"""""""""""""""""""""""""""
ታዋቂው ዳዒ ዐምር ኻሊድ እንዲህ ይላል - በአንድ ወቅት ከሆኑ ወጣቶች ጋር ተቀማምጠን ሳለን እንደዋዛ የአላህን (ሱ.ወ.) ፀጋዎች መቁጠር ጀመርን፡፡ የትኛው ፀጋ እንደሚበልጥም አወጋን፡፡
~ ከኛ መካከል አንዱ ‹ጤና ነው› ሲል
ተናገረ፡፡
~ ሌላኛው ‹ልጆች ናቸው› አለ፡፡ ሌላው ‹ማየትና መስማት መቻል ነው› አለ፡፡
~ ‹ትልቁ ፀጋ እናቴ ናት› ያለም አለ፡፡
~ እንዲሁ ‹ሀብት የሠጠኝ ጌታ በርግጥም ትልቁን ፀጋ ሠጠኝ› ያለም ነበር፡፡
~ ‹እስልምና ነው› ያለም አለ፡፡
~ ከመካከላችን አንድ የአሥራ ስምንት ዓመት ወጣት ግን አላህ (ሱ.ወ.) ከሠጠን ፀጋዎች ሁሉ ትልቁ ፀጋ ‹ጌታችን ጌታችን መሆኑ ነው፡፡› አለ፡፡ ትርጉሙ ምን ማለት ይሆን? ይህ ታዳጊ ወጣት በዚህች ዓለም ላይ ትልቁ ፀጋ ጉዳያችን ይዞ ያለው አላህ (ሱ.ወ.) መሆኑ ነው ማለቱ ነው፡፡ እሱ ነው ዋስትናችን፡፡ ልባችንን፣ እጃችንን፣
ግንባራችንን… ሁሉ ነገራችን ይዞ ወደ መልካም ነገርና ወደ ስኬት የሚመራን አላህ ነው፡፡ ትልቁ የአላህ ፀጋ አላህ አላህ መሆኑ፣ አላህም ጌታችን መሆኑ ነው፡፡ ጥራትና ልዕልና የተገባው ይሁን፡፡ በአላህ ጌትነት ወደድን፣ መልዕክተኛው ነቢያችን መሆናቸውን ወደድን፣ እስልምናን በሃይማኖት በኩል ወደድን፡፡
አላህ (ሱ.ወ.) ለሚወደውም ለማይወደውም ሀብት ይሠጣል፡፡ አላህ ላመነበትም ለካደዉም ገንዘብ ይሠጣል፡፡ ጤና፣ ቤትና ንብረት ይሠጣል፡፡ እስልምናን ግን የሚሠጠው እርሱ ለወደደው ሰው ብቻ ነው፡፡ ወደ መንገዱ የሚመራው ራሱ የመረጠውን ሰው ነው፡፡ ስለዚህ ሙስሊም መሆን መመረጥ ነው፡፡ ሙስሊም
መሆን መብለጥ ነው፡፡ ሙስሊም መሆን መወደድ ነው፡፡ ባይወደን ኖሮ መቼ ይሠጠን ነበር፡፡ አላህ ወዶን እስልምናን
ሠጠቶናልና ክብር ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ይሁን፡፡ አላህ እኔ፣ አንተና አንቺ ግን ሳንለምነው፣ ሳንማፀነው ፣ ሳንወተውተው ሙስሊም አደረገን። ለኢብራሂም (ዐ.ሰ.) አባት ፣ ለኑሕ (ዐ.ሰ.) ልጅ፣ ለሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ.) አጎት ያልሰጠውን ፀጋ ሠጠን፡፡ አላህ እስልምናን ሠጠን፡፡ አምላካችን ንፁህ የተፈጥሮ ሃይማኖትን ለገሰን፡፡ እንደ እስልምና ምን ገር የሆነ ሃይማኖት አለ፡፡ ለመረዳትም ሆነ ለትግበራ አይከብድም፡፡ ይህ በርግጥም ትልቅ ችሮታ ነው። አላህ የትላልቅ ችሮታዎች ባለቤት ነው። እርሱ ችሮታውን
ለሚሻው ሰው ብቻ ይሠጣል። ነገርግን ብዙዎች አላህ የሠጣቸውን ፀጋ አያስተውሉም ፤ አያስተነትኑም ፤ አስተንትነውም
አያመሰግኑምም፡፡ የእስልምና ፀጋ ከየትኛውም ፀጋ ሁሉ የላቀ ነው፡፡ ቢመዘን ቢለካ የትኛውም ፀጋ አይደርስበትም። ምስጋና ወደቀናው መንገድ ለመራን ጌታ ይሁን። እሱ ባይመራን ኖሮ ባልተመራን ነበር።
"እስልምናን ለሰጠን አላህ ምስጋና ይገባው" በሉ።
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️