Diredawa Adminstration Electric Utility (@eeudiredawa) Kanalının Son Gönderileri

Diredawa Adminstration Electric Utility Telegram Gönderileri

Diredawa Adminstration Electric Utility
Officail Telegram channel of EEU Diredawa Region.
1,507 Abone
606 Fotoğraf
4 Video
Son Güncelleme 06.03.2025 11:30

Diredawa Adminstration Electric Utility tarafından Telegram'da paylaşılan en son içerikler

Diredawa Adminstration Electric Utility

26 Sep, 08:33

1,738

የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለክቡራን ደንበኞቹ እንኳን ለመስቀልና ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

የቅድመ ክፍያ ደንበኞች የመስቀል በዓል ቀን በካርድ ማለቅ ምክንያት አገልግሎት እንዳይቋረጥባቸው በማሰብ ኮኔል እና ሳቢያን በሚገኙ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ የካርድ ማስሞላት አገልግሎት የምንሰጥና የድህረ ክፍያ ደንበኞቻችንም የተጠቀሙበትን የፍጆታ ሂሳብ የምንቀበል በመሆኑ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን አውቃችሁ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

መልካም በዓል!!!!



#የድሬዳዋአስተዳደርኤሌክትሪክአገልግሎት



ወቅታዊና ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት የትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ:-

ፌስ ቡክ፡https://www.facebook.com/diredawaelectric2011
ቴሌግራም፡ https://t.me/eeudiredawa
Diredawa Adminstration Electric Utility

26 Sep, 08:02

1,459

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!! በዓሉ የሰላምና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

21 Sep, 07:37

1,825

ውድ #የድህረ_ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ ክፍያ ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተቋሙ በዘረጋቸው ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች ይፈፅሙ! ከዚህ በተጨማሪም ወርሃዊ የቆጣሪ ንባብ እየተወሰደ መሆኑን ያረጋግጡ! የቆጣሪ ንባብ ካልተወሰደ ለተጨማሪ ውዝፍ እዳ የሚዳርግ በመሆኑ ወቅቱን የጠበቀ ንባብ መወሰዱን ያረጋግጡ፤አለመነበቡን እርግጠኛ ከሆኑ በአቅራቢዎ ለሚገኙ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ ያሳውቁ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

18 Sep, 18:46

1,791

አዲሱ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ አተገባበር በምሳሌ ሲቃኝ

ከመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ ለቀጣይ 4 ዓመታት በየሶስት ወር ተከፋፍሎ በ16 ጊዜ ተግባራዊ እንደሚደረግ ይታወቃል፡፡ ይህም አነስተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን የሚጠቀሙ ደንበኞችን እንዳይጎዳ፣ አሁናዊ የኑሮ ደረጃን ያገናዘበና ድጎማን መሰረት ያደረገ ማስተካከያ መሆኑ ነው፡፡

ይህ የታሪፍ ማስተካከያ የመኖሪያ ቤት፣ ንግድ ተቋማት፣ ዝቅተኛ ኢንዱስትሪ፣ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ እንዲሁም የመንገድ መብራት ተጠቃሚ ደንበኞች በሚል የተከፋፈለ ነው፡፡

የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ ሰባት እርከኖች ያሉት ሲሆን፤ እንደ አጠቃቀማቸው መሰረት ያደረገ ድጎማ ተደርጎበታል፡፡ በዚህም ከ0 እስከ 200 ኪሎዋት ሰዓት የሚጠቀሙ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች የድጎማው ተጠቃሚ ናቸው፡፡

ለአብነት በአገራችን ካሉ የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች ውስጥ 75 በመቶ የሚደርሱት ለመኖሪያ ቤት አገልግሎት የሚውሉ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ካሉት አጠቃላይ ደንበኞች ደግሞ ግማሽ የሚሆኑት በወር 50 ኪሎዋት ሰዓት እና ከዚያ በታች የሚጠቀሙ ናቸው፡፡

እንደ አጠቃቀም ደረጃ ካየነው በወር እስከ 100 ኪሎዋት ሰዓት የሚጠቀመው ደግሞ ቁጥሩ 65 በመቶ ድርሻ አለው፡፡ ከፍ አድርገን እስከ 200 ኪሎዋት ሰዓት በወር ኤሌክትሪክ የሚጠቀመውን ብንመለከት ከአጠቃላይ የተቋሙ ደንበኛ እስከ 80 በመቶ ይደርሳል፡፡

በተሻሻለው ታሪፍ ለምሳሌ የመጀመሪያው እርከን ማለትም እስከ 50 ኪሎዋት ሰዓት በወር የሚጠቀሙ የተቋሙ ግማሽ የሚሆኑ ደንበኞች 75 በመቶ የተደጎመ ታሪፍ ነው አሁንም እንዲከፍሉ የሚደረጉት፡፡

በወር እስከ 50 ኪዋሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች ድጎማ ሳይደረግላቸው በትክክለኛው የታሪፍ ቀመር እንዲከፍሉ ቢደረግ ለአንድ ኪሎዋት ሰዓት 6.01 ብር ይከፍሉ ነበር፡፡ ድጎማ በመደረጉ ለአንድ ኪሎዋት ሰዓት በዚህ በያዝነው መስከረም ወር 0.35 ብር እንዲከፍሉ ተደርጓል፡፡ ይህም ከነባሩ 0.27 ታሪፍ ያለው 12 ሳንቲም ብልጫ ብቻ ነው፡፡

በተመሳሳይ ከ51 እስከ 100 ኪሎዋት ሰዓት ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ቀድሞ ይከፍሉት ከነበረው 0.77 ብር ታሪፍ በዚህ ወር በ1 ኪሎዋት ሰዓት የሚከፍሉት 0.95 ብር ነው፡፡ ይህም ጭማሪው 2 ሳንቲም ነው፡፡ ከ101 እስከ 200 ኪሎዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች ደግሞ 1.63 ብር የነበረው፤ አሁን 1.89 ብር በመክፈል 26 ሳንቲም ጭማሪ ብቻ ይከፍላሉ፡፡

ተጨማሪ ማሳያ ለመጥቀስ በአንድ ወር ውስጥ 50 ኪሎዋት ሰዓት የሚጠቀም አንድ ደንበኛ ድጎማ ባይደረግለት ኖሮ በአጠቃላይ ትግበራው በአማካይ ይከፍል የነበረው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሒሳብ የአገልግሎት ክፍያን ጨምሮ ብር 311 (50 ኪዋሰ *6.01+10.24=310.74) ይሆን ነበር፡፡ ሆኖም ድጎማ በመደረጉ 59.74 ይከፍላል ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት ደንበኛው ለተጠቀመው 50 ኪዋሰ ብር 251 በተቋሙ ይሸፈናል ማለት ነው፡፡

የያዝነው የመስከረም ወር ወርሃዊ ፍጆታ እንኳን በምሳሌ እንመልከት፡-

👉 50 ኪሎዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሆነ አንድ ደንበኛ በነሃሴ ወር ይከፍለው የነበረው 24 ብር ታሪፍ፤ በአዲሱ መስተካከያ ሚከፍለው 28 ብር ይሆናል፡፡ ጭማሪውም 4 ብር ነው፡፡

👉 በተመሳሳይ አንድ 200 ኪሎዋት ሰዓት በወር የሚጠቀም ደንበኛ በቀድሞ ታሪፍ (200*1.63+42 = 368 ብር) ይከፍል የነበረ፤ በዚህ ወር (200*1.89x42.95 = 420.95 ብር) ይከፍላል፡፡ ልዩነቱም 52.95 ብር ብቻ ነው፡፡

በዚህ ማሳያ መሰረት ማንኛውም የተቋማችን የመኖሪያ ቤት ደንበኛ በሚያርፍበት እርከን ውስጥ የሚገኘውን የታሪፍ መጠን በተጠቀመው ኪሎዋት ሰዓት መሰረት በማስላት ወርሃዊ የፍጆታ መጠኑን ማወቅ ይችላል፡፡ የዚህ ወር የአገልግሎት ክፍያ (ለድህረ ክፍያ) ከ50 ኪሎዋት ሰዓት በታች 10.24 ብር እንዲሁም ከዚያ በላይ ለሚጠቀሙት ደግሞ 42.95 ብር ነው፡፡

ሆኖም ሰሞኑ ይህንን እውነታ ባፈነገጠ መልኩ የተዛባ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ጥቂት መገናኛ ብዙናንና የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች ተጠቃሚውን እያሳሳቱ በመሆኑ፤ ክቡራን ደንበኞቻችን ተገቢውን ጥንቃቄ እንድታደርጉና ትክክለኛውን መረጃ ከተቋማችን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Diredawa Adminstration Electric Utility

14 Sep, 10:13

2,201

ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታይ ደንበኞቻችን በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!

በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

ኢድ-ሙባረክ
Diredawa Adminstration Electric Utility

10 Sep, 12:29

2,165

የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለክቡራን ደንበኞቹ እንኳን ለ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

የቅድመ ክፍያ ደንበኞች በበዓሉ ቀን በካርድ ማለቅ ምክንያት አገልግሎት እንዳይቋረጥባቸው በማሰብ ኮኔል እና ሳቢያን በሚገኙ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ የካርድ ማስሞላት አገልግሎት የምንሰጥ ሲሆን ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን አውቃችሁ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

መልካም በዓል!!!!



#የድሬዳዋአስተዳደርኤሌክትሪክአገልግሎት



ወቅታዊና ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት የትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ:-

ፌስ ቡክ፡https://www.facebook.com/diredawaelectric2011
ቴሌግራም፡ https://t.me/eeudiredawa
Diredawa Adminstration Electric Utility

10 Sep, 11:57

2,018

የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለክቡራን ደንበኞቹ፣ ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለመላው የተቋማችን ሰራተኞች እንኳን ለ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅርና የብልፅግና እንዲሆንልን መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡
ፍቅረማርያም አለማየሁ
የድሬዳዋ አስተዳደር ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ስራ አሰፈጻሚ


#የድሬዳዋአስተዳደርኤሌክትሪክአገልግሎት



ወቅታዊና ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት የትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ:-

ፌስ ቡክ፡https://www.facebook.com/diredawaelectric2011
ቴሌግራም፡ https://t.me/eeudiredawa
Diredawa Adminstration Electric Utility

10 Sep, 11:45

1,468

ለቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ

ተቋማችን የዘመን መለዋጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ የቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በበዓሉ ዕለት በመላው አገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ካርድ መሙላት እንዲችሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡

በዚህ መሰረት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ በመጫን በበዓሉ ዕለት የካርድ መሙላት አገልግሎት የሚሰጡ ማዕከላትን ዝርዝር መመልክትና አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
http://www.eeu.gov.et/contents/prepaid?lang=am
Diredawa Adminstration Electric Utility

09 Sep, 07:56

1,299

የተቋማችን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ ያስተላለፉት #የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት