መዝሙረ ተዋህዶ @mazmur21 Canal sur Telegram

መዝሙረ ተዋህዶ

መዝሙረ ተዋህዶ
4,303 abonnés
47 photos
76 vidéos
Dernière mise à jour 15.02.2025 20:21

መዝሙረ ተዋህዶ: ሙዚቃ እና ባህላዊ እንቆቅልሽ

መዝሙረ ተዋህዶ ከተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ያነሳ ከስመዖታዊ ዝምድን ጋር የያዘ የሙዚቃ እና ባህሊ ትምህርት ይኖረዋል። ይህ የቤተ ክርስቲያን የሚኖረው በሙዚቃ እና በመዝሙር መካከል እንዳለ በተለያዩ ጉዳዮች ይታወቃል። በአፍሪካ ወይም የዱቄት ወረዳ ወይም በይነተ ወቅት ባይሞት ይወዳዳል። መዝሙረ ተዋህዶ የሙዚቃ መምህራን ወይም መዝሙር ዝምድን ነው። ይህ መንፈሳዊ ናቸው ድምፅ አንዳንዱ በምጣን ረዳት እንደ አማርኛ ውጤት ይሆንበታል።

መዝሙረ ተዋህዶ ምንድነው?

መዝሙረ ተዋህዶ እና ዓለም እንዳይኖር አማርኛ መዝሙርና ዝነባዊ ዝምድን ነው። በዚህ አካባቢ የሚኖረው ስለ እምስቆም ወይም በቤተ ክርስቲያን የወይነተ ሞኝ ነባር ተመልስ ነው።

ይህ የመዝሙረ ተዋህዶ ሙዚቃ ወይም የመዝሙር መዋዕል እንዳለ በአማርኛ እና ባህላዊ አቅም ይኖረዋል። በሙዚቃ እና ዝምድን ይወዳዳል ወይም እንደ ከኪ ቡድን ይሆን ወረዳ የሚኖረው ሙዚቃ ይወዳዳል ማለት እንዳለ የሚለው አቀራርቲ ነው።

መዝሙረ ተዋህዶ መስማት ምን ይሆን?

የመዝሙረ ተዋህዶ መስማት አዳዲስ አመለካከት ይይይ የአካል መዝሙር እንዳለ የካንዳ በስተር ነው። መዝሙረ ተዋህዶ የዚያ ወይም መዝሙር ሚገኝ።

የመዝሙረ ተዋህዶ የሚለው መስማት ወይም ዝምድን አዳዲስ ይወዳዳል። ይህ ከጌታዬ አሳባለን ወይም ይህ የመዝሙረ ምህዳር መናገር ይኖር የቆረጅ ይወዳዳል።

መዝሙረ ተዋህዶ የድምፅ ዓለም ነው?

እንደ መዝሙረ ተዋህዶ ወይም የድምፅ ዓለም እንዳይኖር እንደ የዋሕል ይወዳዳል። መዝሙረ ተዋህዶ ሙዚቃ ወይም መዝሙር ይወዳዳል ማለት እንዳለ የሙዚቃ አዳሲ ይኖረዋል።

ከአንደኛው ጋር የታወቀ የዋሕል መዝሙር የህይወት ይወዳዳል ይህ እንደ ወንድም የወይም በታይዕ መጠን ይቻላል።

መዝሙረ ተዋህዶ ከየት ይቀበላል?

መዝሙረ ተዋህዶ የሙዚቃና የመዝሙር መነሳት የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና ወርቅ የወሮ ተመለክቷል።

እንደ መዝሙረ ተዋህዶ የዚያ ወይም ዓለም እንዳይኖር ነው። በአማርኛ ይታወቃል ወይም የመዝሙር እነዚህ ውርሱ ይወዳዳል ወይም እንደ ይድር ይወዳዳል ይወዳዳል ውርሱ ውርሱ ይዘነ የሚኖረው ሙዚቃ ይወዳዳል።

መዝሙረ ተዋህዶ እንዴት ይገኛል?

መዝሙረ ተዋህዶ መሰረት ወይም ይኖረዋል በአባይም መንግስት ይቀበላል ይወዳዳል።

እንደ መዝሙረ ተዋህዶ ወይም የሙዚቃ ይወዳዳል ወይም ባህላዊ እንዲገኛ ይኖረዋል።

Canal መዝሙረ ተዋህዶ sur Telegram

መዝሙረ ተዋህዶ እስከ ጥቁር መንፈሳዊ ልብስ ድረስ በተመሠረተ መዝሙሮች ውስጥ ባለፈው ቋንቋ በማወቅ ለሚፈልጋቸው ሰኞ ትግራይ፣ አርቲስቶች፣ ድራማዎች፣ እና አኒቃቂ ተደራሽነትን ማናቸውም የድራማዎች አገልግሎት ለማድረግ የፈቃዷን ቦታ ለመዝሙር የሚገባ ቢቻል ያደርገዋል፡፡ 'መዝሙረ ተዋህዶ' በዚህ ልዩ ውቅዋታ ውስጥ ያግዛል፡፡ ይህ የመዝሙር መዝሙሮች አባላትንና ሌሎችን ወንጌላዊ ጉዳዮችን የሚያስደሳብ እና መዝሙሮችን በነፃ ዕድል ለማዝረቅ ልክ አትችልም፡፡

Dernières publications de መዝሙረ ተዋህዶ

Post image

ልደታ ለማርያም

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰን!!!

ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተመረጡ የተመረጠች ክብርት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በከበረች ቀን ግንቦት አንድ ቀን ተወለደች፡፡ የመወለዷም ነገር እንዲህ ነው፡፡ በጥሪቃና ቴክታ የተባሉ የእግዚአብሔር ሰዎች ነበሩ፤ ባለጸጎች ቢሆንም ልጅ ግን አልነበራቸውም፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቴክታ ሕልም አለመች፡፡ ለባሏም እንዲህ ስትል ነገረችው «በራእይ ነጭ ዕንቦሳ ከማሕፀኔ ስትወጣ፤ ያችም ዕንቦሳን እየወለደች እስከ ፮ ትውልድ ስትደርስ ፮ኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃ ደግሞ ፀሐይን ስትወልድ አየሁ» አለችው፡፡ (ውዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ)         

ባሏ በጥሪቃም «ራእዩስ ደግ ነው፤ የሚፈታልን የለም እንጂ» አላት፡፡ በማግሥቱ ለሕልም ፈቺ ሔዶ ነገረው፡፡ ሕልም ፈቺውም «እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል፤ በሣህሉ መግቧችኋል» ብሎ ፮ቱ እንስት ጥጆች መውለዳቸው ፯ ሴቶች ልጆች እንደሚወልዱ፤ ፯ኛይቱ በጨረቃ መመሰሏ ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት እንደሚወለዱ፤ የፀሐይ ነገር ግን እንደንጉሥ ያለ ይሆናል አልተገለጸልኝም ብሎ ነገረው፡፡ (ነገረ ማርያም)

  

09 May, 04:46
11,057
Post image

  ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ሚያዝያ 30 የቅዱስ ማርቆስ ሰማዕትነት
  ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

❖ የቅዱስ ማርቆስ አባቱ አርስጦቡሎስ የእናቱም ስም ማርያም ይባላል፤ የተወለደውም ሳይሬኔ በምትባል በሊብያ ፔንታፖሊስ ሲኾን እናቱ የዮናናውያንን፣ የሮማይስጥን፣ የዕብራይስጥን ትምህርት እንዲማር አድርጋዋለች፤ ኹለት መጠሪያ ሲኖሩት በዕብራይስጥ ዮሐንስ፤ በላቲን ማርቆስ ተብሏል ትርጒሙም “መዶሻ” ማለት ነው።
📖የሐዋ 12፥12-25፤
📖የሐዋ 15፥37

❖ በርበር ጥቃት ሲያደርሱ ወላጆቹ ሳይሬኔን ለቀው ወደ ፍልስጥኤም በመምጣት ለጌታችን ዐደሩ፤ የማርቆስ እናት ማርያምም ቤቷን ለሐዋርያት የወንጌል አገልግሎት የሰጠች ሲኾን ከጌታችን ዕርገት በኋላም 120 ቤተሰብ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዘው ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ጸጋውን ሰጥቷቸዋል
📖የሐዋ 2፥1-4

❖"ወንጌላዊዉ ማርቆስ በገጸ አንበሳ ይመሰላል፤ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሰዓታቱ ላይ

ዘአንበሳ ማርቆስ እስመ ከመ አንበሳ ይጥሕር አድያመ ግብጽ ዘአድመፀ እንዘ ይሰብክ ወንጌለ እስከ አጽርዐ ምሕራማተ ጣዖት

👉የጣዖት ማምለኪያዎችን እስከ ማጥፋት ደርሶ ድረስ ወንጌልን ሲሰብክ የግብጽን አውራጆች ያነዋወጠ ማርቆስ በገጸ አንበሳ ይመሰላል እንደ አንበሳ ይጮኻልና) ይለዋል፡፡

❖ በገጸ አንበሳ ወንጌላዊዉ ማርቆስን መመሰሉ፤ አንበሳ ኑሮው ከሰው ርቆ በምድረ በዳ ሲኾን ከዚያ ኾኖ ድምፅን ባሰማ ጊዜ እንስሳት ይገሠጻሉ አራዊት ይደነግጣሉ፤ ቅዱስ ማርቆስም ከትምህርት ምድረ በዳ በነበረችው በግብጽ

👉የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መዠመሪያ ብሎ ባስተማረ ጊዜ ምእመናን ተገሥጸዋል አጋንንት ከሓድያን ደንግጠዋልና


ናሁ አንተ ኮንከ ዕሩየ ምስለ አኃዊከ ሐዋርያት”

❖ በማግስቱም ለኹለተኛ ጊዜ ገመዶችን በአንገቱ አድርገው በአገሮቹ ኹሉ ጎትተውት በቀኑም መጨረሻ ሚያዝያ 30 በ68 ዓ.ም ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጥቷል፤ ከዚያም እሳት አንድደው በድኑን ለማቃጠል ከውስጡ ቢጨምሩትም በጌታችን ፈቃድ ንውጽውጽታ ጨለማ መብረቅ ነጐድጓድ ኾነ፤ ይኽነንም ባዩ ጊዜ ከሓዲዎቹ ደንግጠው ሸሽተው ኼደዋል፤ ምእመናንም መጥተው ምንም ጥፋት ያላገኘውን የቅዱስ ማርቆስን ሥጋ አግኝተው በመልካም ልብስ ገንዘው በጥሩ ቦታ አኑረውታል፡፡

👉በላም በረት ውስጥ እንደ ወይፈን በገመድ የሳቡት ለኾነ ለማርያም ልጅ ለማርቆስ ሰላምታ ይገባል፤ ርሱን በእሳቲቱ ላንቃ (ወላፈን) ለማቃጠል በወደዱ ጊዜ ውርጭ እና ዝናብ ማዕበሏን አጠፉ፤ መብረቅም ሥጋውን ጋረዳት በማለት ተጋድሎውን እንደ ወርቅ አንከብልሎ እንደ ሸማ ጠቅልሎ ገልጾታል፡፡

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ “ሰላም ለማርቆስ ዜናዊ ወንጌለ ጽድቅ ሰባኪ ለእለ በግብጽ ኖላዊ”

❖ ሚያዝያ 30 በግብጽ እስክንድርያ በ68 ዓ.ም. በሰማዕትነት ያረፈው ወንጌልን የጻፈው የቅዱስ ማርቆስ መቃብሩና ክቡር ዐፅሙ የሚገኝበት ቅዱስ ቦታ ይኽ በፎቶ ላይ የምታዩት ነው፤ በካይሮ መንበረ ማርቆስ ውስጥ ይገኛል፤ የግብጽ ኦርቶዶክስ አማኞች ወንድሞቻችን እኅቶቻችን የከበረ የቅዱስ ማርቆስ ዐፅሙ በሚገኝበት በዚህ ቅዱስ ስፍራ ሻማ እያበሩ ወልድ ዋሕድ የምትለውን ቅዱስ ወንጌልን በግብፅ ሰብኮ ጣዖታትን ያጠፋላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ያጠመቃቸው በአንበሳ የተመሰለው ቅዱስ ማርቆስ ወደ አምላኩ ክርስቶስ እንዲያማልዳቸው ዘወትር ይለምናሉ።

❖ እኔም ወንጌል ለማስተማር ግብጽ በነበርኩበት የአንድ ወር ቆይታዬ ከ72ቱ አርድዕት ወደኾነው የቅዱስ ማርቆስ ክቡር ዐፅሙ (ሰውነቱ) በክብር ባለበት መዐዛው ልቡናን ወደሚመስጠው ቦታ በየዕለቱ እየኼድኩ ስሳለምና ሻማ ሳበራ እንደ ኤልሳዕ ዐፅም የቅዱሳን ዐፅም ሙት ያነሣል በረከትን ያሰጣልና መቼም መች የማልረሳው ጊዜ ነበር፤ የቅዱስ ማርቆስ በረከት በኹላችን ዐድሮ ይኑር።

በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ

08 May, 13:14
9,541
Post image

እሁድ፦ ዳግም ትንሣኤ ይባላል፦

"…ከመጀመሪያው ትንሣኤ ቀጥሎ ያለው የመጀመሪያው ሳምንት በስምንተኛው ቀን የምናገኘው እሁድ ዳግም ትንሣኤ ይባላል። በዚህ ዕለት ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤው ፍጹም መሆኑን ለማረጋገጥ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱን በማሰብ ዕለቱ ይታሰብ፣ ይከበርበርም ዘንድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሠርታለች።

"…ከስምንት ቀን በኋላም ደቀ መዛሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ። ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ፦ ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው። ከዚያም በኋላ ቶማስን፦ ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው። ቶማስም፦ ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት። ኢየሱስም፦ ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ዮሐ 20፥ 26-29።

"…ይህ ዕለት እንደ ሐዋርያው ቶማስ ላሉ ትንሣኤውን ለተጠራጠሩ ሰዎች የተወጋውን ጎኑን ተመልክተው እና ደስሰው በእውነት የተነሣው ጌታ እሱ መሆኑን በእርግጠኝነት ያመኑበት ዕለት ነው። የዛሬው እሁድ የዕለተ ትንሣኤ ስምንተኛ ቀን አግብዖተ ግብር ዳግም ትንሣኤም ይባላል። “እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤” ዮሐ 17፥4 ብሎ በሐዋርያቱ ፊት ለመጨረሻ ጊዜ ከእርገቱ በፊት በቅዱስ ወንጌል ያልተጻፉ ድንቆችን ያደረገበትም እለት ነው።“ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤” ዮሐ 20፥30

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም።

23 Apr, 09:41
8,615
Post image

#እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በጌቴ ሴማኒ በአትክልቱ ቦታ ሳለ ጸሐፍት ፉሪሳውያን በአይሁድ ሸንጎ ውሳኔ መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ ያለበትን ለጠቆመ ወሮታ እንከፍላለን ባሉት መሠረት ከዳተኛው ይሁዳ በዚህ ምሴተ ሐሙስ የካህናት አለቆችንና ፈሪሳውያንን እንዲሁም ኢየሱስን ለመያዝ የተመደቡት የሮማ ቄሳር ወታደሮችን በመምራት ኢየሱስ በጸሎት ከሚያሳልፍበት ከጌቴ ሴማኒ ይዟቸው እየመጣ ነው ። እግዚእነ ኢየሱስም ሁሉን አዋቂ አምላክ ነውና ይሁዳ የሮማ ቄሳር ወታደሮችንና ፈሪሳውያንን እየመራ ሊያሲዘው እየመጣ መሆኑን ለደቀ መዛሙርቱ " ገናም ሲናገራሳቸው እነሆም ቆመጥ የያዙ የሮማ ቄሳር ወታደሮች ወደ አትክልት ስፍራ ገቡ። ይሁዳም ከፈሪሳውያን ጋር በተነጋገረው የያዙት ምልክት መሠረት ሊስመው ወደ ኢየሱስ ቀረበ ፣ ኢየሱስም በመሳም አሳልፈህ ልትሰጠኝ መጣህን?? አለው ። የሮማ ቄሳር ወታደሮችም እግዚእነ ኢየሱስን ያዙት።

#ሰባተኛው ሰዓት ሌሊት ሲሆን የአይሁድ የሃይማኖት መሪዎችና ፈሪሳውያን ኢየሱስ እንደተያዘ እንደተያዘ ወደ ተሻረው የአይሁድ ሊቀ ካህናት እንዲወሰድ የያዙትን የሮማ ቄሳር ወታደሮችን መከሩ ። የአይሁድ ካህናት ተንኮል የረቀቀ ነበር ። በዚህን ወቅት በሕጋቸው በማይፈቀድ ሁኔታ ሁለት ሊቃነ ካህናት ነበራቸው፣ አንዱ የይስሙላ ሲሆን በሕግ ግን የተሻረ ነበር ። ከሥልጣኑ የተሻረው ሊቀ ካህናት ሐና ይባላል ። ይህ የተሻረው ሊቀ ካህናት ሌሊትም እሠራለሁ ባይ ነበርና አይሁድ ሆን ብለው ውሳኔ መስጠት ወደ ማይችለው ሊቀ ካህናት ዘንድ ኢየሱስን አስወሰዱት። (ዮሐ.18:23፤ማቴ.27:26) ሐናም ይሄን ጉዳይ እኔ ማየት አልችልም ብሎ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀያፋ መራው ።

#ይሁንና የአይሁድ ሸንጓቸው ሥራ የሚጀምረው ሲነጋ ጠዋት ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ባለው አደባባይ ላይ ሆኖ በሊቀ ካህናቱ ቀያፋ እየተመራ ስለሚካሄድ የሮማ ቄሳር ወታደሮች ኢየሱስን ወደየት መውሰድ እንዳለባቸው ባለማወቃቸው ኢየሱስ ክርስቶስን ሊያንገላቱት ሆነ ።

13 Apr, 07:52
8,594