የአዊ ብሄ/አስ ብልፅግና ፓርቲ የስልጠና መርሃ -ግብር በእንጅባራ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
የስልጠና መርሃግብሩ " የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት " በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተሰጠ የሚገኘው።
በብልጽግና ፓርቲ የአዊ ብሄ/አስ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ሰውነት፥ የስልጠናው ዓላማ የአመለካከት እና የተግባር አንድነትን በማጎልበት፣ የመሪዎችን ሁለንተናዊ አቅም በመገንባት የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በችግር ውስጥም ሆኖ ስኬቶችን እያስመዘገበ ያለ ፓርቲ እንደሆነ አቶ አለሙ ተናግረዋል ።በ2016 ዓ.ም የተሰጠውን ስልጠና የሚያጠናክር ለመዋቅሩ በተደራጀ ሁኔታ ስልጠና እየተሠጠ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተሰጡት ስልጠናዎችም ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተዋል።ህልመኞች ሀገር ያሻግራሉ፣ ህልመኞች ስንሆን ያለንን ፀጋ እንረዳለን፣ሀገር ስለመገንባትና ህዝብ ስለመለወጥ እናስባለን ነው ያሉት ሀላፊው።አሁናዊው ትንቅንቅ የፖለቲካ አውድ ሳይበግረን ህልማችንን ለማሳካት የተስፋ ስንቅ የሚጨበጥበት መድረክም እንደሆነ አመላክተዋል።
ስልጠናው ሰላም እና መረጋጋት የምንፈጥርበት፣ በልማት እና በመልካም አስተዳደር የገጠመንን ስብራት የምንጠግንበት ትልቅ መድረክም እንደሆነ ተናግረዋል።
የአዊ ብሄ/አስ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው እንደገለፁት ስለነገ መዳረሻችን የምናስብ ከሆነ የጋራ የተግባባ ህልም ያስፈልገናል ብለዋል።ለዚህ ደግሞ ከአምና ዘንድሮ መሻሻል ያለው የትርክት እምርታ(ሪፎርም) እንደሚያስፈልግ አስገንዘበዋል ።በስልጠናው የውስጣችንን ልዩነት በማጥበብ እና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የምናጠናክርበት ነው ብለዋል።
የስልጠናው ግብ ጠንካራ ፓርቲ መፍጠር፣ የተጀመረውን ሪፎርም መሬት ማስነካት፣ የፓርቲውን እሳቤ እና ፍላጎት መረዳት እና መገንዘብ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አያይዘውም ጠንካራ ተቋማት መገንባትእና መሪዎች በሥነ ምግባር ተምሳሌት ልንሆንም ይገባናልም ብለዋል፡:
የአማራ ክልል ምክር ቤት መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አየን ብርሃንአቶ አየን ብርሃን ባስተላለፍት መልዕክት ብልፅግና ፓርቲ በችግር ውስጥም ሆኖ የስኬቶች ባለቤት እንደሆነ ገልፀዋል። ሀገርን ለማሻገር የሚያስችሉ የተለያዩ ሴኬታማ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ስልጠናው አመራሩ ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመለካከት ጥራት ግንዛቤ የሚፈጥር እና አሁን ለገጠሙን የሰላም እጦት ችግሮቻችን መፍትሄ የሚቀመጥበት እንደሆነም ተናግረዋል። የገጠምንን የፖለቲካ እና የሰላም ስብራት የሚጠግን እና አቅም የሚፈጥር በመሆኑ ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
የአሁኑ ስልጠና አምና ላይ" ከእዳ ወደ ምንዳ "በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ቀጣይ የስልጠና ክፍል ነው።
Awi communication
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/@amharacommunication
Website: https://www.amharacomm.gov.et
የስልጠና መርሃግብሩ " የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት " በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተሰጠ የሚገኘው።
በብልጽግና ፓርቲ የአዊ ብሄ/አስ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ሰውነት፥ የስልጠናው ዓላማ የአመለካከት እና የተግባር አንድነትን በማጎልበት፣ የመሪዎችን ሁለንተናዊ አቅም በመገንባት የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በችግር ውስጥም ሆኖ ስኬቶችን እያስመዘገበ ያለ ፓርቲ እንደሆነ አቶ አለሙ ተናግረዋል ።በ2016 ዓ.ም የተሰጠውን ስልጠና የሚያጠናክር ለመዋቅሩ በተደራጀ ሁኔታ ስልጠና እየተሠጠ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በተሰጡት ስልጠናዎችም ለውጦች መመዝገባቸውን አንስተዋል።ህልመኞች ሀገር ያሻግራሉ፣ ህልመኞች ስንሆን ያለንን ፀጋ እንረዳለን፣ሀገር ስለመገንባትና ህዝብ ስለመለወጥ እናስባለን ነው ያሉት ሀላፊው።አሁናዊው ትንቅንቅ የፖለቲካ አውድ ሳይበግረን ህልማችንን ለማሳካት የተስፋ ስንቅ የሚጨበጥበት መድረክም እንደሆነ አመላክተዋል።
ስልጠናው ሰላም እና መረጋጋት የምንፈጥርበት፣ በልማት እና በመልካም አስተዳደር የገጠመንን ስብራት የምንጠግንበት ትልቅ መድረክም እንደሆነ ተናግረዋል።
የአዊ ብሄ/አስ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው እንደገለፁት ስለነገ መዳረሻችን የምናስብ ከሆነ የጋራ የተግባባ ህልም ያስፈልገናል ብለዋል።ለዚህ ደግሞ ከአምና ዘንድሮ መሻሻል ያለው የትርክት እምርታ(ሪፎርም) እንደሚያስፈልግ አስገንዘበዋል ።በስልጠናው የውስጣችንን ልዩነት በማጥበብ እና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የምናጠናክርበት ነው ብለዋል።
የስልጠናው ግብ ጠንካራ ፓርቲ መፍጠር፣ የተጀመረውን ሪፎርም መሬት ማስነካት፣ የፓርቲውን እሳቤ እና ፍላጎት መረዳት እና መገንዘብ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አያይዘውም ጠንካራ ተቋማት መገንባትእና መሪዎች በሥነ ምግባር ተምሳሌት ልንሆንም ይገባናልም ብለዋል፡:
የአማራ ክልል ምክር ቤት መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አየን ብርሃንአቶ አየን ብርሃን ባስተላለፍት መልዕክት ብልፅግና ፓርቲ በችግር ውስጥም ሆኖ የስኬቶች ባለቤት እንደሆነ ገልፀዋል። ሀገርን ለማሻገር የሚያስችሉ የተለያዩ ሴኬታማ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ስልጠናው አመራሩ ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመለካከት ጥራት ግንዛቤ የሚፈጥር እና አሁን ለገጠሙን የሰላም እጦት ችግሮቻችን መፍትሄ የሚቀመጥበት እንደሆነም ተናግረዋል። የገጠምንን የፖለቲካ እና የሰላም ስብራት የሚጠግን እና አቅም የሚፈጥር በመሆኑ ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
የአሁኑ ስልጠና አምና ላይ" ከእዳ ወደ ምንዳ "በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው ቀጣይ የስልጠና ክፍል ነው።
Awi communication
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/@amharacommunication
Website: https://www.amharacomm.gov.et