ውድ “የእናት ባንክ መላ” የሬድዮ ፕሮግራም ተከታታዮች፣
ሰላም በያላችሁበት!
የእናት ባንክ መላ የሬድዮ ፕሮግራም፣ አስተማሪ፣ አነቃቂና የስኬት መንገዶች በስፋት የሚዳሰሱበትን ፕሮግራም ለናንተ ለውድ ተከታታዮቹ ማድረሱን ቀጥሏል።
በዛሬው ፕሮግራማችን፣ በትርታ ሬድዮ 97.6 ላይ የህይወት ተሞክሯቸውን ያካፈሉን የኤሌክትሪካል ኢንጂነር ምሩቅ የሆኑት እንዲሁም በመልካም ስራቸው የሚታወቁት አቶ ታምሩ ታደሰ ይባላሉ። የአሎ ቡና (ALO COFFEE) ድርጅት ባለቤት እና ስራስኪያጅ ሲሆኑ፣ የእናት ባንክ ሲልቪያ ፓንክሪስት ሰንጋተራ ቅርንጫፍ ደንበኛ ናቸው።
ድርጅታቸውን ልዩ የሚያደርገው ነገር እንዳለ ይገልጻሉ አቶ ታምሩ፣ እሱም ብዛት ሳይሆን ጥራት ላይ እናተኩራለን ይሉናል። ኢትዮጵያ ላይ በተለምዶ የሚሰሩ ሰዎች ዘንደሮ 1 ሚልዮን ዶላር አተረፍን የሚቀጥለው ሁለት ሶስት አመት እንዴት እንደሚጨምሩ ያስባሉ ነገር ግን እኛ ጥራቱን ነው የምናየው የምናረጋግጠው ቀጥሎ ዋጋው ይመጣል በማለት ያጋሩናል።
ውድ አድማጮቻችን፣ “ወለድ ከፍዬ እንደምበደረው ፊል አድርጌ አላቅም እና የሆነ የራሴን ብር ከዛኛው ኪሴ ላይ ያለውን ወስጄ እዚህ ኢንቨስት እንደማደርገው ነው” የሚሉት አቶ ታምሩ ከባንኩ ጋር ያላቸውን አጋርነት፣ ያሳለፉትን መንገድ፣ ከእናት ባንክ ጋር ያገናኛቸውን አጋጣሚ እና ከዚያ ብኋላ ያለውን ስኬታቸው እንደሚከተለው በማቅረብ፣ እንድትከታተሉ እንጋብዛለን።
ከአቶ ታምሩ ጋር የተደረገ ቃለመጠይቅ ሁለቱነም ክፍል ከታች ባለው ሊንክ እንሆ!
https://t.qrjp.net/89eh