Amhara Region revenue bureau

@bureauof


Amhara region revenue bureau Main office

Amhara Region revenue bureau

22 Oct, 06:23


"ቴክኖሎጅው የግብር ከፋችን እንግልት በማሰቀረት ገቢ አሰባሰቡን የሚያሰድግ ነው" አቶ ክብረት ማህሙድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ
ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ እያስለማ ያለውን የኤሌክትሮኒክስ ታክስ አስተዳደር ስርዓት (eTAS) ፕሮጀክት የሙከራ ትግበራ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት፤ የፕሮጀክት ቡድኑ፤ የያያ ክፍያ ስርዓት አ.ማ፣ የባንክ ተወካዮች፣ የዞን እና ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊዎች እና ሌሎች አጋር አካላት በተገኙበት ጥቅምት 09 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ አስጀምሯል፡፡

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ክብረት ማህሙድ ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለፁት ያለው የታክስ አስተዳደር ስርዓት ኋላ ቀር እና ከወረቀት አሰራር ያልወጣ በመሆኑ ለታክስ መጭበርበር እና ስወራ የመዳርግ እድሉ ከፍተኛ ነበር ብለዋል፡፡

ይህ ቴልኖሎች ግብር ከፋዮች ከእንግልት እንዲወጡ፤ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ እና የሚሰበሰበው ገቢ በትክክትል ለመንግስት እንዲደርስ በማድረግ የገቢ አሰባሰቡን የሚያሳድግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ ሶስት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ሲጠናቀቅ ከከፍተኛ ግብር ከፋይ እስከ እርሻ ግብር ከፋያችን የሚያስተናግድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ የሙከራ ትግበራው በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በሚገኙ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ላይ ነው ብለዋል፡፡

“ዘመኑ የቴክኖሎጅ እና የተሻለ መረጃ ያለው ጌትነትን የሚያገኝበት ጊዜ በመሆኑ ተቋማት አሰራሮችን በቴክኖሎጅ በማስተሳሰር አገልግሎት ሊሰጡ ይገባል” ሲሉ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳነት መንገሻ አየነ (ዶ.ር) ተናግረዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲያችን ከሚሰራቸው ዋና ዋና ስራዎች ውስጥ የማህበረሰብ አገልግሎት በመሆኑ የክልሉን ገቢ የሚሰበስበውን የክልሉን ገቢዎች ቢሮ በቴክኖሎጅ ማዘመን መልካም ተግባር እንደሆነ ተናግረው ሌሎችም ተቋማት በሀገር ውስጥ ባለሙያ የሚበለፅግን ቴክኖሎጅ መጠቀም እንዲጀምሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የያያ ክፍያ ስርዓት አ.ማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ አምደፅዮን ጋሻው እንደገለፁት ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ለመክፈል ወረፋ እና እንግልት በመቀነስ ቤታቸው ሆነው በማንኛው ሰዓት እንዲፈሉ በማድረግ ለኢኮኖሚ እድገት አስተዋፅኦ ማበርከት እና የክፍያ ሂደቶችን ለማቅለል ድርጅታቸው እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የሙከራ ትግበራዎን ተግባራዊ ለሚያደርጉ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ እና ለክፍለ-ከተማ ባለሙያዎች ስለ ቴክኖሎጅው አጠቃቀም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

ዘጋቢ፡- ሲሳይ አስማማው
ካሜራ ባለሙያ፡- ማስተዋል ሁነኛው

መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉ፡-
ፌስ ቡክ፡-https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- https://t.me/bureauof
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
በገቢያችን ተቴሌቪዥን ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 5:30 እስከ 6:00 እና
ሳምንታዊ የገቢዎች ቢሮ የሬድዮ ፕሮግራም ዘወትር እሁድ ከቀኑ 10:10 እስከ 10:40 በአማራ ራዲዮ እና ኤፍኤም 96.9 ይከታተሉን።
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ

Amhara Region revenue bureau

22 Oct, 06:22


"ቴክኖሎጅው የግብር ከፋችን እንግልት በማሰቀረት ገቢ አሰባሰቡን የሚያሰድግ ነው" አቶ ክብረት ማህሙድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ
ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)

Amhara Region revenue bureau

22 Oct, 06:19


"በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ያፈልጋል" አቶ አበባየሁ ሞገስ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም (ደብረብርሐን ከተማ ገቢዎች መምሪያ)

የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከመምሪያ እና ከክፍለ-ከተማ ለተውጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል፡፡

በስልጠናው የመምሪያው የገቢ አሰባሰብ ስራ ሂደት አስተባባሪዎች፣ የክፍለ-ከተማ የገቢ አሰባሰብ ቡድን መሪ፣ የአወሳሰን ባለምያ፣ ታክስ ሂሳብ ሰራተኛች፣ ገንዘብ ያዥ እና ተጨማሪ እሴት ታስክ “ዊይዝሆልዲንግ” ባለምያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የደብረብርሐን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አበባየሁ ሞገስ በመክፈቻ ንግገራቸው እንደገለፁት ባለሙያዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ መምሪያው ለባለሙያዎቹ በአዋጆች፣ ደንቦች፣ በመሪያዎች እና አሰራሮች ዙሪያ ግንዛቤ ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት በቀጣይ ከሰልጣኞች እንደሚጠበቅ አቶ አበባየሁ አሳስበዋል፡፡

ስልጠናው የስራ ግብር፣ ኪራይ ገቢ ግብር፣ ንግድ ትርፍ ግብር፣ የካፒታል ሀብቶች ማስተላለፍ፣ ታክስ የቅጣት አነሳስ፣ ታክስ የቅጣት አወሳሰን እና የክፍያ ግዜ ገደብ አሰጣጥ መመሪያዎች ላይ መሠረት ያደረገ እንደነበር ከመምሪያው ማህበራዊ ድረ-ገፅ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
መረጃው የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ነው፡፡
መረጃዎችን በሚከተሉት አማራጮች ይከታተሉ፡-

ፌስ ቡክ፡-https://www.facebook.com/AmraNews
https://www.facebook.com/profile.
በቴሌግራም:- https://t.me/bureauof
በዩትዩብ:- https://www.youtube.com/ ገቢያችን
በገቢያችን ተቴሌቪዥን ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 5:30 እስከ 6:00 እና
ሳምንታዊ የገቢዎች ቢሮ የሬድዮ ፕሮግራም ዘወትር እሁድ ከቀኑ 10:10 እስከ 10:40 በአማራ ራዲዮ እና ኤፍኤም 96.9 ይከታተሉን።
እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በ 9504 ይደውሉ

Amhara Region revenue bureau

22 Oct, 06:19


"በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ያፈልጋል" አቶ አበባየሁ ሞገስ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም (ደብረብርሐን ከተማ ገቢዎች መምሪያ)

Amhara Region revenue bureau

21 Oct, 08:38


በሩብ ዓመቱ 12 ቢሊየን ብር ተሰበሰበ
ጥቅምት 11/ 2017 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)

ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት ከመደበኛ እና ከከተማ አገልግሎት ገቢ በድምሩ 71.65 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ዐቅዶ ከሐምሌ 01/2016 እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ባሉት ሦስት ወራት ከመደበኛ ገቢ ብር 11.1 ቢሊየን ወይም 19.8 በመቶ እና ከከተማ አገልግሎት ገቢ ብር 939.8 ሚሊየን ወይም 6.06 በመቶ በድምሩ 12 ቢሊየን ብር ወይም 70 በመቶ (ከሩብ ዓመቱ አንጻር) አሳክቷል።
አፈጻጸሙ በ2016 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ4 ቢሊየን ብር ብልጫ እንዳለው አቶ ጥላሁን ጀንበሩ የገቢ ዕቅድና ጥናት ደጋፊ ስራ ሂደት አስተባባሪ ቅዳሜ ጥቅምት 09/2017 ዓ.ም በተካሄደው ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ባቀረቡት መረጃ አብራርተዋል።
አቶ ክብረት ማህሙድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ባስተላለፉት መልዕክት በ2016 በጀት ዓመት በችግር ውስጥ የተሰራን ተግባር እንደ ተሞክሮ በመውሰድ ዘንድሮ በ100 ሺህ የሚቆጠሩ ግብር ከፋዮች አሳውቀው ባልከፈሉበት ሁኔታ እና ያለውን ወቅታዊ ችግር በመቋቋም የተሰራው ስራ አበረታች ነው ብለዋል።
ኮዘኖች ደቡብ ወሎ ዞን ገቢዎች መምሪያ ለገቢ ጽ/ቤቶች በየቀኑ ግብረ-መልስ በመስጠት፣ ሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ገቢዎች መምሪያዎች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ስለሰሩ የተሻለ ገቢ ሰብስበዋል።
ከከተሞች የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የዕቅዱን 20 በመቶ በመሰብሰብ በአንደኝነት እየመራ ሲሆን በቀጣይ ጊዜ ሌሎች መምሪያዎች የተሻለ ፈፅመው የክልሉን ህዝቦች የልማት ጥያቄ መመለስ የሚችል ገቢ መሰብሰብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ ቢሮ ሃላፊውን ጨምሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊዎች፣ 22ቱ መምሪያ ሃላፊዎች፣ የቢሮው ዳይሬክተሮች፣ ታክስ አማካሪዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ:- ደሴ ገላው
ካሜራ ባለሙያ:- ማስተዋል ሁነኛው

Amhara Region revenue bureau

18 Oct, 08:19


የጥሬ ገንዘብ አሰባሰብ በባንክ ብቻ ...

Amhara Region revenue bureau

17 Oct, 12:17


ለግብር ትምህርትና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች ሙያዊ ሥልጠና ተሰጠ
ባህር ዳር ጥቅምት 07/2017 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)

በአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዋና ስራ ሂደት ለባለሙያዎቹ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ዝግጅት፣ የዜና አጻጻፍ፣ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ከጥቅምት 6 እስከ 11 2017 ዓ.ም ሙያዊ ስልጠና እየሰጠ ነው።

አቶ ግርማው ታደግ በአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የዜናና ወቅታዊ ጉዳዮች ዝግጅት አስተባባሪ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ዝግጅትና የዜና አጻጻፍ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዬችን አስመልክተው ስልጠና ሰጥተዋል።

ሥልጠናው የገቢ ተቋሙ ባለሙያዎች በሚዲያ ተቋማት የሚሰጡትን የግብር ትምህርትና ተግባቦት ስራ ለመስራት ግልፅና አጭር ዜና እንዴት መስራት እንዳለባቸው በተግባር ልምምድ አድርገዋል። በቀጣይም ማራኪና ተነባቢ የሆኑ መረጃዎችን ለተደራሲያን ለማድረስ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

ዘመኑ ያፈራው ማህበራዊ መገናኛ ዘዴ አማራጭ መውጫ በር በመሆኑ ባለሙያዎች ለሚሰሩበት ተቋም ወይም በግላቸው ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ዩቲዩብ፣ ቲክቶክ፣ ኢንስታግራም እና ሌሎች አገልግሎቶችን በመጠቀም በርካታ ስራዎችን ለማሳለጥ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ተገልጧል።
በስልጠናው የክልል፣ የባህር ዳር ከተማ ገቢዎች መምሪያ እና የክፍለ ከተሞች ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የቢሮው የግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ታዘባቸው ጣሴ የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ ሥራውን በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ መስራት ይገባል ። ወደ ሂደቱ የሚቀላቀሉ ባለሙያዎች የኮሙዩኒኬሽን ሙያ እንዲኖራቸው በማድረግ ጠንካራ ባለሙያ ለመፍጠር መሰራት አለበት ብለዋል።

ዳይሬክተሩ አያይዘውም እንደገለፁት አቅም በፈቀደ መጠን በቀጣይም ተመሳሳይ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የተሻለ ባለሙያ ለመፍጠር ጥረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ ዘለዓለም ጸጋ
ካሜራ ባለሙያ ማስተዋል ሁነኛው

Amhara Region revenue bureau

17 Oct, 12:17


ለግብር ትምህርትና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች ሙያዊ ሥልጠና ተሰጠ
ባህር ዳር ጥቅምት 07/2017 ዓ.ም (አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ)