🌱🕊🌾🥀🌱🌱🌴🌱🌱🌱🌱🌾
#ቅድስት_ሥላሴ #በማርያም ሕይወት
🌱🕊🌾🥀🌱🌱🌴🌱🌱🌱🌱🌾
በቅዱስ መጽሐፍ ከዘፍጥረት አንስተን እስከ ዮሐንስ ራዕይ ስንመለከት ቅድስት ሥላሴን በሙላት የተቀበለና ማደሪያ የሆነ የተገኘ እንደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡
#በዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ አባታችን አብርሃም የተቀበላቸውን ሦስቱን ሽማግሌዎች ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ ማሳያ አድርገው አስተምረው አልፈዋል፡፡ "የእግዚአብሔር ማደሪያ በሰዎች መካከል ነው'/ራእይ 21፡3/ ይላል ቃሉ። እመቤታችን በሰዎች መካከል የሚያድረው በስጋዋ አደረ፡፡ የታላቁ የቅድሰድት ስላሴ ማደሪያ ሆና በፍጥረት መካከል ተገኘች፡፡ "የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ' መዝ. 26፡ 8
#በሉቃስ ወንጌል በአንደኛው ምዕራፍ ላይ እንደምናገኘው ሊቀ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ የምስራቹን ቃል ሊያበስራት ወደ እርሷ በመጣ ጊዜ በመላእኩ ቃል ውስጥ ቅድስት ሥላሴ እንዴት በማርያም ሕይወት ውስጥ እንደታየ መረዳት ልበ ደንዳና ካልሆኑ በስተቀር ለማንም አይከብድም፡፡ የማርያም ቅድስት ሥላሴን በምን መልኩ እንደተቀበለች ቃል በቃል ከወንጌል ወስደን እናስቀምጠው፡፡
🌱👑
1) እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፡፡/ሉቃ. 1፡28.
ለብዙ ቅዱሳንና ለእስራኤል እራሱ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነኝ ብሎ ሲናገር አብሯቸውም ሲሆን አይተናል፡፡ የእመቤታችን ለየት የሚያደርገው ከዚህ ቀደም በመላእክቱ፤ በነብያቱና በቅዱሳን ለሌሎች በተናገረው መለኩ ሳይሆነ እጅጉን ረቂቅና ልዩ በሆነ አሰራሩ ነው፡፡ ይህም የወልደ እግዚአብሔር ማረፊያ ናትና፤ ወልደ አምላክን ትወለዳለችና፤ አማኑኤልን ትወልዳለችና እግዚአብሔር ለማዳኑ ስራ ከእርስዋ ጋር ሆነ፡፡ ሊያዘጋጃትና ተልዕኮውን ሊፈጽምባት፡፡ እግዚአብሔር በእውነትም ከእርስዋ ጋር ነው፡፡
🌱👑
2) መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል/ሉቃ. 1፡ 35/
እግዚአብሔር ቅዱስ መንፈሱን በእያንዳንዳችን ላይ ያሳርፋል፤ እኛ እንደቃሉ መሰረት የቅዱሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ መቅደስ ነው/1 ቆሮ. 6፡ 19/ እግዚአብሔር በመንፈሱ የሚኖርበት ማደሪያ ትሆኑ ዘንድ…ኤፌ. 2፡ 22/፡፡ ሰው ሕይወቱን በቅድስና ሲመራ አምላኩን ደስ የሚያሰኝ ለራሱም ቅድስና ለሌሎችም ደህንነትን የሚያስገኝ ሕይወት ሲኖር መንፈስ ቅዱስ በውስጡ ፍሬ ያፈራል፡፡/ገላ. 5፡ 22/ ይህም የመንፈስ ፍሬ ከሰው ጋር በፍቅር፤ በሰላም፤ በትዕግስት፤ በበጎጎት፤ በቸርነትና በገርነት እንዲኖር ለአምላኩ ታማኝ እራሱን የሚገዛ እንዲሆን ኃይል ይሰጠዋል፡፡ ይህ አንዱ መንፈስ በእመቤታችን ሕይወት ላይ ያፈራው በማህጸኗ ያደረው ፍሬ፤ ሕይወት የሚሰጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ የመንፈስ ቅዱሰ ስራ በእርሷ ሕይወት እጅጉን ልዩና በማንም ላይ የማይደገም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሆነ ነው፡፡
🌱👑
3) …ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ/ሉቃ. 1፡ 31-33/
ታላቁ የአምላክ ስጦታ ሰውን ወደ ቀደመ ክብሩ ይመልሰው ዘንድ ከሰማያዊ ዙፋኑ ወርዶ በታላቅ ትህትና የሰው ስጋን ለበሰ፡፡ ከትውልድ ሁሉ የተለችውና የተመረጠችው ለልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡
እግዚአብሔር አስቀድሞ የሚወስን አምላክ ነውና ወስኗት ከሴቶች ሁሉ እጅጉን ብርክት ሆና በመገኘቷ ጊዜው በደረሰ ጊዜ በፊቱ #ሞገስን አግኝታለችና ጠራት፡፡
#የእርሷ_መጠራት ጌታ ለቅዱሳኑ ለአብርሃምና ለዳዊት የገባውን ኪዳን ይፈጽም ዘንድ አብ እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር ሆኖ፤ ወልደ እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት በማህጸኗ እንዲጸነስ በማድረግ አከበራት፡፡
#በአብ ዘንድ ሞገስን ያገኘች፤ ወልድን ጸንሳ የወለደች፤ መንፈስ ቅዱስን በሙላት የተቀበለች፤ ማዕደረ ሥላሴ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአማላጅነቷ ምንጭ እራሱ በእርሷ ላይ ያለው ቅድሰት ሥላሴ ነው፡፡
#የልጇን_አስተምህሮ ቀድማ የኖረች/እኔ የዋህና ትሁት ነኝ ከእኔ ተማሩ…/ማቴ. 11፡ 29/ ይኼ ሁሉ ድንቅ ነገር በሕይወቷ ሲከናወን "እግዚአብሔር #እኔን_ዝቅተኛይቱን_አገልጋይ ተመልክቷልና…'//ሉቃ. 1፡ 48/ በማለት መልካም መአዛ እንዳለው ሽቱ አምላኳን በትህትናዋ ማረከች፡፡ ቅድስናዋንና ጽድቋን በተግባር አሳየች፡፡ የተላበሰችው ጽድቅ ኢየሱስን እስክትወልድ ብቻ አይደለም ይልቁንስ የሕይወቷ አካል ነው፡፡ ጽድቅ ደግሞ በጌታ ፊት ሞገስ ታሰጣለች፡፡ በጻድቃን ይደሰታልና፡፡ ስለዚህም "የጻድቅ ሰው ጸሎት ኃይል አለው'/ያዕ. 5፡ 16/፤ "የጻድቃንን ጸሎት ይሰማል'/ምሳሌ 15፡ 29/፡፡
#የእመቤታችን_ምለጃ የሕይወቷ ሁሉ ድምር ውጤት ነው፡፡ ቃሉን በማመንና በመቀበል የተመሰገነች፤ "እንደቃልህ ይሁንልኝ'/ሉቃ. 1፡ 38/ ያለች፤ ሳታመነታ የማይቻለው እንደሚቻል/ሉቃ. 1፡37/ የማይሆነው እነደሚሆን አመነች "እግዚአብሔር የተናገረውን ሁሉ የሚፈጽም መሆኑን በማመንሽ ምንኛ የታደልሽ ነሽ'/ሉቃ. 1፡ 45/፡፡
#ጽድቋን በሕይወቷ በተግባር በማሳየት የጽድቅ አክሊልን የደፋች እናት፡፡ ምልጃዋ ከጽድቅ ሕይወቷ የሚመነጭ መንፈሳዊ ምንጭ ነው፡፡ #በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አግኝታለች፡፡ ይህ ሞገስ ሞገስ የእመቤታችን ምልጃ ነው፡፡
#ቅዱስን_መላእክት በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ ናቸው፤ ቅዱሳን ደግሞ በፊቱ ሊያቆማቸው የሚችለውን የጽድቅ ስራ ለመስራት ይታገላሉ፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያም ግን መላእክት የሚሰግዱለትን ቅዱሳን የሚያመልኩትን ቅድስት ሥላሴን ተቀበለች፡፡ ሞገስና አግኝታለችና፡፡ ስለዚህም ከምልጃ በላይ የሆነ ስጦታ የተቀበለች እመቤታችን ለቅድስት ስላሴ ማረፊያ ሆናለች፡፡
#እንኳንስ_ማማለድ ይቅርና የሥላሴ ማደሪያ ሆናለች፡፡ በአመክንዮ እንኳን ብንረዳው ቅድስት ስላሴን በተግባር በስጋዋና በሕይወቷ ያስተናገደች እናት ምልጃዋ በዚህ ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡
. . . . ይቀጥላል።
(አስተምህሮ:- በክቡር አባ ዓብዮት ክብረት)
አዘጋጅና አቅራቢ: ያሬድ ደሳለ
#ክርስትናን_ክርስቶስን_እንወቅ፡፡
“አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፡፡” (ማቴ. 6:33)
ቤተሰብ ይሁኑን
👇👇👇
https://t.me/YariedDessale/6788
☝️#ኑ ☝️#እንማማር
The Universal Catholic Church Teaching Channel.