Последние посты Etege Menen Boarding School (@emgbss) в Telegram

Посты канала Etege Menen Boarding School

Etege Menen Boarding School
2,657 подписчиков
376 фото
4 видео
Последнее обновление 25.02.2025 23:52

Похожие каналы

BANK SBI PO CLERK ENGLISH GRAMMER QUIZ
239,051 подписчиков
OROMIA TEACHERS COMMUNITY
13,057 подписчиков
ODA Boarding School Academy
10,600 подписчиков

Последний контент, опубликованный в Etege Menen Boarding School на Telegram


#NationalExam

" ፈተናው ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት እየተዘጋጀ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፤ " የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ብሏል።

" ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ እንዳሉም ጠቁሟል።

በዚህም " የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።

የፈተና ዝግጅቱ፡-

1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣

2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ እንደሆነ ተገልጿል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ እንደሆነ ተመላክቷል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎት መ/ቤቱ አሳስቧል።

ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል።

የዘንድሮ ሀገር አቀፉ የ12ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም።

@tikvahethiopia

በ2018 ዕድሜያቸው መታወቂያ ለማውጣት የደረሱ ተማሪዎች ለትምህርት ቤት ምዝገባ የፋይዳ መታወቂያ ይጠየቃሉ ተባለ።

በሚቀጥለው ዓመት ትምህርት ቤት ከሚመዘገቡ ዕድሜያቸው መታወቂያ ለማውጣት የደረሱ ተማሪዎች ከልደት ካርድ ውጭ የፋይዳ መታወቂያ እንደሚጠየቁ ሰምተናል።

የሲቪል ምዝገባ እና አገልግሎት ኤጀንሲ ከብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተከትሎ በሚቀጥለው አመት ተግባራዊ እንደሚደረግ የኤጀንሲው ዳይሬክተር ዮናስ አለማየሁ ገልፀዋል።

ኤጀንሲው ከአገልግሎቱ ጋር መስራት ከጀመረበት 2 ወር ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ 1.8 ሚሊየን የሚሆኑ ነዋሪዎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመሆን የምዝገባው ሂደት የሚከናወን ሲሆን፤ 40 በመቶ የሚሆነው ምዝገባ በኤጀንሲው መከናወኑን ገልፀዋል።

የተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባን ከመንግስት ትምህርት ቤቶች በተጨማሪ ወደ ግል ትምህርት ቤቶች ለማስፋፋት ዕቅድ መያዙንም ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

በሚቀጥለው 6 ወራት ጊዜ ውስጥ የነዋሪነት መታወቂያ የሆነ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥር የያዘ፣ የመንጃ ፍቃድ ቁጥር ያለው እንዲሁም እንደ ኤቲ ኤም ካርድ የሚያገለግል ሁሉንም በአንድ የያዘ ስማርት ካርድ ወደ ስራ እንደሚገባም ተናግረዋል።


ETHIO FM 107.8

ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

Baga Ayyaana Cuuphaan Isin Gahe
እነኳን ለጥምቀት በዓል አደረሰቸሁ
እንኳዕ ንበዓል ጥምቀት አብፀሐኩም

የኢትዮ ቴሌኮም የቀጥታ ድርሻ ባለቤትነት ዕድል የካቲት 7 ያበቃል!

💁‍♂️ የአክሲዮን ሽያጩ በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ይከናወናል፤ እርስዎም የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጋብዘዋል፡፡

🗓 እስከ የካቲት 07/2017 ዓ.ም ብቻ!

📖 የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን https://teleshares.ethiotelecom.et/ ያንብቡ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ወደ 128 ይደውሉ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

ወወላዲቱሂ፡ ኮነት፡ ድንግልተ፡ ዘበአማን፡ እስመ፡ ወላዲተ፡ አምላክ፡ ይእቲ፤ ወዘተወልደሂ፡ እምኔሃ፡ አምላክ፡ ሥግው፡ ውእቱ፤ የወለደችውም በእውነት በድንግልና ጸንታ ኖረች፤ አምላክን የወለደች ናትና፤ ርሷም የወለደችው ሰው የኾነ አምላክ ነው፤ ሃ.አበው ዘአክርስቶዶሎስ ም.፩፻፲፪ ቁ. ፲
መልካም በዓለ ልደተ እግዚእነ ከነ ቤተሰዎ!!!

#NationalExam : የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ምዝገባቸውን ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድመው እንዲያጠናቅቁ አገልግሎቱ አሳስቧል።

የፈተና ይዘትን በተመለከተ የሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን ተገልጿል።

ተማሪዎች በተማሩበት የክፍል ደረጀ የተማሪ መጽሐፍን መሠረት አድርገው እንዲዘጋጁ ተብሏል።

በሌላ በኩል ፥ ዘንድሮ በመደበኛው እና በግል 750,000 ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ  ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

እስካለፈው ሳምንት ባለው ዳታ ወደ 500 ሺህ  ተማሪዎች ተመዝግበል።

በመደበኛው ፕሮግራም 600 ሺህ ተማሪዎች ለመመዝገብ እቅድ የተያዘ ሲሆን እስካሁን ባለው 82 በመቶ የሚሆኑ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ አከናውነዋል ፤ በግል የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል።

ኢንተርኔት ማይሰራበት ቦታ ተማሪዎች በወረቀት ከተመዘገቡ በኋላ ኢንተርኔት የሚሠራበት አካባቢ በመሔድ መረጃቸውን ወደ ኦንላይን እየተጫነ ነው።

የመረጃ ባለቤቶች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ኤፍኤምሲ መሆናቸውን እንገልጸለን።

@tikvahethiopia

የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት መወሰድ ያለባቸው የጥንቃቄ እርምጃዎች
******

የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ሰሞነኛ የመሬት መንቀጥቀጥን (ንዝረትን) አስመልክቶ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ይፋ አድርጓል።

የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ ኮሚሽኑ ያጋራው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

የመሬት ንዝረት/መንቀጥቀጥ/ ክስተት ጋር ተያይዞ ከክስተቱ በፊት፣ በክስተቱ ጊዜና ከክስተቱ በኃላ ሊወሰዱ የሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎች፤

በየትኛውም ወቅት የመሬት ንዝረት ወይም መንቀጥቀጥ በሚከሰትበት ጊዜ ከሁሉም ነገር በፊት አለመሸበር፣ መረጋጋትና ሊወሰዱ የሚገባቸው የጥንቃቄ እርምጃዎችን በጥንቃቄ ማከናወን፤ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን መከታተልና ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ትክክለኛ ያልሆነና ከትክክለኛ ምንጭ ያልተገኘ መረጃዎችን አለመቀበልና አለማሰራጨት እጅግ ተፈላጊ ባህሪያት ናቸው፤

ማንኛውም ግለሰብና ቤተሰብ የፀጥታና ደህንነት ችግሮች እንዳያጋጥሙ በየአካባቢው ካሉ የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅትና በትብብር የመሥራት ኃላፊነት አለበት፡፡ በተጨማሪም በአደጋ ስጋት ምክንያት በተከለሉ አካባቢዎች አለመንቀሳቀስ ተገቢ ሲሆን ከዚህ በታች የተመለከቱት የጥንቃቄ መልዕክቶችም በሁሉም ማህበረሰብ ዘንድ ተግባራዊ መደረግ አለባቸው፡፡

1. የመሬት ንዝረት ከመከሰቱ በፊት፤

• ከቤቱ ወይም ከህንፃው ውስጥ እንዴት መውጣት እንደሚቻልና የት ላይ መሰብሰብና መቆየት እንዳለብን ማወቅ፤

• በአደጋ ወቅት ከጣራ ወይም ከከፍታ ቦታ ከሚወድቁ ቁሳቁሶች ራስን ለመከላከል የሚያስችሉ መከለያዎችን መጠቀመ (ጠረጴዛ፣ ዴስክ፣ ምሶሶ፣ ወዘተ)፤

• የነዳጅ፣ የጋዝ፣ የውሃ፣ የኤሌክትሪክ መስመሮች እንዴት ቶሎ እንደሚዘጉ እና እንደሚቋረጥ አስቀድሞ መለማመድ፤

• በመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት የሚወድቁና ጉዳት የሚያደርሱ ትላልቅ ዕቃዎችን መለየት፤ አስቀድሞ ማስወገድ፤

• ሊቀጣጠሉ ወይም አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ፈሳሾችና ኬሚካሎች ዝቅ ባሉ ካቢኔቶች/ሼልፎች ውስጥ ማስቀመጥ ወይንም ማስወገድ፤

• በአስቸኳይ ጊዜ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ( መድኃኒት፣ የእጅ ባትሪ ፣ ሬዲዮ፣ አልባሳት) መለየትና ማዘጋጀት፤

• በአደጋው ምክንያት የሚበተነው ቤተሰብ እንዴትና የት ቦታ እንደሚገናኝ አስቀድሞ መወሰን፤ (የስልክ ቁጥሮችን መያዝ)፤

• በቀላሉ ለመፍረስ ተጋላጭ ከሆኑ ህንፃዎችና ቤቶች ራስን ቤተስብ ማራቅና በባለሙያ ምክረ ሀሳብ መሠረት ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ መቆየት፤

2. በመሬት ንዝረት ክስተት ወቅት

2.1 በህንፃ ወይም ቤት ውስጥ ከሆነ፡

o ባሉበት ተገረጋግቶ መቀመጥና ሊያዙ የሚችሉ ነገሮችን መያዝ እንዲሁም ጭንቅላትን ከጉዳት መከላከል፤

o ከአንዱ ክፍል/ህንፃ ወደ ሌላ ክፍል/ህንፃ መሮጥ/መንቀሳቀስ አለመሞከር፤

o ከሚወድቁ ቁሳቁሶች ራስን ለመከላከል በቀላሉ በማይሰበሩ መከለያዎች (በጠረጴዛ፣ በዴስክና በምሶሶዎቸ፣ በአልጋ) ስር ጎንበስ ብሎ ራስን መከላከል፤

o በመስኮት ወይም በሊፍት ለማምለጥ ወይም ለመውረድ አለመሞከር፤

o ፊትን ወደ በር በማዞር ከመስኮት፣ መስታወቶችና ከከባድ ቁሳቁሶች በመራቅ መቆም፤

o የመሬት መንቀጥቀጡ እስከሚቆም ድረስ ባሉበት ቦታ ተረጋግቶ መቀመጥና አለመንቀሳቀስ፤

2.2 ከቤት ውጪ ከሆነ

o ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሮጥ/መንቀሳቀስ አለመሞከርና የመሬት መንቀጥቀጡ እስከሚቆም ድረስ አለመንቀሳቀስ፤

o ከህንፃዎች፣ ከዛፎች ከግድግዳዎች፣ ከኃይል ማመንጫ መስመሮችና ምሶሶዎች፣ ወዘት በመራቅ ክፍት ቦታ ወይም ሜዳማ በሆኑ ቦታዎች ዝቅ በማለትና ሚዛንን በመጠበቅ መቀመጥ/መቆም፤

2.3 በማሽከርከር ላይ ከሆነ (የንዝረት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ)

o በማሽከርከር ወቅት ክፍት ቦታ መምረጥ፣ በፍጥነት ማቆም፣ ሞተር ማጥፋትና የደህንነት መጠበቂያ ህጎችን ጠብቆ በተሸከርካሪው ውስጥ መቆየት፣

o ተሸከርካሪውን በመተላለፊያ መንገድ ወይም ድልድይ ላይ ወይም በኃይል ማመንጫ መስመር ስር አለማቆም፤

o አስቸጋሪ ሆኖ የግድ ከተሸከርካሪው መውጣት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከተሸከርካሪው በመውጣት ወደ በሜዳማ ቦታ መቆየት፤

3. ከመሬት ንዝረት ክስተት በኋላ

• የመሬት መንቀጥቀጥን ተከትሎ ሊነሱ ከሚችሉ የእሳት አደጋ፣ የመሬት መንሸራተት፣ የውሃ አደጋዎች እና ሌሎች አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ (የኃይል ማመንጫ ምሶሶዎችና መስመሮች፣ እሳት፣ ኬሚካል፣ መርዛማ ነገሮች፣ ሊወድቁ የሚችሉ ነገሮች) ነገሮች መኖራቸውን ማረጋገጥና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያስከትል ጥንቃቄ ማድረግ፤

• የተጎዱ/የቆሰሉ ሰዎች መኖራቸውን ማረጋገጥ፣ የመጀመሪያ እርዳታ መስጠት፣ የተጎዱ/የቆሰሉ ሰዎችን በጥንቀቄ እና በፍጥነት ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፤

• የህንፃ መሠረቶች፣ ግድግዳዎች፣ ጣራዎች፣ የጭስ መውጫዎች፣ መሰነጣጠቃቸውንና መጎዳታቸውን ማረጋገጥና ሌላ ጉዳት እንዳያስከትል ጥንቃቄ ማድረግ፤

• የንዝረቱ ወይም የመሬት መንቀጥቀጡ የሚቀጥል መሆኑ ከታወቀ ወደ ተዘጋጀው ጊዜያዊ መጠለያ መቆየት አካባቢው አደገኛ መሆኑ ከተረጋገጠ ሌላ ጊዜያዊ መጠለያ በማዘጋጀት ከአካባቢው መራቅ፤

• ለአስቸኳይ ጊዜ የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ፍላጎቶች ምግብ፣ ውሃ፣ አልባሳትና መድኃኒት መኖራቸውን ማረጋገጥ፤

• ከዋናው ንዝረት/ መንቀጥቀጥ ተከትሎ ሊከሰት ከሚችል ዳግም የመሬት ንዝረት /መንቀጥቀጥ/ በቂ ዝግጅት ማድረግ፤

#ለጥንቃቄ🚨

የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ምን ማድረግ አለብን ?

➡️ ከቤት ውጭ ከሆኑ ፦ ከዛፎች ፣ ከሕንፃዎች ፣ ከኤሌትሪክ ምሶሶዎች እና ሌሎች ወድቀው ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች መራቅ እና ገላጣ ሜዳ አካባቢ መቆየት።

➡️ በቤት ውስጥ ከሆኑ ፦ በበር መቃኖች ፣ ኮርነሮች እና ኮሪደሮች ተጠግቶ ማሳለፍ። ከእሳት ምድጃዎች፣ ከተሰቀሉ ፍሬሞች እና የግድግዳ ጌጦች፣ ከመጽሐፍ መደርደሪያዎች እንዲሁም ከመስኮት አካባቢ መራቅ። የጋዝ ምድጃዎችን በተቻለ ፍጥነት ማጥፋት ካልሆነም ከአካባቢው መራቅ።

➡️ በትልልቅ ሕንጻዎች ውስጥ ከሆኑ ፦ ከሕንጻዎቹ ለመውጣት አለመሞከር ፣ አሳንሰር (ሊፍት) በፍፁም አለመጠቀም። ከደረጃዎች አካባቢ መራቅ።

➡️ መኪና እያሽከረከሩ ከሆኑ ፦ የኤሌትሪክ መተላለፊያ ምሶሶዎችን፣ ዛፎችና ሽቦዎች አካባቢ አለመቆም፣ የኤሌትሪክ መስመር ምሶሶዎች እና ሽቦዎች ተሽርካሪው ላይ ከወደቁ ከመኪናው ለመውጣት አለመሞከር፣ በተቻለ ፍጥነት ገላጣ ወደሆነ አካባቢ መኪናን ማቆም።


#Ethiopia
#የአአእሳትናአደጋስራአመራርኮሚሽን

@tikvahethiopia

በ84 ኮሌጆች የሚማሩ ተማሪዎች፤ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት እንዲዘዋወሩ ትዕዛዝ ተሰጠ

የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመመዝገን ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET