ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

@jeilumedia


የጄይሉ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com
Telegram: https://t.me/Jeilumedia
E-mail: [email protected]
Subscribe: https://www.youtube.com/c/JeiluTube/videos
t.me/Jeilumedia

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

22 Oct, 13:51


የእሳት አደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ።

ጄይሉ ቲቪበመርካቶ ሸማ ተራ የደረሰውን የእሳት አደጋ መንስኤ እየመረመረ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ

ጄይሉ ቲቪ ፣ ጥቅምት 12፣ 2017 ትናንትና ምሽት በአዲስ አበባ አዲስ ክፍለ ከተማ መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ባጋጠመ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ፖሊስ አስታውቋል።

የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩ ተጠቁሟል፡፡

አደጋውን ለመከላከልና በአደጋው ምክንያት ሌላ ወንጀል እንዳይፈፀም እንዲሁም የአደጋ ተከላከይ ሠራተኞች ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ርብርብ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሠላምና ፀጥታ መዋቅር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ተቋማት አደጋው እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው ነው የተገለጸው፡፡

አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ÷ ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ላይ ቀላል በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱንም አመልክቷል፡፡

አደጋውን ለመከለከል የፀጥታና ሌሎች ተቋማት እንዲሁም የአካባቢው ሕብረተሰብ ላደረገው ድጋፍና ተባባሪነት ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በደረሰው የእሳት አደጋ የተሰማውን ሃዘን ገልፆ፥ ወደፊት በምርመራ የደረሰበትን ውጤት ለህዝብ እንሚያሳውቅም በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
ኤፍ ቢ ሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 19:45


"ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጅት አቅም አላት !"

ጄይሉ ቲቪኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት አቅም አላት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራት አመት በኋላ የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀትም በይፋ ለካፍ ጥያቄ አቅርበዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 19:19


መርካቶ ሸማ ተራ በእሳት እየነደደ ነው

ጄይሉ ቲቪበመርካቶ ሸማ ተራ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017  በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ መርካቶ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳሉት÷እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳት የአደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችና ባለሞያዎች በስፍራው ተሰማርተዋል፡፡

የእሳት አደጋውን መንስዔና ያደረሰውን ጉዳት ምርመራ ከተጣራ በኋላ እንደሚያሳውቁም ባለሞያው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር የእሳት አደጋና ስጋት መከላከል ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አደጋውን በፍጥነት ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ጥረት የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከንቲባ አዳነች በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናቸውንም ተናግረዋል፡፡

ኤፍቢሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 18:59


እስላማዊ ዩኒቨርስቲ በባሌ

ጄይሉ ቲቪበኢትዮጵያ የመጀመሪያው እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላይ ምክርቤቱ ፕሬዚደንት ተመርቆ ተከፈተ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጥቅምት 11ቀን 2017
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኾነውን የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መርቀው ከፈቱ።

በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን እና ከፍተኛ ዓሊሞች ተገኝተዋል።

የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መሥራችና ዋና አስተባባሪ ዶክተር ጀይላን ገለታ በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የዩኒቨርሲቲው መከፈት በአካባቢው ማኅበረሰብ የእስልምና እውቀት ላይ ትልቅ አሴት ይጨምራል ብለዋል።

የዩንቨርሲቲው መሥራች ለባሌ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መከፈት ከአካባቢው ማኅበረሰብና ከበጎ አድራጊዎች ትብብር ባሻገር መንግሥትም ትልቅ ድጋፍ በማደረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዩኒቨርሲቲው ምረቃ ላይ ሲናገሩ፣ ባሌ ሮቤ በኢትዮጵያ የእስልምና ትምህርት ላይ ትልቅ አሻራ ያሳረፈ የዓሊሞች መፍለቅያና ትልቅ ታሪክ ያለው አካባቢ መኾኑን ጠቅሰው፣ ይህን መሰል ዩኒቨርሲቲ መከፈቱ ለእስላማዊው ትምህርት ጥራት ትልቅ የብርሃን ጎዳና እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሁኑ ጊዜ 80 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው ይህ ዩንቨርሲቲ ከሃይማኖታዊ ትምህርት ባሻገር በተለያዩ የአካዳሚ ዘርፎች ትምህርት የሚሰጥበትና ማኅበረሰቡን የሚያገለግል በመኾኑ፣ ሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ዩኒቨርሲቲውን እንደ ሃብታቸው እንዲንከባከቡት ፕሬዚደንቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዚሁ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ምሥረታ ሂደት ላይ የተሳተፉትን የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናትን፣ እንዲሁም ዓሊሞችን አመሥግነዋል።

መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከሚያደርገው ጥረት አኳያ የዩኒቨርሲቲው መከፈት ለሀገር ትልቅ ዕድል መኾኑ የተጠቀሰ ሲኾን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሚቻለው ሁሉ ከዩኒቨርሲቲው ጎን ለመቆም ቃል ገብቷል።

•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 08:35


ፈቱላህ ጉለን ህይወታቸው ማለፉ ተገልጸ

ጄይሉ ቲቪእ.ኤ.አ. በ2016 በቱርክዬ በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት አቀናባሪ ናቸው በሚል ተጠርጥረው የነበሩትና መኖሪያቸውን አሜሪካ ያደረጉት ፌቱላህ ጉለን መሞታቸውን የቱርክ የህዝብ ቴሌቪዥን ዛሬ ዘግቧል።
@ጄይሉ ቲቪ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 08:24


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና አንቶንዮ ጉቴሬዝ

ጄይሉ ቲቪጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከተመድ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ ብለዋል፡፡

ዛሬ ማለዳ ዋና ፀሃፊውን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በተለያዩ ቀጣናዊ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል፡፡
ኤፍቢሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

20 Oct, 19:09


የዳሌ አጥንት ህክምና በወራቤ ሆስፒታል

ጄይሉ ቲቪበወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ (Total Hip Replacement ) ተጀመረ!

* ለሁለት ታካሚዎቸ የተሳካ የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ(Total Hip Replacement ) ማድረግ ተችሏል።

በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ (Total Hip Replacement) በንዑስ ስፔሻሊስት (Sub specialist) የተጀመረ ሲሆን የአጥንት ህክምና ስፔሻሊስት እና የቀዶ ህክምና ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር አብዶ ዳመስ በግራ ዳሌ የመበስበስ (osteonecrosis) ችግር ተጠቂ ለሆነ የ45 ዓመት እድሜ ያለው ታካሚ ሶስት ሰዓት የፈጀ ስኬታማ ውስብስብ ቀዶ ህክምና ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ከ6 ወር በፊት በግራ ዳሌ አንገት ስብራት ተጠቂ የሆነች የ50 ዓመት እድሜ ያላት ታካሚም እንዲሁ ሁለት ሰዓት የፈጀ ስኬታማ ቀዶ ህክምና እንደተደረገላት ዶ/ር አብዶ አክለዋል።

ታካሚዎቹ ከህክምና በኋላም በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ዳይሬክተሩ በቀዶ ህክምናው ለተሳተፉ የህክምና ባለሙያዎች በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

በሆስፒታሉ የአጥንት ህክምና ክፍል ላለፉት ዘጠኝ አመታት ከቀላል የአጥንት ህክምና ጀምሮ፣ ከአደጋ ጋር የተያያዙ የአጥንት ስብራቶች፣ ውልቃቶች እንዲሁም ከፍተኛ እና ውስብስብ ልዩ ልዩ የአጥንት ቀዶ ህክምናዎች እየተሰጡ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ይህም ለተመሳሳይ ህክምና የሚደረግ ሪፈራልን በማስቀረት ህብረተሰቡን ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ከመታደግ አንፃር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የሚገልጹት ዶ/ር አብዶ የህክምና ክፍሉ እንደ ሲ-አርም እና አርትሮስኮፕ (C-ARM, Arthroscope) ያሉ አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎችንና ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ ማሽኖችን በማስገባት አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም አስታውሰዋል።

ማህበረሰቡም ይህንን አውቆ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል ።