የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

@yezelalemhiywet


🟫ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል
እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤|1ኛ ዮሐ 1፥2


🟫ሕይወት ከሞት በኃላ ከጌታ ጋር ይቀጥላል፡፡ቻናሉ የተከፈተው ሰዎች በክርስቶስ በማመን የሚገኘውን ሕይወት እንዲካፈሉና የቃሉን እውነት ተምረው አርነት እንዲወጡ ነው፡፡You can contact me📲 @ZoeLife123

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

20 Oct, 14:40


የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE pinned «📜📜.....ሥላሴ.....📜📜 📦በመጀመሪያ ሰዎች የሥላሴን አስተምሮ ማመንና መቀበል እንዳለባቸው ላሳስብ እፈልጋለሁ፡፡መለኮት በሶስት አካል እንደተገለጠ የማያምን ሰው አልዳነም፡፡ወልድን የሚቀበል አብን ይቀበላልና፡፡ኢየሱስን ተቀብለህ አብንና መንፈስ ቅዱስን መቀበልና ማመን ግዴታህ ነው፡፡በመጀመሪያ የእግዚአብሔርን ምስጢር ለማወቅ፤ የራስ ጥበብ፣ የራስ እውቀት፣ በጥናት የሚመጣ ጉዳይ አይደለም፡፡ እራሱ መንፈስ…»

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

04 Oct, 14:24


🟫ወንጌል በመልአክት ስብከት በቅዱሳን ስብከት የተመሰረት ሳይሆን በራሱ በወንጌሉ ባለቤት የሁሉ ፈጣሪ በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ ነው።ለሐዋርያቱ መልአክ ተገልጦላቸው ሳይሆን ወንጌልን የጻፉት እራሱ እግዚአብሔር ሰው ሁኖ በመገለጥ ነው።ወንጌል ኢየሱስ ነው።ለዚህ ከሐዋርያቱ አንዱ የሆነው ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር፥ ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም።ገላትያ 1፥11-12 እምነት ወይም ሃይማኖት የሚመሰረተው በመልአክት መገለጥ አልያም በጥሩ ሰዎች መገለጥ ሳይሆን በራሱ በፈጣሪ መገለጥ ነው።የሚታመንበት እርሱ እግዚአብሔር ያልተገለጠበት እምነት ሊባል አይችልም።ጳውሎስም እያለ ያለው ይሄን ነው።ያመናችሁት ወንጌል መልአክቶች ተገልጠውልኝ የነገሩኝ አይደለም።ከጥሩ፣ ከጨዋ አልያም ጻዲቅ ነን ከሚሉ ሰዎች አይደለም።ስለዚህ ብሎ ሲያስጠነቅቀን፥ እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ።ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።ገላትያ 1፥1-9 አስቀድሞ ቃሉ ተናግርዋል።እንኳን ሐዋርያቱ ቀርቶ መልአክቶች መጥተው እነርሱ ከሰበኩት ወንጌል ውጪ ቢሰብኩላችሁ የተረገመ ይሁን።ስለዚህ አስቀድማችሁ የተቀበላችሁት ወንጌል አጥብቃችሁ ያዙት።እናንተስ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ጸንቶ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ቢኖር፥ እናንተ ደግሞ በወልድና በአብ ትኖራላችሁ።እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።1ኛ ዮሐንስ 2፥24-25 በዓለም ላይ በጣም ብዙ እምነቶች አሉ።ነገር ግን እውነተኛ እምነት የሚመዘነው እምነት በሚደረግበት አምላክ መገለጥ ነው።አምላክ የተባለው እምነት ሊደረግበት የሚችለው ቀድሞ ካልተገለጠ ያ እምነት ሳይሆን ፍልስፍና ነው።አልያም ሰዎች የራሳቸውን እምነት ለመመስረት ተጽኖ ለመፍጠር የሚጠቀሙበት አሰራር ነው።ወንጌል ለሰዎች አልያም ለ 12 ሐዋርያት የተገለጠው በአንድ ሃያል መልአክ ሳይሆን በራሱ በእምነቱ ባለቤት በክርስቶስ መገለጥ ነው።በዚህ አለም እምነት የሚጣልበት እራሱ ፈጣሪ እንጂ መልአክት አልያም ሰዎች አይደሉም።ስለዚህ ለእውነተኛ እምነት መሠረቱ እራሱ እሙን የሆነው ፈጣሪ እንጂ መልአክት አልያም ሰዎች አይደሉም።በእኛ ሀገር ጠቅላይ ሚኒሰትር እንዳለ ይታወቃል የታወቀው ታድያ በስሩ ያሉ ሰዎች መንግስት አለ ብለውን ሳይሆን እራሱ መድረግ አዘጋጆቶ ለሕዝቡ በመገለጥ ነው።ከዛ በኃላ ሁሌ መለገጥ አይጠበቅበትም አንዴ መሠረት ስላስያዘ።በመጨረሻም ቃሉ እንዲህ ይላል፥ ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው።1ኛ ዮሐንስ 2፥18-22
@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

22 Sep, 00:51


🚧 እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ።ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።
<<><><>< ገላትያ 1፥7-9 <><><>><
@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

19 Jun, 06:35


🍙እግዚአብሔር አብ እርሱ ለዘላለም በማይታይ ብርሃን ይኖራል።እግዚአብሔር እርሱ ልብሱ ብርሃኑ ነው።ብርሃኑን እንደልብስ ይለብሰዋል።የማይበራለት የሚያበራ።የብርሃናት ሁሉ መገኛ።በብርሃኑ ሰማይን የሞላ ድንቅ አምላክ ክብር ለእርሱ ይሁን።

@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

10 Jun, 18:23


#ጸልዩልኝ...!
@ZoeLife123

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

03 Jun, 02:45


🍙በልጁ በክርስቶስ ምሮን እንጂ መርምሮን ቢሆን በድፍረት በፊቱ መቆም ባልቻልን ጠፍተን ለዘላለም በቀረን ነበር።አሁን ግን በፊቱ እንድንቆም ኢየሱስ አለልን ክብር ለእርሱ ለታረደው በግ ይሁንለት።
@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

17 May, 04:42


🚧 ይሹሩን ሆይ፥ በሰማያት ላይ ለረድኤትህ፥ በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም።መኖሪያህ የዘላለም አምላክ ነው፥ የዘላለምም ክንዶች ከአንተ በታች ናቸው፤ ጠላትህን ከፊትህ አውጥቶ፦ አጥፋው ይላል።ዘዳግም 33፥26

@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

04 May, 08:29


#የሞትን_ዋጋ ከፍሎ ሊያድነን ከመጣ፤ ያዳነን እኛን ለመውሰድ እንዴት አይመጣም! እንደ ቃሉ ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል።

@ZoeLife123

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

02 May, 19:37


🚧ምንም ነገር ልታጡ ትችላላችሁ ኢየሱስን ግን ምንም ቢሆን ማጣት የለባችሁም።ምክንያቱም እርሱ አንድ ነው በምንም በማንም አይተካም፣ በምንም አይለወጥም።ኢየሱስ ሁለት የለውም።እርሱ አንድ ነው።የሚተካው የሚስተካከለው የለም።በዚህ ምድር ብዙ ነገር ልታጡ ትችላላችሁ ኢየሱስን ማጣት ግን ዘላለምን ማጣት ነው።ኢየሱስ መተክያ የለውም።ኢየሱስ የሚወዳችሁ ሰይጣን ከሚጠላችሁ በላይ ነው።ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ሮሜ 8፥35

@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

21 Apr, 05:43


@ZoeLife123

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

14 Apr, 02:40


♨️የቀጠለ፡ ቤተ-ክርስትያን ከተነጠቀች በኃላ በሰማይ ከሙሽራው ጋር አንድ ሱባኤ ትቆያለች ሰባት አመት።ታድያ በምድር በዚህ በሰባት አመት ታላቅ መከራ ሲሆን በሰማይስ ምን አይነት ትንቢቶች ይፈጸማሉ የሚለውን እንመልከት።የበጉ ሰርግ የእራት ግብዣ ስነ ስርዕት የሚፈጸመው በሱባኤው መጨረሻ ኢየሱስ የአርማጌዶ ጦርነት ለመግጠም፣ በእስራኤል ምድርም የሺህው አመት መንግስት ለመመስረት ሊመጣ ሲል አከባቢ ከቤተ-ክርስትያን ጋር ለዘላለም ቃልኪዳን ቀለበት የሚያስርበት ድንቅ የሆነ ጊዜ ይኖራል።ያን ጊዜ ቤተ-ክርስትያን በበጉ ፊት ምንም እድፍ ነውር የሌሌባት ሁኗ ትቀርባለች።የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ።

♨️ያጌጠና የተጣራ ቀጭን የተልባ እግር ልብስ እንድትጐናጸፍ ተሰጥቶአታል።ቀጭኑ የተልባ እግር የቅዱሳን ጽድቅ ሥራ ነውና።ራዕይ 19፥7 እርሱም፦ ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው ብለህ ጻፍ አለኝ። ደግሞም፦ ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው አለኝ።ራዕይ19፥9 በዚህ ታላቅ የሰርግ እራት ላይ የተጠሩት ታድያ እነማን ናቸው!?እኛ በዋናነት ስንሆን በፀጋው የዳነው፣ በመቀጠል ከታላቁ መከራ የመጡ እነዚያ መልክቱን አንቀበልም ያሉትም ጭምር በክብር በበጉ ሰርግ ነጭ የተልባ ልብስ ተሰጥተዋቸው አብረው የዚህ ክብር ተቋዳሽ ይሆናሉ።እንዲሁም አማኞች በምድር ስለሰሩት ሥራ አክሊል የሚሸለምቡት ጊዜ ነው።ጳውሎስ የአክሊል ሽልማት እንደተዘጋጀለት የተናገረው።ለሱ ብቻ ሳይሆን በምድር ለምንሰራው ሥራ ሽልማትን የምንቀበልበት ጊዜ ይሆናል።2 ተኛ ጢሞ 4፥8

♨️ወደ ምድር ልመልሳችሁ በአንድ ሱባኤ ከሚፈጸሙ ትንቢቶች መካአል አንዱ የመንግስቱ ወንጌል ለአሕዛብ መመስከር ነው።ይሄ ማለት ታድያ በዛ ሱባኤ በጣም ለማመን የሚከብዱ ጊዜአት የሚታዩበት በዋናነት መለኮታዊ ፍርድ በምድር የሚፈስበት ወቅት ነው።በክፍል አንድ ሐሰተኛው ክርስቶስ ሲገለጥ በመጀመርያ ሱባኤ አጋማሽ ላይ ዓለምን ሰላም እንደሚያደርግ ከዓለም መንግስታት ጋር እስራኤልን ጨምሮ እንደሚስማማ አይተናል።ነገር ግን ሁለተኛው ሱባኤ መቆጠር በሚጀምርበት ጊዜ ከእስራኤል ጋር የተፈራረመውን የሰላም ስምምነት ያፈርሰዋል።ከሌሎቹ ጋር ያለውን ስምምነት ግን እንደተጠበቀ ነው።ይሄ የሆነበት ምክንያት ይሄ ሐሰተኛው ክርስቶስ ክብርን ስግደትን በአጭሩ አምልኮን ይፈልግና እስራኤላውያን ይሄንን ለማድረግ አእምረዋቸው አልፈቀደምና የመጣውን መከራ ለመቀበል እንቢ ይላሉ።

♨️በዚህ ጊዜ ሐሰተኛው ክርስቶስ ከሌሎች የዓለም መንግስታት ጋር በማበር እስራኤልን ለመውጋት እንቅስቃሴ የሚጀምርበት ወቅት ይሆናል ይሄ ሁለተኛው ሱባኤ መጀመርያ።አሁን ያሉት ኃያል ሀገር ከሚባሉት አንድዋ በስተምስራቅ የምትገኘው ራሽያ ናት።ራሽያና አብዛኛው የዓረብ ሀገሮች እስራኤልን ለመውጋት በሐሰተኛው ክርስቶስ መሪነት የሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ነው።በዚህ ጊዜ ሶስተኛው የዓለም ጦርነትም የሚገለጥበት ወቅት ነው።እኛ እንኳን ይሄው እያየን ለሶስተኛው የዓለም ጦርነት መንስኤ የሚመስሉ ነገሮችን ራሽያና ዩክረን እየተመለክትን ነው።በቀጣይም ስለዚህ የመጨረሻ ጦርነትና ስለ 144,000 ሰዎች ማንነት በሰፊው እንመለከታለን።

ይ----ቀ----ጥ----ላ----ል
@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

06 Apr, 05:10


የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE pinned «🟧 የዘመን-መጨረሻ! ክፍል አንድ ◻️መጀመርያ ያለው ነገር ሁሉ መጨረሻ ሊኖሮው ግድ ነውና፤ አሁን እየኖርንባት ያለቺው ዓለም ካለመኖር ወደመኖር እንደመጣቺው ሁሉ፥ ከመኖር ወዳለመኖር ልትሸጋገር የግድ ነው፡፡ዓለም በዚህ ሰዕት መጨረሻዋ በታላቅ ምጥ ላይ ትገኛለች፡፡ምክንያቱም ምንም እንኳን ለዘመናት በእግዚአብሔር ቸርነት ብትኖርም አሁን የመጥፍያ ወደ ባህር እሳት የመጣልዋ ጊዜ እንደደረሰ ስለምታውቅ በጭንቅ…»

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

05 Apr, 03:35


ሐዋርያት 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ታላቅ የሆነ የተሰማም የጌታ ቀን ሳይመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ።
²¹ የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል።

ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል ተዘጋጁ! በመጠን ኑሩ።በአቅራቢያችሁ ላሉት ሰዎች ሁሉ ወንጌልን ተሎ ተሎ ንገርዋቸው።

@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

20 Mar, 02:47


👑 ኢየሱስ ናፈቀኝ! መጥቶ እስኪወስደኝ።

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

15 Mar, 18:38


🍙 የአዲስ ኪዳን ጸሓፊዎች እግዚአብሔር አብን ለማመልከት "እግዚአብሔር" የሚለውን ስም ሲጠቀሙ እንዲሁም ወልድን ለማመልከት "ጌታ" በግሪኩ ኩሪዎስ የሚለውን ስም ተጠቅመዋል።ሐዋርያው ጳውሎስ ሲጽፈው ሥላሴ ሲባል ሶስት አምላክ እንዳልሆኑ አንድ አምላክ እንደሆነ ነገር ግን አሰራሩ ልዩ ልዩ እንደሆነ በመገለጥ ጽፎልናል። "የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤ አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።" 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥4-6
@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️

የዘላለም ✞ ሕይወት||ETERNAL LIFE

14 Mar, 15:32


🌓የቀጠለ...የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ፦ ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።1ኛ ቆሮንጦስ 15፥47-50 የመጀመርያው ሰው ምድራዊ ነው።የተፈጠረውም አሁን በምናያት ምድር ላይ በገዢነት እንዲኖር አካልን ከምድራዊው አፈር አበጀለት።ከእግዚአብሔር ጋርም ህብረት እንዲያደርግበት መንፈሳዊ ማንነትም ሰጠው።ነገር ግን በኃጢአት ከወደቀ በኃላ ይሄ የፊተኛው ሰው ሁሉ ነገሩ ምድራዊ ሆነ።መንፈሱ በኃጢአት ምክንያት ጨለመ ሞተ።ስለዚህ አፈር ሆነ በስጋው ብቻ የሚኖር ሰው ሆነ።አይታችሁ ከሆነ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን የሰው መንፈስ በኃጢአት ስለሞተ መንፈስ የሚያድረው በቅዱሰ ቅዱሳን ወይም በሰው እጅ በተሰራ መቅደስ ላይ ነበር።ታድያ መንፈሱ አይቆይም ነበር።አንድ ሥራ ለመስራት ሲፈልግ ይመጣና ይሄድ ነበር።በአዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ በመንፈሱ አድርዋል።መንፈስ ቅዱስ እርሱ እግዚአብሔር ነውና በእኛ ከራሱ በተወለደ መንፈሳችን ውስጥ ጥሎን ላይሄድ አደረ።አሁን በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ ዳግመኛ ያልተወለደ ሰው ሁሉ አፈር ነው።ማለትም ስጋ ነው።የሚመራውም በስጋው ነው።ታዲያ ኢየሱስ የመጣው ይሄን አሮጌ ስጋ የሆነን ሰው ለማደስ ሳይሆን አሮጌውን ሰው ገድሎ አዲሱን ሰው ለመውለድ ነው።ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም።“ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው።የሐንስ 3፥8 የኢየሱስ መልስ ነበር።ነፋስ ሲነፍስ ድምጹ ይሰማል ነገር ግን ከወዴት እንደመጣ ወዴትም እንደሚሄድ አታውቁም አለና ከእግዚአብሔር በመንፈስ መወለድም ልክ እንደዚሁ ነው።ሰው ኢየሱስን አምኖ ሲቀበል ተቀብሎም ስለ እርሱ ሲመሰክር በመንፈሳዊ ዓለም የሚሆነው እንዲህ ነው።መንፈስ የሆነ ሰው ይወለዳል።ከማን? ከእግዚአብሔር።በምን በመንፈስ።ይሄ አዲሱ ሰው ለኃጢአት እንግዳ የሆነ፣ በክርስቶስ የጸደቀ፣ ከኃጢአት ነጻ የሆነ፣ በትንሳኤ ቀን የራሱ የሆነ አካል የሚለብስ፣ ለግዜው በሚበሰብሰው አካል ላይ የሚኖር፣ የራሱ የሆነ ልክ እንደወደቀው አዳም የሚገዛት እቺን የወደቀች ምድር ይሄ አዲስ ፍጥረት የሆነው መንፈሳችንም  እርሱ የሚገዛው አዲስ ሰማይና ምድር የተዘጋጀለት ድንቅ ሰው ነው።ከላይ እንዳየነው የመጀመርያው ሰው ከመሬት መሬታዊ ሲሆን ይሄኛው ሰው ግን ከሰማይ ነው።ውልደቱ ሰማያዊ ነው።በትንሳኤ ቀን የሚሰጠው የራሱ የሆነ አካሉ ጭምር ሰማያዊ አካል ነው።"ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል።1ኛ ዮሐንስ 5፥1 ከእግዚአብሔር ተወልዳችዋል ሲባል በኖርማል አትረዱት።አዲሱ የክርስትና ሕይወት የሚጀምረው እንደ አዳም ከጭቃ በመፈጠር ሳይሆን በኢየሱስ በማመን ከእግዚአብሔር በመወለድ ነው።“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።2ኛ ቆሮ 5፥17 አዲስ ፍጥረት ማለት ከዚህ ቀደም በዚህ ምድር ያልነበረ ነገር ግን ከዘላለም በፊት ከእግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ የተመረጠ አዲስ ሰው ማለት ነው።ልክ ከቤተሰቦቻችሁ በስጋ ተወልዳችሁ ወደዚህ ምድር እንደመጣችሁ ሁሉ ወደአዲሱ ዓለም ወደ አዲሱ ሰማይና ምድር የምትቀላቀሉትም ከእግዚአብሔር በመንፈስ ስትወለዱ ነው።አማኝ ማለት አዲስ የሆነ ምድራዊ ያልሆነ ሰማያዊ ሰው ከእግዚአብሔር የተወለደ ነገር ግን በቀድመው በወደቀውና አፈር ነህ በተባለው አሮጌው ሰውነቱ አዲሱ ሰው መንፈስ የሆነው ማንነቱ በዚህ ሰውነት ውስጥ የራሱ ሰማያዊ አካል እስኪለብስ ድረስ እየኖረ ያለ የፍጥረት ሁሉ በኩር ነው።አዲሱ ከእግዚአብሔር የተወለደው መንፈሳችን ፍጹም የሆነ፣ ጥበበኛ፣ የጸደቀ፣ በሚመጣው ዓለም ላይ የሚገዛ፣ በሙታን ትንሳኤ ቀን የራሱ የሆነ የማይበሰብስ አካል የሚለብስ በመጨረሻም ጌታው እስኪመጣ አልያም ከዚህ ለሞትና ለኃጢአት ተላልፎ ከተሰጠው ስጋችን ወጥቶ እስኪሄድ በመቃተት ላይ ይገኛል።"ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና።2ተኛ ቆሮ 5፥1-10
@ZoeLife123
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️  @Yezelalemhiywet✳️✳️