أحدث المنشورات من ማራናታ.....MARANATHA😍 (@maranathawoch) على Telegram

منشورات ማራናታ.....MARANATHA😍 على Telegram

ማራናታ.....MARANATHA😍
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch

Inbox Comment @Taddyapostolic
12,253 مشترك
1,643 صورة
73 فيديو
آخر تحديث 06.03.2025 04:17

أحدث المحتوى الذي تم مشاركته بواسطة ማራናታ.....MARANATHA😍 على Telegram

ማራናታ.....MARANATHA😍

05 Mar, 02:48

1,247

የማለዳ ትምህርት
ቀን 26/6/2017


ሰላም እንዴት ናችሁ የተወደዳችሁ የማራናታ ቻናል ቤተሰቦቻችን ውድ ቅዱሳን የክርስቶስ ፀጋ በያላቹበት ይድረስ ዛሬም ምህረት ጥበቃው በዝቶልን በቀን ላይ ቀን ተጨምሮልን ዛሬን አይተናል በቤቱ ያኖረን አምላክ ይመስገን!!

ትናንት ምርጫችን እንለይ በሚል ርዕስ ተምረን ነበር እናም መልካም ነገርን መምረጥ ህይወትን መዳንን ያስገኘናል ምክንያቱም የመረጥነው ኢየሱስን ነውና ዛሬም ከዛ በመቀጠል የመረጥነውን መዳን በትጋት እንጠብቅ በሚል እንማራለን

ርዕስ:መዳናችንን በትጋት እንጠብቅ

ሮሜ 13:11 ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።

በቃሉ የተነገሩ ትንቢቶች እየተፈፀሙ ነው እግዚአብሔር ወደ እኛ የእቀረበ ነው እናም የመዳናችንን ፍፃሜ በትጋት መፈፀም አለብን ዘመኑ አልቋል በእግዚአብሔር አሰራል የመንግስቱ ፍፃሜ የተወሰነለት ጊዜ አለ እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል በዛ ሰዓት ሲመጣ እንዳያጣን ዛሬ ቀን ሳለ ለመዳናችን ዋጋ እንስጥ

በቤታችሁ አንድ የከበረ እንግዳ ሊመጣ እንደሆነ ቢነግራችሁ ምን ያክል እንደምትዘጋጁ አስቡት ያለ የሌለ ነገራቹን ፍስስ አድርጋቹ አዘጋጅታችሁ ነው ምጠብቁት አይደል ለሰው እንደዚህ ከሆናችሁ ይልቁንስ የመዳናችሁ ዋስትና የሆነ የዘላለም ህይወትን ያገኛችሁበት የልጅነት ስልጣን የሰጣችሁ ከእርሱ ጋር ልትነግሱ ውቢቷን ኢየሩሳሌምን ሊያወርሳችሁ ቃል ኪዳን የገባላችሁን አምላክስ በምን መልኩ ነው ተዘጋጅታችሁ ምጠብቁት??


ሌሎች እንደሚኖሩት እንደሚመላለሱት መመላለስ የለብንም በዋጋ ነው የተገዛነው እርሱ ሞቶ ነው እኛ ህይወትን ያገኘነው ስለዚህ መዳናችንን አጥብቀን መያዝ አለብን መዳናችንን ማቃለል የለብንም

ዕብራውያን 6:11-12 በእምነትና በትዕግሥትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ፥ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን።

ዳተኛ መሆን ከእኛ ይራቅ በህወታቸው የእግዚአብሔርን ስም የሚያስነቅፉ ለቤተክርስቲያን ስራዎች እንቅፋት የሆኑ ሰዎች ይኖራሉ መዳናቸውን ችላ ብለው በአለማዊነት በስጋዊነት ተግባር የተጠመዱ ይኖራሉ እውነት ኢየሱስ እንደሆነ አውቀው ብርሀን በርቶላቸው ነገር ግን ያገኙትን ድንቅ መዳን ችላ ይላሉ እግዚአብሔርን በነገር ሁሉ ያዋርዳሉ ከዚህ ነገር እራሳችንን እንጠብቅ

ዕብራውያን 6:4 አንድ ጊዜ ብርሃን የበራላቸውን ሰማያዊውንም ስጦታ የቀመሱትን ከመንፈስ ቅዱስም ተካፋዮች ሆነው የነበሩትን
5 መልካሙንም የእግዚአብሔርን ቃልና ሊመጣ ያለውን የዓለም ኃይል የቀመሱትን
6 በኋላም የካዱትን እንደገና ለንስሐ እነርሱን ማደስ የማይቻል ነው፤ ለራሳቸው የእግዚአብሔርን ልጅ ይሰቅሉታልና ያዋርዱትማልና።

እናም ዛሬ በህይወታችን በኑሮአችን ላይ የሚፈታተነን ነገር ይኖራል ለመዳናችን እንቅፋት የሚሆኑ ብዙ ፈተናዎች ሊፈራረቁብን ይችላሉ ማጣት መታረዝ እስከ ሞትም የሚያደርስ ፈተና ልገጥመን ይችላል ነገር ግን የሞተልንን ክርስቶስን ብቻ እንመልከት በትዕግሥት እና በእምነት ወደ ፊት እንሂድ እንጅ ለመዳናችን እንቅፋት እንዲሆኑብን እጅ አንስጥ አንሸነፍ እንደ ወርቅ የነጠረ ክርስቲያን እንሁን እንደዛ ሲሆን ነው መዳናችንን በትጋት መጨረስ የምንችለው

የተስፋውን ቃል ለመጨረስ መዳናችንን መፈፀም አለብን በራሳችን ምኞት እና ሀሳብ ተታለን ከመንግሥቱ እንዳንጎል
ኢየሱስ ሁላችንንም ይርዳን መዳናችንን በትጋት የምንጠብቅበት ሀይል ይስጠን አሜን!!

🤷‍♀🤷‍♂በፀሎት ወጣችሁ በምስጋና ግቡ🤷‍♀🤷‍♂

🌻የእለቱን ትምህርት በየማለዳ🌻
🌸የጉዞአችንን ስንቅ ከማራናታ🌸

            🌼ብሩህ ቀን🌼

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

Any comments@maranathawoch
Inbox @Fasikaa
ማራናታ.....MARANATHA😍

04 Mar, 19:55

1,397

ስሜ ኢየሱስ ያውቃል ያለ ወንድም ኢየሱስ አብዝቶ ይባርከውና ለእህታችን ከነጸሎቱ ብር አስገብቷል

አሁንም ትብብራችሁን ቀጥሉ......
ማራናታ.....MARANATHA😍

02 Mar, 03:33

624

ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርክህ ወ/ም FIKADU FISA

አሁንም ትብብራችሁ ይቀጥል..........
ማራናታ.....MARANATHA😍

02 Mar, 01:24

658

የእርዳታ ጥሪ፦ ለወገን ደራሽ ወገን ነው

" ሁሉም እያንዳንዱ ባልንጀራውን ይረዳው ነበር፥ ወንድሙንም። አይዞህ ይለው ነበር።" (ት ኢሳይያስ 41:6)

እኛ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በተሰጠን አቅም አይዞህ/ሽ ማለት ዛሬ ብቻ የተጀመረ አይደለም ድሮም የተለመደ ነው። ደግሞ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆናችን ብቻ በቂ ነው።

በእርግጥ በፊትም በቅርብ ቀን ለታመሙና ለተቸገሩ ወንድሞቻችን እንዲሁም ለአባታችን ብዙ መሥዋዕት ከፍላችኋል። ኢየሱስ በማያልቅ በረከት በእጥፍ ይባርካችሁ። ይህንን ያደረጋችሁት ሰው ይመልስልናል ብላችሁ ሳይሆን ለነገ በመዝገብ ላይ መታሰቢያ ሆኖ ይጻፍልን ብላችሁ ነው።


(ወደ ዕብራውያን ምዕ. 6) 10፤ እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና። 11-12፤ በእምነትና በትዕግሥትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ፥ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን።

ስለዚህ አሁንም ያን ትጋትና ፍቅር እንድታሳዩልን እንመኛለን።


እህት ትዕግስት ትባላለች፤ የሚትኖሪው አዳማ አክባቢ ነው። በድንገት ታምማለች፤ ወደ አዳማ ሆስፒታል ገብታለች። በምርመራ የተገኘ ውጤት በሁለቱም ኩላልቷ ላይ ጠጠር ተገኝቷል የሚል ነው። ለቀዶ ጥገና or Surjery ይደረግ ተብላለች። ይሁን እንጅ ያለቻት እናት ምንም ማድረግ አልቻለችም። ለህክምና 95,000 ብር ተጠይቃለች። እሷ ግን እንዳለችኝ " ለዋራ ትራንስፖርት ብዬ ያስቀመጥኩት 1900 ብር ብቻ አለኝ እሱም ገና አንድ ጊዜም መድኃኒት መግዣ ሳይበቃ አለቀ" ትላለች። ስለዚህ ለዚህች እህታችን፦

🙏😭እባካችሁ እህታችን ጤናዋ ተመልሶ(ድና) የጓጓችውን ዋራ ጉባኤ እንድትካፈል በምንችለው አቅም እንዲናግዛት በኢየሱስ ፍቅር እንለምናችኋለን። 

የተጠየቀችው 95,000 ብር
95 ሰው 1000 ብር 95,000
190 ሰው 500 ብር 95,000
475 ሰው 200 ብር 95,000
ለተቸገረ የሰጣችሁት ለፈጣሪ እንዲሰጣችሁ ስለምቆጠር ዋጋውን ከፈጣር እንደምታገኙ አስባችሁ  እህታችንን አግዟት🙏😥


1, በመጀመሪያ በያለንበት ሆነን በጸሎት እንድረስላት፦ ከዚህ በፊትም ጸሎታችሁ ዋጋ እንዳለ አይተናልና

(የያዕቆብ መልእክት ምዕ. 5) 15፤ የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል። 16፤ እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።

2, እያንዳንዳችን ኢየሱስ በሰጠን መጠን እጃችንን ወደ እህታችን በመዘርጋት ከጎኑዋ እንሁን። ነገ ለእኛ ምን እንደሚያጋጥመን አናውቅምና እስቲ ከአስር ብር አንስተን ልባችን የፈቀደልንን ሁሉ እናደርግ። እሷም አንድ ቃል ተናግራለች፦ " የማራናታ ተለግራም ቻናል ወንድሞችና እህቶች ብቻ ከረዱኝ በቂ ነው፤ እኔ እህታችሁ በህይወትና በሞት መካከል ነኝ፤ ድረሱልኝ" ብሎዋለች። እሽ ውድ ማራናታዎች ምን እንመልስ?

ይህ ከላይ የሚትመለከቱት #Vedio እና #photo የምርመራዋ ውጤት የሚያሳይ ነው። ስለዚህ ልባችሁ የተነካ ሁላችሁም ለዚህች ምስክን እህታችን አንድ ነገር በሉአት አደራ

እንደ በፊቱ screen shot አድርጋችሁ ላኩልኝ አልላችሁም ስማችሁን ኢየሱስ ብቻ ይወቅ፤ ለእህታችን በጎነት እናደርግላት።

ነገር ግን ግልጽ ያልሆነላችሁ ነገር ካሌ ጠይቁኝ
እኔ ወንድማችሁ ወ/ም ታደሰ ነኝ
@Taddyapostolic
@Fiqaduuapostolic ላይ ጠይቁኝ

ንግድ ባንክ
1000681055758
miss tigist isak abreham

@MARANATHAWOCH

Screenshot @marantawoch or @Fiqaduuapostolic ላይ share አድርጉልን
ማራናታ.....MARANATHA😍

02 Mar, 00:15

624

ቀን 23/6/2017 ዓ/ም

ውድ የማራናታ ቻናል ተከታዮች በያላችሁበት የእግዚአብሔር ሰላምና ደስታ ይድርስላችሁ እያልኩይኝ እስካሁን ሰለችኝ ደከመይኝ ሳይል በማይዝል ትከሻ ለተሸከመን አምላክ ክብርና ውዳሴ ለእርሱ ብቻ ይሁን እነን ደካማን ሳይንቀይኝ  የክብር እቃ አድርጎ እየተጠቀመይኝ ያለው ለዝ ክብር ለመርጠይኝ አምላከን እያከበርኩይኝ  ተመስገን እያልኩኝ ወደ መልዕክተ እገባለው ።

               
 ርዕስ👉 እየሱስ 👉በአንተ ምን ሠራ ?👈

ጥያቄ:- እየሱስ በእኔ ምን ሰራ? ብለህ እራሰህን ጠይቄ ታውቃለህ?

ሐዋርያ ጳዉሎሰ  ምን አለ?
☞ "ለዚህም ነገር ደግሞ፥ በእኔ በሀይል እንደምሰራ እንደ አሰራሩ እየተጋደልሁ፥ እደክማለሁ።" ቆላሰ 1፥29

ሰለዚህ እኔና አንተ/ች ምን እንድንሆን እየተጋደልን ነን?

🗣 ነገር ግን እኔ አሁን እግዚአብሔር በእኔ ምን ሰራ የሚለውን ቀይሬ ፦
👉 እግዚአብሔር ለአንተ ምን ሰራ ብል ኖሮ የማያልቅ ነገር በሽህ የምቆጠር ነገር ትነግሩኛላችሁኝ።

ግን በአንተ ምን ሰራ ሰላለሁኝ ለአንዳንዶች አንድም ሰራ የለንም።

በሰማይ የምጻፈው ግን እግዚአብሔር ለአንተ/ች የሰራልህን/ሸን ሳይሆን እግዚአብሔር በአንተ/ የሰራ ነገር ነው።

እግዚአብሔር በሙሴ ዘመን #ቅማል ተጠቅሞ ፊርኦንንና ሀገሩን በጠቅላላ ቅማል በቅማል አደረገ። አጃብዎችና ወታደሮችም በጥይት እንዳይገሉ ቅማል በጥይት አይገደልም።
            ዘፀዓት 8፥16

⁉️ አንተ ግን ለእግዚአብሔር ከቅማል ታንሳለህን ?

እግዝአብሔር የሐ/ያ ጳውሎሰን ጨርቅ ተጠቅሞ የታመሙትን ፈውስ፣ እውሮችን አበራ፣ የሞቱትንም አነሳ።
            ሐዋ 19፥11

⁉️ አንተ ግን ከጠርቅ ታንሳለህን?

እግዚአብሔር ሞቶ የደረቀውን የኤልሳዕን አጥነት ተጠቅሞ የሞተውን ሰው አሰነሳ።   2ኛ ነገ 13፥20

⁉️ አጥነት ሙታንን የምያነሳ ከሆነ አንተ ዛሬ ከሬሳ አጥንት ታንሳለህን?

እግዝአብሔር የአህያን መንጋጋ ተጠቅሞ 1000 ሰው ገደለው።
       መሳፍ 15፥15

⁉️ አንተ ግን በሰሙ የተጠመቅክ
☞ በደሙ የተዋጀህ ሰው በመንገድ ላይ ውሻ ከምጎትተው ከአህያ መንጋጋ ሰለምታንሰ ነው?

እግዚአብሔር የሙሴን በትር ተጠቅሞ የኤርትራን ባህር አካፈለ።
         ዘኁ 20፥8

⁉️ አንድ ከብትን የምንጠብቅ በትር አለዝያም የምትቃጠል በትር ባህርን ካካፈለች እኔና አንተ ከበትር አንበልጥም?

እግዝአብሔር እኛን ተጠቅሞ መሰራት ያለብን ነገር እንድሰራ እራሳችንን እንፈቅድ።

ዘመናችን በከንቱ አይለቅ❗️❗️❗️
ሁል ጊዜም እየሱስ በእኔ ምን ሰራ እያልን ፍቃዱንም እየጠየቅን እንኑር ወንድሞች እህቶች❗️❗️❗️❗️


ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፥ እንድህ ያለው መሰዋዕት እግዚአብሔርን ደሰ ያሰኘዋልና።      ዕብራ 13፥16

በዚህች አጭር ክፍል ላይ በቀረበው መልእክት ልባችሁን አንጽታችሁ ወደ እግዚአብሔር በፍጹም ልብ ውድ እግዚአብሔር  እንመልስ ቀር ዘመናችን ኢየሱስ ይባርክ መልካም የበርከት ቀን ይሁንላችሁ!!

እግዚአብሔር የልመናችን ድምጽ ይስማልን አሜን!!!

🤷‍♂🤷‍♀በጸሎት ወጥታችሁ በምስጋና ግቡ🤷‍♂ኸኀ🤷‍♀

      🌻የዕለቱን ትምህርት በየማለዳ🌻
        🌸የጉዞአችንን ስንቅ ከማራናታ🌸

                    🌼መልካም ቀን!!!🌼
Any Comment @maranathawoch
Inbox me @Fiqaduuapostolic

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
ማራናታ.....MARANATHA😍

22 Feb, 11:51

775

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
ማራናታ.....MARANATHA😍

22 Feb, 11:51

864

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
ማራናታ.....MARANATHA😍

22 Feb, 03:25

1,148

የማለዳ ትምህርት
ቀን 15/6/2017

      "ልብህን ጠብቅ"

በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር የተወደዳችሁ ውድ ወንድሞችና እህቶች እንዲሁም የማራናታ ተለግራም ቻናል ቤተሰብ እና የማለዳ ትምህርት የሚትከታተሉ ሁሉ እንኳን ኢየሱስ በትላንትናው ላይ ዛሬን ጨምሮ አዲሱን ቀን አሳየን/አሳያችሁ እያልኩኝ "ልብህን ጠብቅ " በሚል ርዕስ አጭር ጽሁፍ አቀርባለሁ።

እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ከፈጠረው ሰውነት ክፍል ውስጥ ልብ አንድ ትልቅ የፍርድ ቤት ዳኛ ነው። ይህ ማለት ክፉንም ደጉንም ሀሳብ ግራ ቀኙን መዝኖ ውሳኔ ለመስጠት ድርሻ አለው። ነገር ግን ይህ ልብ ሁሌ መልካም ውሳኔ ብቻ ይሰጣል ማለት አይቻልም። ምክንያቱም አንዳንዴ ክፉንም ሀሳብ እንደ መልካም አድርጎ ሊያስቆጥር ይችላል። ክፉን መልካም አድርጎ ከወሰኔ ግን መንፈሳዊ የሆነ ሰው በመንፈሱ ይገምግምና ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ማቅረብ ግድ ይለዋል። ይህ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ማንነው ካላችሁኝ ልብን የፈጠረ እግዚአብሔር በራዕይ እንድያሳይ ይግባኝ መጠየቅ ይኖርብናል።

ልቤ የወሰነው ውሳኔ ትክክል ነው? አንተን ደስ የሚያሰኝ ነው? መንፈሰን የሚያነጻ ነው? ብሎ ፈቃዱን ካልጠየቀ ይህወቱ ስለሚበላሽ መንፈሳዊ ሰው ሁሉን ይመርምር። ለዚህም ነው በመ.ምሳሌ 4፥23 ላይ "አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የህይወት መውጫ ከእርሱ ነውና" የተባለው። እሽ የህይወታቸን መውጫ ልብ ከሆነ ዛሬ ልባችን ምኑን እያሰበ ይውላል? ጽድቅን ወይስ ኃጥአትን? ስለ አለም ወይስ ስለ ኢየሱስ? ህይወትን የሚሰጥ ወይስ ሞትን የሚሰጥ ነገር ነው የሚናስበው? ህይወትን የሚንመኝ ከሆነ ልባችንን ጠብቀን እንዋል።

እኛ በአንድ ቦታ ተቀምጠን እያለን ልባችን ወዴት ሄዶ ይመጣል? አንደ ክፉ አንደ ደጉ ያስባል። ነገር ግን አብሮን የተቀመጠ ጎደኛችንም አያውቅም የልባችን ሀሳብ.... ነገር ግን ልብን የፈጠረ እግዚአብሔር ያውቃል።


(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ ምዕ. 28)
----------
8፤ አሁንም የእግዚአብሔር ጉባኤ እስራኤል ሁሉ እያዩ፥ አምላካችንም እየሰማ፥ ይህችን መልካሚቱን ምድር ትወርሱ ዘንድ፥ ለልጆቻችሁም ለዘላለም ታወርሱአት ዘንድ የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሁሉ ጠብቁ፥ ፈልጉም።

9፤ አንተም፥ ልጄ ሰሎሞን ሆይ፥ እግዚአብሔር ልብን ሁሉ ይመረምራልና፥ የነፍስንም አሳብ ሁሉ ያውቃልና፥ የአባትህን አምላክ እወቅ፤ በፍጹም ልብና በነፍስህ ፈቃድም አምልከው፤ ብትፈልገው ታገኘዋለህ፤ ብትተወው ግን ለዘላለም ይጥልሃል።

ስናገለግልም፣ ስናመልክም በፍጹም ልብ እንድናመልክ ይፈልጋል። እኛ ስናመልክ ስንባረክ ሰው ሁሉ ንጹህ ነው ሊለን ይችላል፣ ቄስንም ደስ ሊናሰኘው እንችላለን..... ኢየሱሰ ግን የውጫዊ ማንነታችን ሳይሆን ልባችንን ይመረምራል፣ ይህ ማንነው ይላል፣ ትላንትና የት ዋሌ ይላል፣ አሁን ከዚህ ወጥቶ ምን ልሰራ ነው ብሎ የነገውን ያያል። በልብ ሌላ ይዘን በአፍ ስናመልክም ያውቃል።


(ትንቢተ ኤርምያስ ምዕ. 23)
----------
23፤ እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም።

24፤ ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።

እግዚአብሔርን የሚያይ ሰው ማንነው ብባል ልቤ ንጹህ የሆነ ሰው ብቻ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔርን ማየት ከፈለግን ልቤ ንጹህ መሆን ይጠበቅብናል።

" ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።"
(የማቴዎስ ወንጌል 5:8)

የንጉሱ ዳዊት ጸሎት ንጹህ ልብ እንድፈጥርለት ነው። ምክንያቱም ዳዊት በህይወቱ ያዬው ትልቅ ነገር ብኖር የሳኦል ህይወት ነው። ሳኦል ንጹህ ልብ ከተወሰደበት ቀን ጀምሮ በምን ህይወት ውስጥ እንዳሳለፈ አስተውሎ ስላየው ነው ቅዱስ መንፈሰህንም ከእኔ ላይ አትወስድብኝ ያለው።


(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 51)
----------
10፤ አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።

11፤ ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።

12፤ የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።

ዛሬ እኛስ የሚንለምነው ነገር ምን ነበረ? ልባችን አሳስቶን ከእግዚአብሔር እንዳይለየን በጸሎት መትጋትና ዘወትር ልቤን ጠብቅ ማለት አለብን።

            መልካም ቀን!!!

        🙏 በጸሎት ወጥታችሁ በምስጋና ግቡ 🙏

             🌻 የማለዳ ትምህርት በየማለዳ 🌻
               🌸 የውሎአችን ስንቅ ከማራናታ 🌸

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch
inbox comment @Fiqaduuapostolic
ማራናታ.....MARANATHA😍

21 Feb, 15:45

1,528

ይህ የምትመለከቱት ምስል በ1987 ዓ.ም ቤተክርስቲያን ገና ለጋ በነበረችበት ወቅት በወላይታ ምድር የመጀመሪያውን የመዝሙር ካሴት ለቤተክርስቲያንቱ ያበረከቱ የቀድሞ መዘምራን በገንደባ ቤቴል ጉባኤ በጋራ ሲያዜሙ የሚያሳይ ምስል ነው።

ያኔ ብዙ ጭንቅና ስደት በነበረበት ጊዜ በተስፋ እንደ ትንቢት የዘመሩት መዝሙር እንዲህ ይላል፦

"ሁለትና ሶስት ሆነን ባንተ ፊት ስንጸልይ ሲናለቅስ፣ የሚንገባበት ስፍራ አጥተን ምን እንሁን ብለን ባንተ ፊት እየወደቅን፣ ያ የጭንቅ ዘመን አልፎ በዚህ ባማረ ስፍራ አቁመኸናል፣ ቁጥር ስፍር የሌለውን ህዝብ አንተ አምጥተሃል ለአብርሃምና ለይስሐቅ የገባኸውን ማላ አስበሃል፣ እንደዚሁ ተሸክመህ ሁላችንንም ወደሚንናፊቃት አገር ወደ ጽዮን አድርሰን"

ዛሬ ቤተክርስቲያን ለዚህ ደረጃ የደረሰችው እንዲሁ በቀላሉ አይደለም፣ ስለዚህ ወንጌል ብዙ የተከፈለ ዋጋና መስዋዕትነት አለ። በገዛ ደሙ የዋጃትን ቤተክርስቲያንን እንዲህ ያበዛት ያሰፋት አምላክ ኢየሱስ ለዘላለም የተባረከ ይሁን። አሜን!
ማራናታ.....MARANATHA😍

21 Feb, 04:07

1,975

#እንኳን_ለ34ኛው_ዋራ_ቤቴል_ጉባኤ_በሰላም_አደረሳችሁ።
34ኛው ዋራ ቤቴል ዓለም አቀፋዊ ኮንፍረንስ ከመጋቢት 4-7/2017 ዓ.ም ይካሄዳል።እግሮች ሁሉ ወደ ዋራ🕎...🚶‍♂️🚶‍♂️
1ኛጢሞ 1፥17 ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን🙏

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH


ANY COMMENT👉@Fiqaduuapostolic