! እግዚአብሔር በእውነት ሁላችንንም ይርዳን። በተቻለን አቅም ሁላችንም እርስ በእርስ እንተጋገዝ። በያላችሁበት አከባቢ የተጨነቁ የተቸገሩ አባቶችን እናቶችን አባካችሁን አለሁ በሏቸው። ዛሬ በየመስሪያ ቤቱ በራፍ ብትሄዱ እንደ ቤተክርስቲያን የተማጽኖ እጆችን በብዛት ትመለከታላችሁ። ሁላችንም ምክንያቱ ምን እንደሆነ እናውቃለን። ሁላችንም ወደ ራሳችን እንመለስ፣ እውነትን እንያዝ። እውነትም ክርስቶስ ነው። 🙏

እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንን ሰላም ያድርግለን 🙏 ሞገሱን ይላክልን 🙏

ለማገዝ ፍቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር አናግሩኝ አስፈላጊውን መረጃ እሰጣችኋለሁ።

https://t.me/haile_gebriel_tube_bot

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

16 Oct, 11:29


አጋንንት ስደክሙና ስቀጠቀጡ የሚያሰሙት ድምጽ! || መንፈስ መጮሁ ምን ያደርጋል መሸኘቱ እንጂ! || ገንዘባችን የማይበረክተው ለዚህ ነው #ethiopia 😱😭🔥 https://youtu.be/LxR-P7WT1PU

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

16 Oct, 05:28


«ያሳዘነህን፣ ያቆሰለህን፣ የበደለህን ክፉ ያደረገብህን እንደ ሐኪምህ እንደ ፈዋሽህ አስታውሰው። ክርስቶስ እንዲፈውስህ ልኮታልና በቁጣ አስታውሰው።" (አባ ዞስማስ)»

«"እውነተኛና ብልህ ሰው አንድ ነገር ይፈልጋል ይኸውም ለእግዚአብሔር መታዘዝ ነው። በዚህች ዓለም እያለ ነፍሱን ሥርዓት ያሲዛል ስለ ሥጦታዎቹና ስለሚያጋጥመው ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል።" (አባ እንጦንስ)»

«"ዳርቻ ሳይርቅህ ካለንበት የምትጎበኘን፣ መጋረጃ ሳይከልልህ ኑሮአችንን የምታይልን፣ ቁልፍ ሳያሻህ የልባችንን ምሥጢር የምታውቅልን ጌታ እናመሰግንሃለን።"»

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

15 Oct, 13:39


"ከግልሙትና መውጣት ይቻላል!"

=> አባ ሰራፕዮን በአንድ የግብፃውያን መንደር መካከል ሲያልፍ አንዲት ጋለሞታ አየ። እርሱም "በዚህ ምሽት ጠብቂኝ፣ ሌሊቱን ካንቺ ጋር አሳልፋለሁ" ብሏት ሄደ። ጋለሞታዋም ራሷንም አልጋዋንም አዘጋጀች። ሲመሽ አባ ሰራፕዮን መጣና "አልጋውን አዘጋጀሽውን?" ሲል ጠየቃት። "አዎ አባ" ስትል መለሰች። በሩን ግጥም አድርጎ ከዘጋው በኋላ "ጥቂት ጠብቂኝ፣ በሕጋችን መሠረት ቀድመን መጸለይ አለብንና፣ መጀመሪያ ያንን ልፈጽም" አላት። ከዚያም ዳዊት መድገም ጀመረ። ከእያንዳንዱ መዝሙር በኋላ ለዚያች ሴት ይጸልይላት ነበር። ይህን ከመሰለው ሕይወት አውጥቶ እግዚአብሔር ነፍሷን ያድን ዘንድ አጥብቆ ለመነው። እግዚአብሔርም ሰማው። ያቺ ሴት እየተንቀጠቀጠች ከአባ ሰራፕዮን አጠገብ ቆመችና መጸለይ ጀመረች። መዝሙረ ዳዊትን ሲጨርስ ያቺ ሴት መሬት ላይ በግንባሯ ተደፋች። ከዚህ በኋላ ደግሞ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን መልእክታት ማንበብ ቀጠለ።

=> ጸሎቱን ሲፈጽም ያቺ ሴት ልቡናዋ በፀፀት ተመልቶ ይህ ታላቅ ሰው ወደ ርሷ የመጣው ነፍሷን ለማዳን እንጂ ኃጢአት ለመሥራት አለመኾኑን ተረዳች። ከዚያም እግሩ ሥር ተደፍታ "አባ እባክህን እግዚአብሔርን ላስደስተው ወደምችልበት ቦታ ውሰደኝ" አለችው። እርሱም ወደ ሴቶች ገዳም ወሰዳትና ለእመ ምኔቷ "ይህቺን እኅት ተቀበዪኝ፣ ነገር ግን ምንም ዓይነት ቀንበር አትጫኚባት። የፈለገችውንም ስጫት፣ እንደምትፈልገውም ትጓዝም ዘንድ ተያት" አላት። ከጥቂት ቀናት በኋላ ያቺ ሴት "እኔ በደለኛ ነኝና በየኹለት ቀኑ ነው መመገብ የምፈልገው" አለች። ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ "እኔ ብዙ ኃጢአት ሠርቻለሁና በየአራት ቀኑ ነው የምመገበው" አለች። በዚህ ኹኔታ ጥቂት እንደ ቆየች ደግሞ ወደ እመ ምኔቷ ሄዳ በኃጢአቴ ጌታን አሳዝኜዋለሁና እኔን ለብቻዬን በበኣት አስቀምጠሽ ዝጊብኝ፣ ጥቂት ዳቦና የምሠራውን ሥራ በመስኮት በኲል ስጪኝ አለቻት። እመ ምኔቷም እንዳለችው አደረገችላት። ያቺም ሴት እስከ ዕለተ ዕረፍቷ ዝጉሐዊት ባሕታዊት ኾና ኖረች።" እንዲል። (ዳንኤል ክብረት (ዲ/ን፣ አርተር)፣ በበረሓው ጉያ ውስጥ፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 75-76)።

=> ከማንኛውም ክፉ ልማድ ከኾነብን ኃጢአት ለመውጣት የቅዱሳንን ጸሎት ከልባችን ኾነን ሳናቋርጥ እንጠይቅ። እግዚአብሔር ስለ ወዳጆቹ ጸሎት ብሎ ከተላመድነው ክፉ የሕይወት መርሕ ያስወጣናልና። ይህ ኹል ጊዜ በአንዴ ብቻ የሚኾን አለመኾኑንም ልብ በሉ። አንዳንዴ የብዙ ጊዜ ያልተቋረጠ ትጋታችንን ሊፈልግ ይችላል፣ አንዳንዴ ወዲያውኑ ልቡናችን ሊከፈት ይችላል። የልቡናችንን ቅንነት ሲያይ እግዚአብሔር መልአኩን ወደ ቤታችን በሰው አምሳልም ቢኾን ልኮ ከየተያዝንበት ክፉ ወጥመድ ሊያስወጣን ይችላል። እግዚአብሔር በአንዳች መንገድ ውስጣችንን እንዲነካው ተስፋ ሳንቈርጥ ልንጸልይ ይገባል። ከልብ በልቅሶ የኾነ ጸሎት የለመድነውን ክፋት ማስወገድ ይችላልና።

=> በታሪኩ ላይ እንደተመለከትነው ልክ እንደ አባ ሰራፕዮን ለብዙዎቻችን የሚጸልዩ ቅዱሳን መኖራቸውን በማሰብ ልንጽናና ይገባናል። በምንም ዓይነት የኃጢአት ሕይወት ውስጥ ያለን ብንኾንም ልባችንን መለስ ካደረግን እግዚአብሔር ሊቀበለን ፈቃደኛ እንደ ኾነ ልብ ማለት ይገባል። በግልሙትና ውስጥ የነበረችው ሴት የቀደመ ነገሯን ትታ እግዚአብሔርን ማግኘት ወዲያውኑ መፈለጓን እናስተውል። ወንድም እኅቶቼ ሆይ! በእርግጥ እኛ ብዙ ዕድሎች እንዳሉንና በአግባቡ እንዳልተጠቀምንባቸው አስተውሉ! ነቅተንና ተግተን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጸሎት ብንሳተፍ የእውነት መለወጥ እንችላለን። በየዕለቱ የሚነበብልንን የቅዱሳንን ተጋድሎና ሕይወት የያዘውን ስንክሳር ከልብ ብንሰማ ተጣብቀን የተያዝንበት ኃጢአት ምን ያህል መርዝ እንደ ኾነ ልብ እንላለን። እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ የሚያሰማንን ድምፁን እንስማው፡ ከውስጣችንም ለመለወጥ እናስብ። ጥሩ ክርስቲያን መኾን የማይቻል እንደ ኾነ አድርገንም አጽር ቅጽር አንሥራ፤ ይልቅስ "ኃይልን በሚሰጠን በክርስቶስ ኹሉን እንችላለን" እያልን በመንፈሳዊ ኃይል እንመላ። በየደቂቃውና በየሰዓቱ ኹሌም "እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ" እያልን በልቡናችን ውስጥ ያልተቋረጠ ጸሎት እንጸልይ። እግዚአብሔር ከክፉ መንገዶቻችን ይመልሰን።

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

15 Oct, 12:03


የወይባ ጢስና አጋንንታዊ ሴራው || ባህል ሆነው በአጋንንቱ የተጠለፉ የባከነ ሕይወት እየመራን ይሆን? || ያልተረዳነው የመናፍስቱ ድብቁ ሴራ #ebstv 😱😭 https://youtu.be/aOksr8cr1HQ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

14 Oct, 17:09


በጥንቃቄና በማስተዋል አዳምጡ!! የጋብቻችን ሁኔታ በዚህ ዘመን ትዳርና መስቀልን ምን አገናኛቸው? | ሁላችንም ክፋትን እናግዛለን #ethiopia 😭😱

https://youtu.be/2x91sW-fGe4?si=M80nfUnDvb10kUIi

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

14 Oct, 05:55


* አትሌት ግዛው ታደሰ አሸንፎ የተሸለመውን ሽልማት ለመልዓከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ልጅ ለቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ በስጦታ ሰጠ

* አትሌት ግዛዉ ታደሰ ከብዙ መከራ እና ስቃይ በኋላ በፆም፤ በፀሎትና በስግደት የክፉ መናፍስትን ሴራ በከፍተኛ ትግል በመቋቋም እና በማሸነፍ በዓለም አቀፍ ማራቶን ዉድድር ለተወዳዳሪነት እጩ ይሆናል እጩ መሆን ብቻ አይደለም በተሳትፎዉም በዉድድሩ ላይ አሸናፊ ይሆናል።

* ታድያ ይህ ወንድማችን የማሸነፌ ሚስጥር ድንግል ማርያም ነች የሚለዉ አትሌት ግዛዉ እሷን የመቅረቤ እና የመማፀኔ ሚስጥር ደግሞ የእርሶን ትምህርት እና የአምልኮት ሕይወት ማወቄ እና የተግባር ክርስቲያን መሆኔ ሽልማቱ ለእኔ በአለማዊ ለምሮጠዉ ሳይሆን ለእርሶ ለመንፈሳዊ ሯጩ ይሁንልኝ ብሎ ሽልማቱን በስጦታም በሽልማትም መልኩ አበርክቶልኛል። አገልግሎቱም እንዳይቋረጥ በማንኛውም ነገሮች እገዛ እንደሚያደርግልን ቃል ገብቷል!

* በመቀጠልም የበረከት ስራ፦ በመልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ አማካኝነት ከአንድ መቶ ሰላሳ ሺህ ብር በላይ ለ ሰሚት ዋሻ መካነ ሕይወት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ገቢ ሆንዋል።

* በዘመናችን እግዚአብሔር ድንቅ ስራውን እየገለጠ መሆኑን ምስክር እንድንሆን ስለፈቀደልን ስሙ ቡሩክ ይሁን። በአገልግሎታችን ብዙዎች ከጭንቀታቸው አረፈው ስር ሰዶ በስውር ከያዛቸው እና ካሰቃያቸው ጠላት ተላቀው እንደ ማየት በጎ ህሊና ላለው የሚያስደስት ነገር የለም።

#Subscribe #Like #Share
   👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

13 Oct, 16:33


ይሄንን ምልክት ካያችሁ በጭራሽ አትሸበሩ! የጸሎት መጽሐፍትን ስናነብ የዲያብሎስ ውጊያዎች የጸሎት መጽሐፍትና የአጋንንት ውጊያ #ethiopia 😱😭💥🚩

https://youtu.be/IIOjnXthkws

2,120

subscribers

1,553

photos

77

videos