የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ እስካልወጣ ድረስ ህወሓት ትጥቅ እንደማይፈታ አቶ ጌታቸው ረዳ ገለፁ!
የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ እስካልወጣ ድረስ ህወሓት ትጥቅ እንደማይፈታ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ገልጸዋል።በደቡብ አፍሪካ እና በኬንያ ከተደረገው ስምምነት በኋላ “የኤርትራ ሰራዊት ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመ እና ንጹሃን ዜጎች እየገደለ” እንደሆነ የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ የተደረሰው ስምምነት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉት የውጭ ሃይሎች እንዲወጡ የሚያስገድድ ነው ብለዋል።
“ከጅምሩም የህዝባችን ደህንነት ለማስጠበቅ ነው ስንዋጋ ይነበርነው” ያሉት አቶ ጌታቸው “ህዝባችን በአንድም በሌላም መንገድ ደህንነቱ ከተጠበቀ ከባድ መሳርያዎች እና ታንኮች ተሸክመን የምንቀጥልበት ምክንያት የለንም”ብሏል።በስምምነቱ መሰረት ለ6 ሚልዮን ዜጎች የሚደርስ ሰብአዊ እርዳታ እየጠበቁ መሆናቸውንም አቶ ጌታቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ተናግረዋል።
[Addis Zeybe]
የኤርትራ ሰራዊት ከትግራይ እስካልወጣ ድረስ ህወሓት ትጥቅ እንደማይፈታ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ ገልጸዋል።በደቡብ አፍሪካ እና በኬንያ ከተደረገው ስምምነት በኋላ “የኤርትራ ሰራዊት ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመ እና ንጹሃን ዜጎች እየገደለ” እንደሆነ የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ የተደረሰው ስምምነት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉት የውጭ ሃይሎች እንዲወጡ የሚያስገድድ ነው ብለዋል።
“ከጅምሩም የህዝባችን ደህንነት ለማስጠበቅ ነው ስንዋጋ ይነበርነው” ያሉት አቶ ጌታቸው “ህዝባችን በአንድም በሌላም መንገድ ደህንነቱ ከተጠበቀ ከባድ መሳርያዎች እና ታንኮች ተሸክመን የምንቀጥልበት ምክንያት የለንም”ብሏል።በስምምነቱ መሰረት ለ6 ሚልዮን ዜጎች የሚደርስ ሰብአዊ እርዳታ እየጠበቁ መሆናቸውንም አቶ ጌታቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ተናግረዋል።
[Addis Zeybe]