እኔና አንቺ

@fikrhn


ስንቶቻችን ነን 💏ሮሚዮ ና ጁልየትን የምናውቀው በቅርብ ቀን ጣፋጭ የፍቅር ታሪካቸውን C.soon
ከዚህ በተጨማሪም
የchannaሉ መጨዋወቻዎች
1ስነ-ጽሁፍ📜
2ግጥም📝
3አስገራሚ ትረካዎች🎵🔬
4ቀልዶች ና😂



5አዳዲስ ነገሮች እንዲሁም ሌሎች ፈጠራዎችን እነሆ ለናንተ ይዘን ከች እንላለን

for any Message Contact wz
@RfJolly
@MacTj
@E7F15Lv

እኔና አንቺ

17 Apr, 09:54


👸
ብሌን ?

ወዬ

ችስታ  መሆኔ አልታየሽ ይሆን ? በኋላ አስቤዛ  እንዴት በዚህ ፍጥነት አለቀ?  አንበጣ ግሪሳ አሰማርተሽ ነው ወይ ?ማለቴ አይቀርም ....

ዋ ...መምረጥ አይደለም የሚከብደው ምርጫን መኖር እንጂ
አልኳት ፌዝ ባዘለ አኳኋን

ሳቀች ሳቅ ከፊቷ አይጠፋም ።  አይኔን እያየች ትህትና ባለው ፈገግታ

"እየውልክ  እኔ ድህነትን አልፈራም ። አባቴ ግንበኛ ነበር እናቴ እንጀራ ትሸጥ ነበር ። አባቴ አባወራ ነው እቤት ውስጥ ንጉሱ እሱ ነው ። ትሁት ንጉስ ።

እናቴ አባቴን ታንቀባርረዋለች ። ሲሚንቶ ሲያቦካ አሸዋ እና ድንጋይ  ሲታገለው ውሎ ነው የሚመጣው ብላ ጥሙን የሚቆርጥለት  ጠላ ትጠምቅለታለች ። ሲመጣ እንደእንግዳ ነው ሽርጉድ የምትለው ።

እንደ እንግዳ እየተገለገለ ይመገባል ። እየተገለገለች  ትጎርሳለች  ያጎርሳታል ።

አባቴ እናቴን አልማዜ የኔ አልማዝ ይላታል ። ስትቆጣው ይሰማታል እኛን ስትቆጣ ጣልቃ አይገባም ስሞታ ስትነግረው
ይሰማታል ።

እናቴ ሃይለኛ ናት ከጎረቤት ስትጣላ አልማዝ አልማዜ  ግቢ ሲላት አባቴን ትሰመዋለች ትገባለች ከገባች በኃላ ተይ ተያቸው እያለ ያረጋጋታል ታብራራለች እያብራራች በዝምታ እየሰማት  ትረጋጋለች ።

እወድሃለሁ እወድሻለሁ ሲባባሉ ሰምቼ አላውቅም መዋደድን ይኖራሉ ።

እናቴ አመም ካደረጋት ቶሎ ቶሎ እቤት ይመጣል።
እናታቹ እንዴት ዋለች አመማት እያለ በር ላይ ያገኘውን ይጠይቃል ።

አልማዜ እንዴት ነሽ ይላል እንደገባ  አጠራሩ እና አጠያየቁ ስጋት እና ስስት አለው ። ምን ልግዛልሽ? ምን ላምጣልሽ ? ይላል

የፊቱ ሁኔታ ያለችውን ሁሉ  እንደሚያመጣ አይነት ነው ።

ሽቦ አልጋችን ላይ ጫፍ ላይ ተቀምጦ እጁን ግንባሯ ላይ እያስቀመጠ ሙቀቷን ይለካል  አይበሉባዋን  ይስማል ።

ስታየው የምትበረታ ይመስለኛል ።

ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆነ ወይ ደሞ በየቀኑ እየተለማመጠች ስለምትመግበው ይሆን ? ምችት ጥብስቅ ድልድል ያለ ሰውነት ነው  ያለው ።

እኔን ጨምሮ ሶስት ልጆች ነበራቸው ። ደስተኛ ነበሩ ደስተኛ ነበርን ።

ማታ ማታ ካርታ እንጫወታለን ። አሹቅ ወይ በቆልት አልያ  ሽንብራ አይጠፋም ሻይ ይፈላል ። አባቴ ጨዋታ ይችላል አናቴ ጨዋታ ይገባታል ስትስቅ  በሳቅ እያጀብናት ነው ያደግነው ።

እንዴት ደሃ ሆነን ድህነታችን ሳይታወቀኝ አደኩኝ ?! 
በዛ ድህነት ውስጥ እንዴት  ጨዋ ጌጣጌጥ የማይባርቅብኝ የማልታለል  ሆኜ አደኩኝ ? እንዴት ቁጥብ ጨዋ ህልም ያላቸው ወንድሞች  ኖሩኝ ?

ድህነት አይደለም የሚያስፈራኝ ። ፍቅር አልባ ህይወት መተማመን የሌለበት ኑሮ እንጂ ። ሃብት ኖሯቸው የቀዘቀዘ ጎጆ ያላቸው ብዙ ሰዎች አውቃለሁ ።

ከወደድኩህ ፣አምላክህን ከፈራህ  ፣ህልም ካለህ ፣ጠንካራ ከሆንክ ትበቃኛለህ  I think ሁሉም አለህ ሊያውም ትበዛብኛለህ ።

እወድሃለሁ
           ©  Adhanom Mitiku

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

15 Apr, 09:20


እኔና አንቺ pinned « 😂 ሳቅኩባቸው 😂 "ከትናንት የተላቀቀን ሰው ከትናንት የሸሸን ሰው እንዴት #ዛሬ ወደ ኋላ አሻግሮ ሊወቅሰው ይቻለዋል?"...... የተሰጠኝን ቢያዩ ለተሰጠኝ የህይወት በረከት አምላክን ያዳላል ብለው ከመክሰስ ወደ ኋላ ባላሉ ነበር። ዘማዊት ነበረችኮ ምነው ካልጠፋ ሴት የቡና ቤት ሰው ያገባል? የሚቀርቧት ሴቶች በቧልት ሲያወሩ ድንገት ጆሮዬ ሰማ.....የዚህን ጊዜኮ ምናምኑም አይጠፋባትም።(ሌሎች…»

እኔና አንቺ

03 Dec, 05:29


ገጣሚ፦ ደስአለኝ ቢተው
ምንጭ- ያልተፈቀረች ሴትና ሌሎችም የግጥም ስብስቦች ላይ የተቀነጨበ

🗣....... #ጆlly

@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

12 Nov, 17:38


#ሰሎሜ

ልጅ ሆኜ ነው በዝግታ ስታለቅስ የምሰማት፡በዝምታዋ ውስጥ ተኮራምታ ስመለከት ገና በስድስት አመቴ ማንባትን እፈራ ነበር:: የሀዘን ቃልን ከሷ ፊት በላይ የሚገልጽ ማንንም አላየሁም "በወደቀ ህይወት ውስጥ የተገኘ ሴትነት" ትላለች በእሮሮዎቿ መሀል..... በተከፋችበት ቀን ሁሉ አባቷን ትናፍቃለች፤መነሻዋን አብርቶላት መዳረሻውን ላጠፋችበት የአባቷ ቃል ሰርክ በቁጭት እንደነደደች ነው።ብዙ ጊዜ የተነፈገቻቸውን ነገሮች አብዝታ እያሰበች፣ጣርያው ከተበሳሳው ታዛዋ ስር ቁጭ ብላ ስትተክዝ አያታለሁ።

መሞንጨር የጀመርኩት በእሷ ታሪክ ነው።የመጀመርያ ድርሰቴ እሷ ናት።በአይኔ ያየሁት ማንነቷን በብእር ማቅለም ህመሟን ስለሚያሳንስብኝ አልጽፈውም ነበር።
ልጅነቷን፣ሴትነቷን፣ቤተሰብ ማጣትን እሷን ሆኜ ነው ያደግኩት ጥንካሬና ስብራትን ዘወትር ሳትነግረኝ ከሁኔታዋ እማር ነበር።መለየትና ብቸኝነትን ነፍስ እስከማውቅበት ጊዜዬ ድረስ በደንብ አለማምዳኛለች።

በትኩስ ገላዋ በሙቀቷ ነደው በወጣትነቷ የተጣቧት፡ ከጭኖቿ ስር ለመገኘት የሚደረድሩትን የመሃላ ፍሬ አልባ ንግር፡ በስሜት የተወጠረ ስጋቸውን ለማስተንፈስ የክህደት ቃልን ሰጥቶ የከሸፈ ስጦታቸውን ሲቸሯት ከኛ ቤት አጥር ቀዳዳ አሻግሬ እያየሁ ነው የኖርኩት።የምታፈቅራቸው ወንዶች በሙሉ እንደ በረዶ አይበረክቱላትም ጸሃይ ይመስል ከፍላጎታቸው በኋላ ይቀልጣሉ ሁሉም በጊዜ ትተዋት ይበራሉ። በየዋህነት ትወዳቸዋለች እነሱ ግን በብልጠት ኑሮዋን ያከብዱባታል።ሁሉም የመንደራችን ሰዎች በሙሉ ውጣ ውረዷን ከመረዳት ይልቅ የፍርድ ሚዛናቸው ላይ ማስቀመጥ ይቀላቸዋል።
ሳይገባቸው ይረዷታል፡:" የአበባነት ዘመኗ ኮስምኖ የደረስኩበት ወጣትነቴ የመልካምነትን ኢ-አጸፋ አሳይቶኛል። ዘመኗ ዘግይቼም ቢሆን ተከትሎኛል። በህጻንነቷ ያጣቻት የእናቷን ጠረን ከቶ አታውቀውም ባላሳደገቻት የእናቷ ምትክ በጉስቅልና ዘመኗ የተነፈገቻቸው የኑረቷ ብሶት ሔዋንነቷን ከስሩ ሊቀጩባት ይታገሏታል።እናትነት ህልሟ ነበር።ከነ ህመሟ ጠንካራ ናት።

በውርስ ከምትኖርበት የቀበሌ ቤት ጎረቤታቸው ሆኜ በጉልምስናዋ ጎርምሻለው ነፍስ ባላወቅኩበት እድሜዬ እንባና መከፋቷን ከገላዋ ላይ እየተመለከትኩኝ፡እየሰማው ነው ያደግኩት።ሰዎችን በሚገባ ያወቅኳቸው በራሴ ትርምስ ሳይሆን በሷ ታሪክ ነው።
"ሳታውቅ ተረድቻት ሳልናገር ኖርኩት።" ከአመታት ቆይታ በኋላ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ የጓጋሁት ግን ሰሎሜን ለማየት ነበር::ትናንቷንና ዛሬዋን ላነጻጽር፡በአሮጌ ቆርቆሯችን አጥር እንደ ልጅነቴ በቀዳዳው ተመለከትኩኝ።እድሜዋ ገፍቷል ጸጉሯ:ቆዳዋ፡ሁናቴዋ እርጃናዋን እያጎሉት ነው...........#ሰሎሜ! እንባዬ መጣ አሁንም በረንዳዋ ላይ ተቀምጣለች......አሁንም ተክዛለች........

........ #ፍርድኤ(Joሊ)

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

25 Jul, 16:12


የዚህ መንደር ነዋሪዎች የጋሼ ሰላምነህን ልጅ ህልም እንድናልም ልጆቻቸውን ያስገድዱናል።በተለያየ መኝታ በተለያየ እንቅልፍ ውስጥ አንድ አይነት ህልም እንዴት ይታለማል።የሆነ ሰው ያለፈበትና የደረሰበት ስኬት እንዴት የሌሎች የብዙዎች መንገድና መዳረሻ ይሆናል...........

(ከ #ጠበኛ_እውነቶች የተወሰደ፦ በሜሪ ፈለቀ) ያላነበባችሁት ተጋበዙልኝ ታተርፉበታላችሁ። 🗣 @RfJolly

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

25 Jul, 16:11


የዓለም ወርቃማ ጥቅሶች

✓ We must all learn to live together as brothers, or we are all going to perish together as fools.
-Martin Luther King Jr.
➢ “ሁላችንም እንደ ወንድማማቾች ተፈቃቅረን መኖር ካልቻልን፤ እንደ ሞኞች ተያይዘን መጥፋታችን አይቀርም::”

✓ Love is fire. But whether it's gonna warm your heart or burn your house down you can never tell.
Jason Jordan.
“ፍቅር እሳት ሲሆን፤ መቼ ልብህን እንደሚያሞቀው፣ መቼ ቤትህን እንደሚያቃጥለው አታውቅም፡፡”


✓ Success is not the key to happiness. Happiness is the key to success. If you love what you are doing, you will be successful.
Albert Schweitzer.
➢ “ደስታ የስኬት ቁልፍ እንጂ፤ ስኬት የደስታ ቁልፍ አይደለችም፡፡ የምትሰራውን የምትወደው ከሆነ ስኬታማ ትሆናለህ::”


✓ The bad news is time flies. The good news is you're the pilot— Michael Althsuler.
➢ “መጥፎው ዜና ጊዜ መብረሩ ሲሆን፤ መልካሙ ዜና ደግሞ አብራሪው አንተ መሆንህ ነው፡፡”


✓ Every king was once a crying baby & every building was once a picture. It's not about where you are today but where u will reach tomorrow.
Anonymous.
➢ ሁሉም ንጉስ ባንድ ወቅት የሚያለቅስ ህፃን ነበር፤ እያንዳንዱ ህንፃ ንድፍ ነበር፤ ወሳኙ ነገር የዛሬው አንተነትህ ሳይሆን ለነገ የምትሰራው ማንነትህ ነው፡፡

✓ Age wrinkles the body. Quitting wrinkles the soul.
Anonymous.
➢ “እድሜ ቆዳን ሲሸበሽብ፤ ተስፋ መቁረጥ ነብስን ያነትባል፡፡”

✓ I don't know the key to success, but the key to failure is trying to please everybody.
Bill Cosby.
“የስኬትን ሚስጥር አላውቀውም፤ የውድቀት ሚስጥር ግን ሁሉንም ለማስደሰት መሞከር ነው፡፡”

✓ God gave us a gift of 86,400 seconds today. Have
we used one to say Thank you? William Arthur Ward.
➢ “ፈጣሪ በዛሬዋ ቀን 86,400 ሴኮንዶችን ሲሰጠን፤ አንድዋን ሴኮንድ እንኳ ለምስጋና አውለናታልን?”


A successful marriage requires falling in love many times, always with the same person.
Mignon McLaughlin.
➢ “ስኬታማ ትዳር ማለት ከአንድ ሰው ጋር በተደጋጋሚ በፍቅር መውደቅ ማለት ነው፡፡”


✓ What is success? It is a toy balloon among children armed with pins
Gene Fowler.
➢ “ዝና፣ መርፌ በያዙ ብዙ ህፃናት መካከል ተወጠሮ የሚንከባለል ፊኛ ነው::


✓ Success is more permanent when you achieve it without destroying your principles. Walter Cronkite.
➢ “የራስህን እምነትና ፍልስፍና ሳታጣ የምታገኘው ስኬት ቀጣይነት ይኖረዋል፡፡”

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

24 Jul, 17:34


✍️.....Jolly( @RfJolly )

እኔና አንቺ

07 Jul, 17:25


✍️

ለካስ የሚሄዱት እንዲኖሩ ስላልተፈቀደላቸው ነው። እግዜአብሔር የወደደውን ያደርጋል፡ ለኛም የተወደደልን እስከ እድሜ ማምሻ ይቆያል። አቤት ደስ ሲል.......

@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

06 Jun, 17:00


ሲመሽ እንደሚነጋ ሁሉ፤ሲነጋም እንደሚጨልም አትዘንጋ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ቀንህ ምሽትህን ይወስነዋልና::

(እድሜ ማምሻ)

እኔና አንቺ

04 Jun, 18:15


ሁሉም ነገር የራቀህ አለም ውስጥ ወስዶ እንዲያኖርህ የፈቀድክለት ቀን ያንተ ብርሃን እየደበዘዘ ይጨልማል።

(ከነገ ዛሬ የተሰረቀ)

እኔና አንቺ

04 Jun, 18:09


ለተሰጣቸው በረከት ሳያመሰግኑ እየጸለዩ ለተነፈጋቸው ነገር ሲያለቅሱ ሳይ አሳዘኑኝ።

(ከምስኪኖቹ የተወሰደ)

እኔና አንቺ

14 May, 17:18


😂 ሳቅኩባቸው 😂

"ከትናንት የተላቀቀን ሰው ከትናንት የሸሸን ሰው እንዴት #ዛሬ ወደ ኋላ አሻግሮ ሊወቅሰው ይቻለዋል?"......
የተሰጠኝን ቢያዩ ለተሰጠኝ የህይወት በረከት አምላክን ያዳላል ብለው ከመክሰስ ወደ ኋላ ባላሉ ነበር።

ዘማዊት ነበረችኮ ምነው ካልጠፋ ሴት የቡና ቤት ሰው ያገባል? የሚቀርቧት ሴቶች በቧልት ሲያወሩ ድንገት ጆሮዬ ሰማ.....የዚህን ጊዜኮ ምናምኑም አይጠፋባትም።(ሌሎች ሲሳካላቸው ለምን ክፉዎች እንሆናለን?)... የሆነ ነገር አስነክታው እንጂ በሰላሙማ እንደዚህ ሊሆን አይችልም.....(ፍቅር እፉዬ ገላ መሆኑን ማን ያስረዳቸው መነሻው እንጂ መድረሻው እንደማይታወቅ ማ ይንገራቸው? እኔ ወይስ...ጊዜ ?) የተሻለች ሴት ለማግኘቴ የተሻለች ሴት ለመሆኗ ከምንም በላይ ምስክር እነሱ ናቸው። በዛ ላይ ቆንጆ ነገር ነው...አንቺ!! አለቻትና ተሳሳቁ። ባክሽ መጨረሻዬን አሳምርልኝ ማለት ነው። (እስኪ አስረዱኝ መጨረሻ ግን ምንድነው? የምንፈልገውን ማግኘት ወይስ የሚያስፈልገንን? እውነት መጨረሻ ምንድነው እኔስ ያገኘውት የቱን ይሆን? ) ብዙ ብዙ አሉ...........ሰውን እንዴትና በምን የንጹህነታችን መስፈርት ሁል ጊዜ ትናንቱ ውስጥ ብቻ ልናኖረው ይቻለናል?
ሁሉንም ሰማዋቸሁ 'ሰው የሚያስበውን ነው::' ተውኳቸሁ #ሳቅኩባቸው....በዚያች ቅጽበት ግን ጅልነታቸው፣የጭንቅላታቸው ማነስና ቀሽምነታቸው ተደማምሮ የእውነት አሳዘኑኝ።'ባልታወቀ መዳረሻቸው ውስጥ የታወቀው መዳረሻዬን ኮራሁበት..... '

ቃልዬን ደጋግሞ ማግባት አማረኝ።መባረኬን እንኳን የማውቀው እሷ እንደተሰጠችኝ ሳስብ ነው።የተመሰቃቀለውን ህይወቴን ለማስተካከል አብራኝ አሳሯን ስትበላ የነበረው ታወሰኝ(ጀግናዬ አልኳት በልቤ)።ማነው ዛሬ በችግርህ ዳፋህን ተጋርቶ አብሮህ የሚቆም?
እኔን ወደ ብርሃን ለመመለስ የለፋችውና፣የደከመችው ድካሟ ለኔ ግን የዘላለም ጉልበት ሆኖኛል። ለኔ ስትዳክር፣ህመሜን መሸከም አቅቶኝ ስንገዳገድና  እራሴን ሳጣው የፈለገችኝና በውድቀት ተሞልቼ ስንደፋደፍ ያዳነችኝ እሷ ናትኮ.....በድክመቴ ሳይገባኝ ያኔ የጮውኩባትን፣ያስቀየምኳትን እንኳ አልፋ ዛሬ ከጉያዬ ሳያት በምን እንደምክሳት ግራ እጋባለሁ.. ይቅርታ ከልቤ!

ከጓደኞቼ ተለይቼ ወደ ቤቴ እስክሄድ እንኳን ናፍቆቷ ያቁነጠንጠኛል። ተገርሜ እስቃለሁ
እሷ እንኳን የምትቀናበትን ክብርኮ ነው የምሰጣት.....ስስቴ መልሶ ያሳሳታል።ስትስቅልኝኮ ሀዘኔ ይከሽፋል። በጊዜ ተመለስ እሺ ስትለኝ ወደምሄድበት ለመጓዝ ከእግሬ ጋር እጣላለሁ።
እሷኮ ህይወት ናት፣እሷኮ ደስታ ናት ፣እሷኮ ከውድም ውድ የሆነች የአብራኮቼ ክፋዮች #እናት ናት። ካለመኖር የቀሰቀሰችኝ፣የተሻለ እንድሆን መንገድ ያሳየችኝ በትሬ ናት። ከቃል በላይ እወዳታለሁ።
(እስኪ ንገሩኝ ከዚህ በላይ ያማረ መጨረሻ ምን ይሆን?)

ቡራኬዬ ናት፣ሰላሜ ናት፣ምሳሌዬ ናት፣እምነቴ ናት........ሁሉዬ ናት
አዎ... ከቃል በላይ እወዳታለሁ

"የእኛን መታደል የእኛን ጥሩነት የሚያዩት የተባረኩ አይኖች ብቻ ናቸው።"

        ሻሎም!.... ለአንባቢያን  ሻሎም              #ለእኔና_አንቺ......
✍️...... #Jo_ሊ

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

10 May, 17:18


* #የዝምታ_መልስ *

ማጣትን ብቻ እያሰበ ስለነገ የሚጨነቅ ልብ ከዛሬ ተኳራፊ ነው።ማሰቧን አልጠላውም ግን ባላሰብኩት ስለምታስበው ታሳዝነኛለች....ላስረዳት ጊዜ ያስፈልገኛል::ወይ እሷ ልትረዳኝ ጊዜ ያስፈልጋታል።

አብርያት ስሆን አይኖቼን መክደን ስለሚቀናኝ...
እኔን ላለማየት ነው የምትጨፍነው አይደል ትላለች?  ከሷ ውጪ እንደታወርኩኝና አለማየቴ ውስጥ እንደማያት ዘንግታ ........
በወሬዎቻችን መሃል ዝምታ ሲውጠኝ ከኔ ጋር ሁነህ ምንድነው የምታስበው? የእለቱ ጥያቄዋ ነው....መጠየቅ ትወዳለች
እኔኮ የማስበው እሷ ከሌለች የመኖሬን ምስቅልቅል ስሌት ነው።ዝም ስል የማስበው አጠገቤ በመሆኗ የአምላክን ድንቅነት ነው....ምን አድርጌ ይሆን የተሰጠችኝ እያልኩ የጸሎቴን መዳረሻ ምስጋና ሳደርስ ነው.....

ለሁለት ቀን ስልኬ ተበላሽቶ ነበር።አለመደወሌ ስህተት አልነበረም ለኔ።ማውራት ካልፈለግክ ለምን እንደዛ ታደርጋለህ? ትላለች። እኔ የነገሩን ምክንያታዊነት እንደ አጋጣሚ ተጠቀምኩኝ እንጂ በሆን የተፈጠረ አልነበረም። እነዛን ደባሪ ቀናቶች ደግሜ ማሰብ እንኳን አልፈግም ለካስ 'በነፍስ የተጣመረን በስጋ መራቅ አይገድበው ኖሯል።' ራሴን ለመፈተን ብጥር ናፍቆት ግን የፍቅሯ ባርነት ስር የጣለኝ ሎሌዋ ነበርኩኝ።
ከሌላ ሰዎች ጋር ያየችኝ ቀን በኩርፍያዋ ውስጥ ስጋቷን አየዋለው፣በድርጊቶቿ ደግሞ አትንኩብኝ ባይነቷ ያሳብቅባታል።እንዴት ላስረዳት...?
ሌሎችን ሳልፈራ እንድቀርብ የሚያደርገኝኮ የእሷ በእኔ አለም ውስጥ የመኖሯ ነጻነት ነው።ልቤም ነፍሴም ከሷ ሆኖ በደመ ስጋ ብቀርባቸው ምን ዋጋ ይኖረው ይሆን? መጨረሻዬ በሙሉ ያረፈው በክቡር ልቧ ውስጥ ነው
ግን ሁሉም ጥያቄዎቿ መልስ ነበራቸው::ዝም ያለ መልስ...
ከዚ በኋላ ማንንም መልመድ አልፈልግም።አንቺን ባጣ አንዳች የሚተርፍ ነገር አይኖረኝም አልኳት... እቅፎቿ፣ስስቷና፣ግርምቷ መልስ ነበሩ

አንድ አለምን አንድ ነፍስን ከመስጠት የላቀ ምን ይኖር ይሆን....?

በእሷነቷ የህይወት ሸራ ላይ ቀለሞቼን አሳርፌ..ትናንታችንን፣ዛሬንና፣ነገዎቻችንን በጥበብ፣ በናፍቆት እያዋዛው፤ የመኖርን፣የተፈጥሮን ሁለት ገጽ እየሳልኩኝ እንደ ብራብሮ የፍቅርን መአዛ ከመልካም ሴትነቷ ውስጥ እየተቸርኩኝ የዘመንን፣የነፍስን ቅሪት እስከ እድሜ ማምሻዬ ገፍቼ በደበዘዙት አይኖቼ ተመልክቻት አቅም ባጡት መዳፎቼ በብርቱ ይዣት እርጅና ወቅሮት በተሸበሸበው ፊቴ፣ጊዜ በራሱ ባጎደላቸው ጥርሶቼ እየፈገግኩኝ፣ ማብቂያዬን፣ ከዚህ አለም መሄጃዬን ስጠብቅ እኖራለሁ።
እሷ የመጨረሻዬ መጨረሻ ናት ሌላ ታሪክ አይኖርም........
.... #Jo_ሊ

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

08 May, 17:16


"ከንፈር መሞከር እፈልጋለሁ።" አልኩት
"እስከዛሬ ተስመሽ አታውቂም።?"
"እስከዛሬ ፈልጌ አላውቅም።" ከንፈሩን አቀበለኝ።
ወራት ነጎዱ……
"ድንግል መሆን አልፈልግም።" አልኩት
"ገናኮ 18 ዓመትሽ ነው ማሬ። ለምን ትንሽ አንቆይም? "
"አሁን ነው የምፈልገው።"…… እሱንም አቀበለኝ።
ወራት ነጎዱ………
"ጫት ለጥናት ጥሩ ነው ሲሉ ጊቢ ሰማሁ። መሞከር ፈልጋለሁ።"
"አይ አይ አይ…… ጥሩ አይደለም ማሬ ስሞትልሽ አትሞክሪ።" አለኝ እያንገፈገፈው
"ልንገርህ ብዬ እንጂ መሞከሬ አይቀርም። እነቤቲ ዛሬ እንቅማለን ብለዋል…… " ሳልጨርስ ቀድሞ
"እሺ በቃ ፍቅሬ እሺ…… መሞከር ከፈለግሽ  እኔም አብሬሽ እሞክራለሁ። ከኔጋ ቃሚ…… " ጫቱንም ፍራሹንም ሰጠኝ።…… መቃም በፈለግኩ ቁጥር ከስራ እየቀረ አብሮኝ ቃመ።
ወራት ነጎዱ………
"ልመረቅ ስለሆነ ስክር ማለት እፈልጋለሁ ክለብ ውሰደኝ" አልኩት……
"እሺ እንደፈለግሽ ሁኚ እጠብቅሻለሁ።" አለኝ…… መጠጡን ቀዳልኝ… እንደፈለግኩ ሆንኩ……
ሰዓታት ነጎዱ……
"ማጨስ እፈልጋለሁ።"
"እማ ስካሩ አይበቃም? ፕሊስ ጭሱ ይቅር? "ለአፉ አለኝ እንጂ የፈለግኩትን ሳልሞክር ማቆሚያ እንደሌለኝ ያውቃል።
"እሺ ገዝቼልሽ ልምጣ? "
"አልፈልግም የተጨሰ ግማሽ የደረሰ ሲጋራ ነው ማጨስ የምፈልገው።… እንደውም ያን ሰውዬ ስጠኝ እለዋለሁ።"
"እሺ እሺ በቃ የተጨሰ አይደል ማጨስ የምትፈልጊው? በቃ እኔ አጭሼ ሰጥሻለሁ።…… ከሌላ ሰው ከንፈር ተውሰሽ አታጨሺም! " አጭሶ ሰጠኝ። አጨስኩ።… እስክመረቅ በጨፈርኩ ቁጥር የተጨሰ ሲጋራ አቀበለኝ።
ዓመታት ነጎዱ…… ብዙ ዓመታት…… እንደተመረቅኩ ከሃገር ወጣሁ።…… ተራራቅን…… ከጊዜ በኋላ መገናኘት አቆምን።… አገባሁ…… ወለድኩ…… ለበዓል ወደሃገር ቤት ተመልሼ ሳለሁ መንገድ ላይ አየሁት።…… ደነዘዝኩ። ያ ሊነኩት የሚያሳሳ ቆዳው ከስሎ…… የሚያንጠራራ መለሎ ቁመናው ጎብጦ… የሚያኮራ ደልዳላ አካሉ ኮስምኖ… አይሆንም እሱ አይሆንም!
"አቁምልኝ! አቁምልኝ! "ጮህኩኝ ባሌ ላይ… ዘልዬ ወረድኩ እና እጁን ይዤ አስቆምኩት።
"እማ አንቺ ነሽ ስካሬ እያስቃዠኝ ነው? " አለኝ ከቃላቶቹ እኩል የርካሽ መጠጥ ጠረን እየተፋ
"አባ አንተ ነህ? ምን ሆነሃል? በየሱስም ምን አገኘህ? ታመህ ነበር? በየሱስ ስም…… ደህና ነህ? ቆይ ምንድነው የተፈጠረው?"
"አንቺ እማ! አንቺ ነሽ የተከሰትሽው! ሌላ ማን አለ አንቺ "…
የሆነ የአዳም ረታ መፅሃፍ ውስጥ ያለሁ ገፀ ባህሪ የሆንኩ መሰለኝ። እንጂማ እኔ በእውነታው ይህችን ሴት ልሆን አልችልም። በሱስ ምክንያት በተደጋጋሚ አማኑኤል ሆስፒታል እንደነበረ ነገረኝ። በዛ ምክንያትም ስልክ ኖሮት ስለማያውቅ ላገኘሁ እንዳልቻልኩ አብራራልኝ……
"እማ አንቺ ማለት የምትበር ቢራቢሮ ነበርሽ…… ነፃ የሆንሽ… ነፃነትሽን የምትወጂ… ካልሞከርሽ የማታረጋግጪ…… ሁሉን ሞከርሽ እኔን ጨምሮ ሁሉን ተውሽ! ሁሉን አስሞከርኩሽ ከሁሉ ተጋባሁኝና ቀረሁ። " አለኝ።

አይ አይሆንም የአዳም አንዷ ገፀባህሪማ ሆኛለሁ።…… ነፃነት? ሌላውን የገደለ ነፃነት? በሌላው ባርነት ላይ የቆመ ነፃነት? የአባን ገፅ ያከሰለ ነፃነት?
……… አይሆንም ውሸት ነው። እኔማ እውን አይደለሁም…

.... ሜሪ ፈለቀ

@fikrhn
@finrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

06 May, 18:23


🧑‍🦯 #እኔና_አንቺ...........? 🧑‍🦯

"ያለ ቦታው ለተገኘ ነገር ምክንያታዊነት እምነት ወይም እውነት ሳይሆን አንጻራዊ ሊሆን ነው የሚገባው።"

የቅርብህን ሰው መለየት ከባድ ነው የአንዱ ስሜት የሌላው ሌላ ስሜትም ነው።በመኖር መላመድ በጊዜ ፍርሃት ውስጥ ተሸሽጎ በማጣት የስጋት እቅፍ ውስጥ ይዋጣል።ሲቀር ሲያልፍ ላይመለስ #ትዝታ ብቻ ይሆናል።

ባንተ ምክንያት ነው እንዲህ የሆንኩት አለች ሲጋራዋን ለመማግ ላይተሯን አውጥታ እየለኮሰች... ኩራትና መጀነኗ ለአመታት ያጬሰ ሽማግሌ እንጂ ከጀመረች ጥቂት ቀናቶች የሞላት እንስት አትመስልም......የማውቃት እሷስ የት ሄደች የት ጠፋች...ለመገረም እንኳን አቅም አጣው  የማደርገው ግራ ሲገባኝ በያዘችው የመጠጥ ብርጭቆ ስር ግማሽ እሷን ግማሽ ሲጋራዋን...አንዴ ትናንቷን አንዴ አሁኗን መመልከት ጀመርኩኝ.....ያ የሚያሳሳው መልኳ፣ልዩ የሚያደርጋት ስብእናዋ፣መካሪነቷ፤ በደግነቷ ከተበላሸ ህይወት ውስጥ የመለሰቻቸው እነዛ የተረሱ ሰዎች፣ አዛኝነቷ፣ ያ ጥዑምነቷ፣ለዛዎቿ አሁን ግን በእሷ ውስጥ የከሸፉ ሆነዋል። የምታደርገውን መቀበል አቅቶኛል

"አፕ አለች ምጋው ስትነሳ እጆቿን ዘርግታ"
"የምርሽን ነው......?"
"የቀልድ የምስብ መስላለው?" አለች ከብርጭቆው ተጎንጭታ እያስቀመጠች
ባለቤትህ እንዴት ናት....?
ደህና ናት....ምነው
ሳታስተዋውቀኝ ለሰርግህ ልትጠራኝ ነው?... አፏ እየተያያዘ ነው

ለምንድነው እንደዚህ የምታየኝ እንደኔ ልትሆን ነው እንዴ እራሴ ነኝኮ.... ሌሎች ጀሌዎቿ ገቡ...ጠሯት እጇን አነሳች እ ጆርጅ፣ቴስ... ፒስ ነው። ከመቼው ኢሄን ሁሉ ሰው ተዋውቃ ነው (ጥያቄዬ ሆነ).......የነሱ ሲገርመኝ መጠጥ ቀጂው ስሟን አቆላምጦ ጠርቶ ነው ምን ይጨመር የሚላት።
"እስኪ አንድ የዛፍ ይዘህለት ና" አለች አስተናጋጁ በቅጽበት ይዞ መጥቶ ቀዳው

''ቺርስ አለች ከፍ አድርጋ"

እምነቷስ፣ሴትነቷስ፣ቁጥብነቷስ
አሁንም ሌላ ጥያቄ.......
አንተን ፍለጋ፤ማጣትን ሽሽት አለች ተክዛ ሳያልቅ ሲጋራውን ጥላው እያየችኝ....
ከሷ አሻግራ በእውነቷ ለኔም ህመምን ሰጠችኝ.....የተሸነፈ ምክንያት....የከሸፈ እውነት መልስ አልባ እውነት....
.
.
.
ሁሉም ታሪኮች ይጀመራሉ እንጂ በሁላችንም ልብ ውስጥ እኩል አያልቁም...........

..... #Jo_ሊ

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

02 May, 16:36


❤️ #እኔና_አንቺ

የደወልኩላት ስለናፈቀችኝ ነበር።ለብዙ ጊዜያት ሞክሬው ከራስ ጋር እየተጣሉ መኖር እየደከመኝ፣ማረፍያዬ ከሷ ውጭ አልታይህ እያለኝ ስረበሽ፣ይቅርታ ልላት ነበር ስልኬን ያነሳውት

....ያኔ ለመጨረሻ ጊዜ ላያት በሰልስቱ ስንገናኝ  ''ላንተነትህ ነፍሴን ባልሰስት ለእኔነቴ ግን ህመምን ሰጠኸኝ።'አለች ባለ ማጥፋቴ ስለቀጣኸኝ አዝኛለው።" አትሂድ አልልህም መንገድ ምንኛ ሸክም እንደሆነ እነዚህ ስብርባሪ ቀናቶች በቂ ናቸው።
ሀሳብህ ምንድነው ? አለች ከመሄድ በማያስቀሩኝ ተስፋዎቿ ውስጥ በስስት ምናልባት እያየችኝ......
'አላውቅም አላውቅም እየሆነ ላለው ነገር ግን አዝናለው'
'የመጨረሻ ቃልህ ኢሄ ነው...? እንድታስብ ጊዜ የሰጠውህ መልስ አለቀ..? አለች በትኩረት እያየችኝ
'አ...አዎ'
በቃ አትጨነቅ የኮበለለን ልብ እግር አያስቆመውም  አይደል ዝም ብዬ ነዋ የለፋውት(የማጣት ፈገግታ)።በነፍስ ካልተጣመሩ ስጋኮ ፈራሽ ነው፤ይቀየራል።እንደማልጨክንብህና ላንተ ልከፍል የነበረውን የህይወቴን ዋጋ ታውቃለህ፣ ብዙ ባወራ ደስታዬ ነበር ግን ምን ሊጠቅም ብለህ.... በቃ ቻው አልያዝህ አለች ድካምና ስብራት ባዘለው ፊቷ ልታቅፈኝ እየቀረበች።

ያኔ እውነት የመሰለኝ አለም እንደ ጉም  ተኖ ከእጄ ወጣ። የሄድኩባቸው መንገዶች በሙሉ ወደ እርሷ እየመለሱኝ፣የመለሱኝ መንገዶች ደግሞ ከእርሷ አላደርስህ አሉኝ።የተለየ የመሰለኝ ነገር የተለየውበት ወንፊት ሆነ እንደ ብናኝ እፍታ ገለባዬ ብቻ ቀረ ማምሻዬ ላይ የትዝታና የናፍቆቷ ንፋስ እየወሰዱኝ ክቡር ፍቅሯን፤ ክቡር ክብሯን አጉልተው አሳዩኝ...ዋጋ የለሽ፣ራስ ወዳድ፣አሁንን ብቻና ለብልጭልጭ የተሸነፍኩኝ ብኩን መሆኔን የስብእናዋ ምስል አሳየኝ።ከሷ ውጪ መኖር ህልም ሆነብኝ።የእውነት ናፈቀችኝ፣የእውነት ላያት ጓጓው......ስልኬን አንስቼ ደወልኩላት ዝምምምም.......'የደወሉላቸው ደንበኛ ቁጥር አገልግሎት ላይ አልዋለም'
ደጋግሜ ሞከርኩኝ ግን ተመሳሳይ መልስ አዲስ ነገር የለውም።

ከወራት በኋላ ግን.........በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ በፈገግታ ታቅፋ አየኋት....ሌላ ህይወት...
.
.
.
#ሻሎም ትዝታዬ..... #ሻሎም  የኔ ናፍቆት......Shalom.....😔

የሁላችንም ልክ በሀቃችን የተመዘነ ነው::

''ሌላ ለመሙላት አጉድለን ስንሄድ ነው የቀነስነው የሚወሰድብን።''

....... #Jo_ሊ

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

28 Apr, 17:27


🚶‍♂🚶‍♂        ❤️❤️                     🚶‍♀🚶‍♀

''የተሻለ ነገር ያለው ወደ ፊት እንጂ ወደ ኋላ አይደለም።''

ከተለያየን ከስድስት ወር በኋላ  ተገናኝተን ስናወራ ነበር ኢሄን ያለችኝ፡፡ ከምትሳሳለት አለም ድንገት እንደመነጠል ጽልመት የሚያለብስ ነገር የለም የተጣጣምንባቸው ነገሮች ብዙ ቢሆኑም።ትንንሽ ኩርፍያዎቻችን አድገው ነበር ለመለያየታችን ምክንያት የሆኑት። የፍቅርን እንቅፋት በጊዜው ባለማንሳታችን የተራራ ያህል ክምር ሆኖ አላሻግር አለን...

ማምሻውን  ጭርታ በሚበዛበት ጎዳና ላይ እየተጓዝን ሳለ በወሬያችን መሃል....
ጥሩ ሁነሻል።ብዙ የተለየ ነገር ስላየውብሽ ደስ ብሎኛል።አዲሱ አለምሽን በደንብ ተጠቅመሽበታል ማለት ነው..... በአሁኑም ቢሆን ይበልጥ ሳቢነትሽ እንደቀጠለ ነው...

እጆቿን ደረቷ እንዳቀፈቻቸው አይኖቿን ፊት ከምታይበት ጎዳና ወደ እኔ አዞረቻቸውና.....በሃዘኔታ አይታኝ አንተም ተለውጠሃል..... አምሮብሃል አለች ፊቷን ወደ ተቃራኒው እያዞረች:(ህመሜ ያመማት ስቃዬ የገባት ትመስላለች)

"እሱ እንኳን ውሸት ነው....ድሮነቴን ዛሬዬ እንደነጠቀኝ አውቃለው፡  የምወዳቸውን ነገሮች በግዴለሽነቴ ጠልቻቸዋለው።የሚስበኝና የምፈልገውን እንኳን መለየት ተስኖኛል ለምን እንደሆነ ግን አላውቅም...

ስራ ብዙም እንደማትገባ ጓደኞችህንም እንደራቅካቸው ማስጠንቀቅያ እንደተጻፈብህና ብዙ ብዙ ሰምቻለው  ለምን እንደዛ ታደርጋለህ...ለምን? የምጠብቅህኮ እንደዚህ አልነበረም?....አይኖቿ እንባ አቀረሩ.........(ልቤን ፍርሃትና እዝነቷ ወጠሩት....ተመለከትኳት)

"አለመኖሩ ውስጥ ለሚኖር ሰው ነገኮ ዓውድ አልባ ነው።" እኔኮ ካንቺ ነፍስ ጋር አብሬ ጠፍቻለው።ስንለያይ ነበር የተከተልኩሽ... የህወቴን ጣዕም ማጣትና ናፍቆትሽ እየበረዙት መኖር ውሏ ሲጠፋብኝ ትናንትሽና ትናንቴኮ ነው እዚህ ያደረሰኝ።አግኝቼሽ የሚመጣውን ቀን ማየት ሲያቅተኝ ተመልሼ ባለፈው ውስጥ ስሆንኮ ነው የማገኝሽ አንቺን ላለመርሳትኮ ነው ምርጫዬ ያ የሆነው...እርግጥ አዎ እኔምኮ ጥሩ ደረጃ መድረስ እፈልጋለው....የተሳካለትና ትልቅ ቦታ የሚደርስ ሰው. እንደዛ መሆንን እሻለው....
የሆነው ሆኖ
'ዛሬ ስላገኘውሽ ግን ደስ ብሎኛል።'
'እኔም እንደዛው'አለች ኪሴ ውስጥ ያለውን እጄን እያቀፈች
'እንዴት መጣሽ?'......
'ስላለፈው ላላወራህ ግን ትናንታችንን ወደ ነገ ልወስደው'
'ለመሄድ የሚሰማኝን በምን ታውቂያለሽ'
'ዘወትር ድርጊትህ ስለሚነግረኝ'
'አንቺንስ በምን ላውቅሽ እችላለው'

(ግንባሮቿ ግንባሬ ላይ ናቸው)
'የመጣሁት አንተነትህ ናፍቆኝ፤መኖር አምሮኝ እንጂ እንድዋሽህ የሚያስገድደኝ አንዳች ነገር ስለሌለ.....ከራሴ ጋር መጣላትና መወሻሸት ስለሰለቸኝ፤ከዚህ በላይ ናፍቆትህን መሸከም ስላቃተኝ ካንተ ጋር መኖርን ስለጓጓው.....ለዛ ነው የመጣሁት።
'ምንም ላደርግልሽ አልችልም.......ግን ቀሪ ዘመኔን ስንከባከብሽ ልኖር ቃሌን እሰጥሻለው......በሚንቀጠቀጡት ትንፋሾቿ መሃል በቅጽበት የሚያሳሱት ከናፍሮቿን አገኘዋቸው..........

"የማልወደውን የሆንኩት የወደድኩትን ባለመሆኔ ነው አሁን ግን የምወደውን ሆኛለው።"

"የተሻለ ነገር ያለው ወደ ፊት እንጂ ወደ ኋላ አይደለም።"

...... #Jo_ሊ

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

26 Apr, 18:49


🧑‍🦯

የሆነ ቀን ላይ ፍቅር ላንተ ምንድነው አለችኝ....በጥያቄዋ ውስጥ ያሰብኩት #እሷን ነበር:: ፍቅር ለኔ አልኳት ፈገግ አልኩላትና አዎ አለች ትኩር ብላ እያየችኝ... ያንቺ ድምጽ፣ያንቺ ሳቅ፣ያንቺ ውብ ገጽታ.....እነዚህን ሁሉ ሳይና ስሰማ ኢሄ ነው ለኔ ፍቅርና እውነተኛ ፍቺው።

@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

25 Apr, 17:20


"ለካስ ደስታም ሲያልፍ ህመም ይሆናል።''

ትዝታዬ እሷ ውስጥ ሰጥሟል እሷነቷ ዘመኔን የደበቅኩበት ባህር ነው።ትናንታችን ያለፈ ሳይሆን ገና እንደሚመጣ ተስፋ በልቤ ተሞንጭሯል።በመቅረት ውስጥ መዘውተርን ማሰብና ማለም በጊዜ ካብ ውስጥ ያሰሩኝ የምናብ ቤቴ ናቸው።በነበረችኝ ጊዜ ያለኝ ደስታ የቀረች እለት እንደ በረዶ ሟምቶ በሃዘን ኮሰመነ።ፈገግታዬ ተሰብሮ እንዳረጀ መስታወት በናፍቆት ተኮራምቶ  ደበዘዘ።

ለካስ እንባና ሳቅ ልክ እንደ ነፍስና ስጋ የተቆራኙ ናቸው።ሲያድር አንዱ ለአንዱ ገጹን ይቀይር ኖሯል.......ሀሴት ያደረግኩባቸው ቀናቶች የሚፈጥሩብኝ  ህመም የህይወት አቅጣጫዬን ወደ ገሃነም ወረወሩት።
የሄደች እለት ነበር ራሴን መሆን ያቃተኝና አዲስ በማልወደው ሰው የተተካውት።የሄደች ግን ያለች እንደ ጨረቃ ያለፈ ብርሃኗ የሚታየኝ ግን ለመንካትና፣ለመዳሰስ ደግሞ ያልታደልኳት ተፈጥሮዬ ናት።የኔ አለም ኢሄው ነው እምኖረውም እሷነቷ ውስጥ ያለውን እኔነቴን ስፈልግ ነው.........

...#Jo_ሊ

#share and #Join it
@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn

እኔና አንቺ

24 Apr, 14:50


ልጅ አባቱን " ፕሬዝዳንትማለትት ምን ማለት ነው? " ብሎ ይጠይቃል።
አባት: _ " ፕሬዝዳንት ማለት መሪ ማለት ነው። አሁን ለምሳሌ እኔ የዚህ ቤት ፕሬዜዳንት ነኝ።" ብሎ ይመልስለታል።
ልጅ ጥያቄውን አላቆመም።
ልጅ:_ " እናቴስ ምንድን ናት?"
አባት:_ " እናትህ ገንዘብ ሚኒስቴር ናት።"
ልጅ:_ " አያቴስ?"
አባት:_ " አያትህ ሰላይ ናት።"
ልጅ አሁንም ጥያቄውን ቀጠለ " እኔስ ምንድን ነኝ?"
አባት:_ " አንተ ህዝብ ነህ።" ብሎ ይመልስለታል።
በሌላ ጊዜ አባት ስራ ሄዶ መኖሪያ ቤታቸው ሌላ ሰው ይመጣል። ከዛም
ልጅ ተደብቆ አባቱ መስሪያቤት ይደውልና ምን ቢል ጥሩ ነወ?
.
.
.
.
" ሄሎ አባየ! ትሰማኛለህ? እቤታችን ሌላ ፕሬዝዳንት መጥቷል፣ ገንዘብ
ሚኒስቴር ሽር ጉድ እያለ ነው፣ ሰላይ ያንቀላፋል፣ ህዝብ ግን ተጨንቋል።ድረስ🧑‍🦯🧑‍🦯😄

√ √ √ √ #join and share
@fikrhn
@fikrhn
@fikrhn