ጥራት ያለው የወተትና የእንቁላል ምርት ከገበያ ባነሰ ዋጋ ከእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል እያገኙ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ።
ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም (አ/አ/ከ/ግ/ል/ኮ)
የእንስሳት ልማት የልህቀት ማዕከል ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ማዕከሉ ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ በማቅረብ የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድ አወንታዊ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የማዕከሉ ኃላፊ ዶ/ር ፀጋ ለማ ገልፀዋል።
በማዕከሉ የከብት ማድለብ፣ የእንቁላል ዶሮ እርባታ እና የወተት ላም እርባታ እያከናወነ ሲሆን እንቁላል በ8 ብር፣ አንድ ሊትር ወተት በ75 ብር እና ሌሎች የእንስሳት ተዋጽኦ በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።
በማዕከሉ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን እየሸመቱ ያሉ ተጠቃሚዎች የእንቁላልና የወተት ምርት በገበያ ላይ ካለው ዋጋ ባነሰ እያገኙ መሆኑን የገለፁለት መሆኑን ማዕከሉ በይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ፔጃችን ላይ ገልፃል፡፡
የማዕከሉ ኃላፊ የእንስሳት ልማት ልህቀት ማዕከል ምርት ለገበያ በማቅረብ ገበያ ከማረጋጋት ባሻገር የልማት ተነሺ አርሶ አደሮችና ቤተሰቦቻቸው በ104 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ እንደሚገኙና በሌሎች የስራ ዘርፎችም ለበርካታ ነዋሪዎች የስራ እድል መፈጠሩን ኃላፊው ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ማዕከላትን በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት በከተማ አስተዳደሩ እቅድ እንደተያዘ የተናገሩት ዶ/ር ፀጋ ምርት ለነጋዴ እንዳይደርስ አሰራር ተዘርግቷል ሲሉ አስረድተዋል።
ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም (አ/አ/ከ/ግ/ል/ኮ)
የእንስሳት ልማት የልህቀት ማዕከል ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ማዕከሉ ጥራት ያለው የእንቁላልና የወተት ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ በማቅረብ የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድ አወንታዊ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የማዕከሉ ኃላፊ ዶ/ር ፀጋ ለማ ገልፀዋል።
በማዕከሉ የከብት ማድለብ፣ የእንቁላል ዶሮ እርባታ እና የወተት ላም እርባታ እያከናወነ ሲሆን እንቁላል በ8 ብር፣ አንድ ሊትር ወተት በ75 ብር እና ሌሎች የእንስሳት ተዋጽኦ በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚዎች እያቀረበ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።
በማዕከሉ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን እየሸመቱ ያሉ ተጠቃሚዎች የእንቁላልና የወተት ምርት በገበያ ላይ ካለው ዋጋ ባነሰ እያገኙ መሆኑን የገለፁለት መሆኑን ማዕከሉ በይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ፔጃችን ላይ ገልፃል፡፡
የማዕከሉ ኃላፊ የእንስሳት ልማት ልህቀት ማዕከል ምርት ለገበያ በማቅረብ ገበያ ከማረጋጋት ባሻገር የልማት ተነሺ አርሶ አደሮችና ቤተሰቦቻቸው በ104 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ እንደሚገኙና በሌሎች የስራ ዘርፎችም ለበርካታ ነዋሪዎች የስራ እድል መፈጠሩን ኃላፊው ጠቁመዋል።
ተጨማሪ ማዕከላትን በሌሎች ክፍለ ከተሞች ለማስፋፋት በከተማ አስተዳደሩ እቅድ እንደተያዘ የተናገሩት ዶ/ር ፀጋ ምርት ለነጋዴ እንዳይደርስ አሰራር ተዘርግቷል ሲሉ አስረድተዋል።