ለማንኛውም "ድነናል፣ እየዳንን ነው" እንድናለን የኛ እንጂ የኦርቶዶክስ ትምህርት አይደለም፤ እነሱ ቋንቋውን ተውሰው ያብራሩበት መንገድ ደሞ Weird የሚባል ነው/አለያም ይጋጭባቸዋል።
(ከታች የምለጥፈው ፎቶ የቤተክርስቲያኔ አስተምህሮ ነው፤ እንደ Reference ነው የተጠቀምኩት)
ይህንን አገላለጽ ለመቀበል የሚከብዳቸው ፕሮቴስታንቶች በሁለት ምክንያት ይተናነቃቸዋል፤ አንድም ስለ ነገረ ድነታችን በትክክል ካልተረዱ፣ አንድም ደግሞ አገላለጹ ወደ ሌላ bad theology ይወስዳል በማለት። ስለዚህ ጥቂት ነገሮችን Address ለማድረግ ልሞክር እስቲ፦
ነገረ ድነታችን በሶስት ዋና ሐሳቦች ላይ የተመሰረተ ነው እነሱም፦
1) ጽድቅ (Justification)
ይህ በጭራሽ፣ በምንም መንገድ፣ በየትኛውም ሁኔታ በእኛ የግብር መታዘዝ የሚገኝ ነገር አይደለም፤ ከጅምሩ ጽድቁ ራሱ የኛም አይደለም፤ በእምነታችን ምክንያት የክርስቶስ ጽድቅ ለእኛ ለሃጢአተኞቹ ተቆጥሮልን እንጂ! (ሮሜ ምእራፍ 4)። ስለዚህ ሰው ባመነበት ጊዜ ይህ የክርስቶስ ጽድቅ ለእርሱ ይቆጠርለታል፤ በልጁ ሞት ከእግዚአብሔር ጋር ይታረቃል፣ በትንሳኤው በማመኑ ሕያው ተብሎ ይጠራል። ይህንን ደሞ ድነናል ብለን በእርግጠኝነት እንናገረዋለን።
2) መቀደስ (Sanctification)
ይህንን definitive and progressive በማለት በሁለት ከፍለንም ማየት እንችላለን። Definitive sanctification አማኙ በክርስቶስ ባመነበት ጊዜ ከሃጢአት ሃይል ተፋቶ ከክርስቶስ ጋር አንድ የሆነበትን Status የሚያሳይ ሲሆን Progressive sanctification ግን ቀጣይነት ያለውና መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ከሚሰራው ስራ የተነሳ ክርስቶስን በመምሰል እለት እለት የምናድግበት Ongoing process ነው (ገላ 5:22-23)። በመቀደስ ውስጥ ከሃጢአት ጋር እስከ ጥግ ድረስ መታገልም አለ! በተረፈ በህብረትና በግል እንደ ቃሉ የምንኖራቸው ሁሉ (ቅዱሳት ምስጢራትን ጨምሮ) የዚህ Process identities ናቸው። ይህንን ደግሞ እየዳንን ነው በማለት እንጠራዋለን። እዚህ ጋር ጥንቃቄ የሚፈልገው ነገር ግን እየዳንን ነው ስንል በእምነት ባገኘነው ጽድቅ ላይ በመቀደስ ስራችን የምንጨምረው ነገር አለን እያልን አይደለም፤ የጸደቅንበት እምነት ሕያውና እውነተኛ መሆኑን እያስረገጥን እንጂ!
እንዲሁም የመቀደስ ዋናው አላማ (ultimate goal) መክበራችን (Glorification) መሆኑን አንረሳም።
እነሆ እየዳንን ነው!
3) መክበር (Glorification)
ይህንን "እንድናለን" ብለን እንገልጸዋለን፤ በክርስቶስ ዳግም መምጣት የምናገኘውን ክብር በተስፋ እንደምንጠብቀውና እስከዚያች ቀን ድረስ ያሳያል (ዕብ 10:36-39፣ 1ተሰ 4:13-18፣ 1ዮሃ 3:2)።
👉 ሰዎች ይህ ትምህርት ጥያቄ የሚሆንባቸው አንዱ ምክንያት እየዳንን ነው የሚለው አገላለጽ የገዛ ስራችንን አዋጥተን የምንገባበት ገነት እንዳለ የሚናገር ስለሚመስላቸው ነው፤ እንደ እውነቱ ግን በእኛ ስራ የዘለአለም ህይወት አላገኘንም፣ አናገኝም! የጸደቅንበት እምነት ግን የሚያፈራና እየተቀደስን የምንሄድበት ህያውና በመንፈስ ቅዱስ የሚያፈራ ነው። ፍሬው Progressively ካላፈራ እምነቱ የሞተ ስለሆነ ግን መቀደስ ግዴታ ነው። እየዳንን ነው ስንል ከሃጢአት Effects progressively እያመለጥንና ጌታን እየመሰልን መሄዳችንን ብቻ እያሳየን ነው፤ ማምለጥ መዳንም አይደል?😁
👉 እንድናለን ስንል ደግሞ ገና የሆነ ነገር ሰርተን ከጸደቅንበት እወነት የተሻለ Further ድነት እናገኛለን እያልን ሳይሆን ጌታን እየመሰልን ጸንተን በመጠበቅ የታሰበልንን የዘለአለም ተስፋ ጌታ ሲመጣ በሙላት እንወርሳለን፤ ከታላቁ ጥፋትም እንደ ወንጌሉ ቃል እውነት እናመልጣለን እያልን በእርግጠኝነት እያወጅን ነው።
በዚህ መልኩ ብትረዱት ጥሩ ነው ብዬ አምናለሁ።
https://t.me/hokhmahchristianstudies