ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

@who_is_jesus


<እርሱም እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።> [ማቴ 16፥15]

ለምን አልሰለምኩም?👇
@Jesuscrucified
@ewnetlehulu

ማንኛውንም ዓይነት መጻሕፍት በPDF ለማግኘት 👇
@mk_bookss @mk_bookss


@zw2we

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 07:57


የእግዚአብሔር ቃል

(ወንድም ሚናስ)

ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ልጁ ለጢሞቴዎስ በሰደደው በኹለተኛው መልእክቱ ላይ የእግዚአብሔርን ቃል፣ θεόπνευστος “ቴኦፕኔውስቶስ” መኾኑን ይገልጽለታል (፪ጢሞ.፫፥፲፮)። θεόπνευστος “ቴኦፕኔውስቶስ” የሚለው ቃል θεό “ቴኦ” ማለትም “እግዚአብሔር” እና πνευστος “ፕኔውስቶስ” ማለትም “መንፈስ” ከሚሉ ኹለት የጽርእ ቃል የተገኘ ነው፤ ተገናኝቶ ሲነበብም “እስትንፋሰ እግዚአብሔር” ወይም “አፊዎተ መለኮት” የሚል ይኾናል። ቅዱስ ሳዊሮስ ዘእስሙናይን የተባለ የቤተክርስቲያን አባት በድርሳኑ ከላይ ያለውን ዐሳብ እንዲህ በማለት ያጠናክረዋል፣ “መጻሕፍት አምላካውያት እስትንፋሰ አፉሁ ለእግዚአብሔር ነዮን-አምላካውያት መጻሕፍት የእግዚአብሔር የአፍ እስትንፋስ ናቸው።” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም “ይደልወነ ናጽምዕ ቃላተ መለኮት ከመ ኢይባእ ውስተ አልባቢነ ቃል ነኪር- ባዕድ ወይም የእግዚአብሔር ያልኾነ ቃል ወደ ልባችን እንዳይገባ የመለኮት ቃላት ልንሰማ ይገባል” ይለናል። እግዚአብሔርን ፊት ለፊት የምናይበት ሕያው መስታወት ቢኖር ቅዱስ ቃሉ ብቻ ነው፤ ወደ ቅዱስ ቃሉ እንመለስ። መልካም ቀን!

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 03:58


የካህናት አለቃ ጌታችን እና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በምንችለውም በማንችለውም ያንተ ኀያል ክንድ ይዘርጋልን። የፈራናቸውን ቀኖች አሻግረን። ዐዘናችንን በፍሥሓ ቀይርልን። ለእናት አገራችን ፍጹም ትንሣኤ፣ ለሕዝቧም ፍቅር ሰላም እዘዝልን።

ሰአልናክ መሓሪ።
ሰአልናከ ከሃሊ።

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 03:26


በእንተ ኢሳይያስ 53

ክፍል አራት
(በወንድም ሚናስ)

በስመ እግዚአብሔር መሓሪ ወመስተሣህል

ቊጥር ዐሥር

“መድቀቁና መሠቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፤ እግዚአብሔር ነፍሱን የኀጢአት መሥዋዕት ቢያደርገውም እንኳ፣ #ዘሩን ያያል፤ ዕድሜውም ይረዝማል፤ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።”

וַיהוָה חָפֵץ דַּכְּאוֹ, הֶחֱלִי--אִם-תָּשִׂים אָשָׁם נַפְשׁוֹ, יִרְאֶה #זֶרַע יַאֲרִיךְ יָמִים; וְחֵפֶץ יְהוָה, בְּיָדוֹ יִצְלָח.

ይሁዲዎች ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ዓመታት ሥጋዊ ልጅ ስላልነበረው ኢሳይያስ 53:10ን “ዘሩን ያያል” የሚለውን ቃል፣ ሊመለከተው እንደማይችል ይናገራሉ፤ ለዚሁም በምክንያትነት የሚጠቅሱት፣ “ዘር” ( זֶרַע “ዜራዕ”) የሚለው ቃል ዅል ጊዜ የሚያመለክተው ሥጋዊ ውልደትን ስለኾነ፣ ትንቢቱ ኢየሱስን ሊመለከት አይችልም ይሉናል። ኾኖም ይህ ሙግት ግን ወንዝ የማያሻግር ድኵም ነው፤ ምክንያቱ ደግሞ זֶרַע “ዜራዕ” የሚለው ቃል ሥጋዊ ብቻ ሳይኾን መንፈሳዊ ጒዳዮችን ለማመልከት በተምሳሌታዊ አገላለጽ(Metaphorical) ጥቅም ላይ ይውላልና። የተወሰኑትን በዚሁ ከኢሳይያስ መጽሐፍ ሳንርቅ የተወሰኑትን እንመልከት፦

“ኀጢአተኛ ወገንና በደል የተሞላበት ሕዝብ፥ የክፉዎች #ዘር(זֶרַע) ፥ ርኵሰትን የምታደርጉ ልጆች ሆይ፥ ወዮላችኹ! እግዚአብሔርን ትተዋል የእሥራኤልንም ቅዱስ አቃለዋል፥ ወደ ዃላቸውም እየኼዱ ተለይተዋል ።” ኢሳ 1፥4

“ምድርኽን አጥፍተኻልና ፥ሕዝብኽንም ገድለኻልና፥ከነርሱ ጋራ በመቃብር በአንድነት አትኾንም፤ የክፉዎች #ዘር(זֶרַע) ለዘለዓለም የተጠራ አይኾንም።” ኢሳ 14፥20

“የምትሣለቁት በማን ላይ ነው? የምታሽሟጥጡት ማንን ነው? ምላሳችኹንስ አውጥታችኹ የምታሾፉት በማን ላይ ነው? እናንት የዐመፀኞች ልጆች፣ የሐሰተኞች #ዘር(זֶרַע) አይደላችኹምን?” ኢሳ. 57፥4

ነብየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ የገቢር ኀጢአትን በመሥራት አምላክን የሚያሳዝኑ ግለሰቦችን የኅሊና ዝቅጠትን ለመግለጽ “ዘር” ( זֶרַע “ዜራዕ”) የሚለውን ቃል እንደሚጠቀም ከላይ ከተጠቀሱት ምንባባት መረዳት ይቻላል። ይሁዲ ወገኖቻችን፣ እንደ ክፋት ፤ ዐመፅ ፤ እና ርኵሰት ያሉ መጥፎ ባህርያት ሥጋዊ ልጆች እንደ ሰው ይወልዳሉ፤ ካላሉን በስተቀር “ዘር” ( זֶרַע “ዜራዕ”) በተዘረዘሩት ምንባባት ውስጥ አካላዊ ውልደትን ሊያመለክት አይችልም።

በዐጭሩ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53 መሲሑ ስለ ኀጢአታችን መከራ በመቀበሉ የዘለዓለም ቤዛነት እንዳስገኘልን የሚያመለክት ድንቅ ምንባብ እንጂ፣ ፈጽሞ ስለ ሕዝበ እሥራኤል የተነገረ መለኮታዊ ትንቢት አይደለም፤ ይህ ተከታታይ ጽሑፋችን መሠረት አድርጐ የተነሣውም ምዕራፉ ለመሲሑ እንጂ ለብዜት አካላት የተነገረ አይደለም በሚል ነው፤ ለዚህም ይሁዲ ወገኖቻችን ለሙግት ዋቢ የሚያደርጓቸውን አራት ቊጥሮችን በተከታታይ ዐቅርበናል። ሀሼም አዶናይ ቢፈቅድ ወደፊት በምዕራፉ ላይ ያሉትን ዐሥራ ኹለቱንም ቍጥሮች የምንመለከት ይኾናል፤ ለአኹኑ ግን በዚሁ ይብቃን።

"ወጸጋሁ: ምስለ: ኵሎሙ: እለ: ያፈቅርዎ: ለእግዚእነ: ኢየሱስ: ክርስቶስ: በኢጥፋአት ፡ አሜን።" ኤፌ.፮፥፳፬

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 03:25


በእንተ ኢሳይያስ 53

ክፍል ሦስት
(በወንድም ሚናስ)

በስመ እግዚአብሔር መሓሪ ወመስተሣህል

ቍጥር 9

“በአፉ ተንኰል ሳይገኝበት፣ ምንም ወንጀል ሳይሠራ፣ #አሟሟቱ ከክፉዎች፣ መቃብሩም ከባለጠጎች ጋር ኾነ።”

וַיִּתֵּן אֶת-רְשָׁעִים קִבְרוֹ, וְאֶת-עָשִׁיר #בְּמֹתָיו; עַל לֹא-חָמָס עָשָׂה, וְלֹא מִרְמָה בְּפִיו.

ይሁዲ ወገኖቻችን በዚህ ክፍል የሚያቀርቡት ሙግት בְּמֹתָיו “ቤሞታው” የሚለው ስም ብዜት ስለኾነ፣ ዕብራይስጡ የሚለን “አሟሟቱ” ሳይኾን “አሟሟታቸው” የሚል ነው፤ ስለዚህ ቊጥሩ ካንድ በላይ ለሚኾኑ አካላት የተነገረ እንጂ ነጠላ አካልን ይኸውም መሲሑን የሚመለከት አይደለም ይሉናል። ኾኖም ግን የይሁዲ ወገኖቻችን ሙግት ተቀባይነት የማያገኝበት ምክንያት፣ በመጽሐፍ ቅዱሳዊው ዕብራይስጥ ኾነ በዘመናዊው ዕብራይስጥ ዘንድ፣ በብዙ ቍጥር የተጻፈ ቃል፣ ዐልፎ ዐልፎ አንድን አካል ብቻ ሊያመለክት የሚችልበት አግባብ አለ፤ ለምሳሌ רחמים “ራሓሚም”፣ הָאֲדֹנִ֑ים “ሃአዶኒም” የሚሉት ቃላት የብዜት ቃላት ቢኾኑም፣ በብዙ ቦታዎች ነጠላ የኾኑ ማጣቀሻዎችን ሲያመለክቱ ይስተዋላል። የሴማዊ ቋንቋዎች ተመራማሪ እና የነገረ መለኮት ጸሓፊ የኾኑት፣ አይሁዳዊው ሊቅ ዶክተር ማይክል ብራውን “የብዜት ቃላት ለነጠላ አካል መጠቀም፣ በቋንቋው ዓለም(በዕብራይስጥ) ዠማሪ ለኾኑ ተማሪዎች እንኳ ሳይቀር እንግዳ ያልኾነ የተለመደ የሰዋስው ሥርዐት ነው” በማለት ይናገራሉ። በማስከተልም ሊቁ “በብሉይ ኪዳን ውስጥ ‛ሞት’ የሚለው ስም በብዙ ቍጥር የተጠቀሰበት ኹለት ጥቅሶች የሚገኙ ሲኾን፤ ይኸውም ኢሳ. 53፥9 እና ሕዝቅኤል 28፥10 ናቸው፤ ታዲያ በሕዝቅኤል 28፥10 ነጠላ ሞትን (תָּמוּת “ታሙት” ) ለማመልከት የብዜት አገላለጽን ( מוֹתֵי “ሞቴይ”) እንደተጠቀመ ማስተዋል ያስፈልጋል።” በማለት בְּמֹתָיו “ቤሞታው” የሚለው የብዜት ቃል ነጠላ አካልን ሊያመልክት እንደሚችል በስፋት ይሞግታሉ[1]

በዘመናችንም ኾነ በጥንት ዘመን በነበሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራት ደግሞ ይህን ጥቅስ እንዴት እንደተረዱት ጠቅለል ባለ መልኩ ደግሞ እንመልከት፡-

፩.በሙት ባሕር ጥቅሎች(መሲሑ ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት የነበረ) ላይ እንደሚታየው፣ ይህ ጥቅስ የተጻፈው በነጠላ ግስ፣ “አሟሟቱ” (“בומתו”) ተብሎ ነው።

፪.የሰባ ሊቃናት ትርጕም አዘጋጆችም የዕብራይስጡ ምንባብ፣ ስለ አንድ አካል እየተናገረ መኾኑን በመረዳት፣ በነጠላ “አሟሟቱ” ( ἀντὶ τοῦ θανάτου “አንቲ ቱ ታናቱ” ) ብለው ተርጒመው አስቀምጠዋል።

፫.ታርጒም ዮናታን ቤን ዑዝኤል ወደ አረማይክ በተተረጐመው ሥራ አሟሟቱ ብሎ በነጠላ (בְמוֹתָא) ገለጸው እንጂ፣ በብዙ ቊጥር (בְמוֹתָיא) ክፍሉን አላስቀመጠውም።

ይቀጥላል።

1.Michael L. Brown, Answering Jewish Objections to Jesus, Volume Three – Messianic Prophecy Objections: ገጽ. 49-57.

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 03:23


በእንተ ኢሳይያስ 53

ክፍል ኹለት
(በወንድም ሚናስ)

በስመ እግዚአብሔር መሓሪ ወመስተሣህል

የክርስትናን አስተምህሮ የማይቀበሉና የማያምኑ ይሁዲ ወገኖቻችን፣ ምዕራፉ ስለ መሲሑ ሳይኾን ሕዝበ እሥራኤልን ይመለከታል፤ ለማለት ምርኵዝ ከሚያደርጐቸው ምንባባት መኻከል ደግሞ ፣ በዛሬው ጥናታችን አንዱን የምንመለከት ይኾናል።

ቊጥር ስምንት

“በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኀጢአት ተመቶ፣ ከሕያዋን ምድር #ርሱ እንደ ተወገደ፣ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?”
מֵעֹ֚צֶר וּמִמִּשְׁפָּט֙ לֻקָּ֔ח וְאֶת־דּוֹר֖וֹ מִ֣י יְשׂוֹחֵ֑חַ כִּ֚י נִגְזַר֙ מֵאֶ֣רֶץ חַיִּ֔ים מִפֶּ֥שַׁע עַמִּ֖י נֶ֥גַע #לָֽמוֹ

ከላይ በተመለከትነው ቊጥር የይሁዲ ወገኖቻችን ሙግት የሚከተለው ነው፤ ክርስቲያኖች “ርሱ” ብለው በነጠላ ተውላጠ ስም የተረጐሙት ቃል לָֽמוֹ “ላሞ” የሚል የብዜት ቃል ሲኾን ትርጒሙ “እነርሱ” ማለት እንጂ “ርሱ” ማለት አይደለም፤ ስለዚህ ትንቢቱ ለብዜት አካላት እንጂ፣ አንድን ግለሰብ ለማመልከት የተነገረ አይደለም ይላሉ። ኾኖም ግን ይህ ይሁዲ ወገኖቻችን ሙግት ቢያንስ በሚከተሉት ሦስት መሠረታዊ ምክንያቶችን ያላገናዘበ ነው።

፩. לָֽמוֹ “ላሞ” የሚለው ተውላጠ ስም ብዜትን ኾነ፣ ነጠላ ቊጥርን ሊያመለክት የሚችልበት አግባብ አለ፤ ለምሳሌ በዚሁ በትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል לָֽמוֹ “ላሞ” የሚለው ተውላጠ ስም ነጠላ አካልን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል፤ አስረጅ፦ “...ከዚሁ ጠርቦ አምላክ ያበጃል፤ ያመልከዋል፤ ጣዖትን ይሠራል፤ ወድቆም #ለርሱ(ላሞ) ይሰግድለታል።” ኢሳ.44፥15

፪.የሰባ ሊቃናት ትርጒምም “ወደ ሞት ተወሰደ” (εἰς θάνατον “ሄይስ ታናቶን”) ብሎ በነጠላ ሐረግ አስቀመጠው እንጂ፣ “ወደ ሞት ተወሰዱ” ብሎ ክፍሉን በብዜት ሐረግ አልተረጐመውም ።

፫. ዐዲሱ የአይሁዳውያን ማኅበር ትርጒም ፣ በመባል የሚታወቀውና በአይሁዳውያን ሊቃውንት በተዘጋጀው ቅጂ፣ עַמִּ֖י נֶ֥גַע לָֽמוֹ “ዓሚይ ኔጋዕ ላሞ” የሚለውን የዕብራይስጥ ሐረግ፣ “ስለ ሕዝቡ ተመቶ” በማለት አንድን አካል በሚመለከት መልኩ ተተርጒሞ እናገኛለን።

ይቀጥላል።

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 03:22


በእንተ ኢሳይያስ 53
ክፍል አንድ

(በወንድም ሚናስ)

በስመ እግዚአብሔር መሓሪ ወመስተሣህል

ኢሳይያስ 53 ስለ መሲሑ ሞት እና ቤዛነት የሚናገር ድንቅ ምንባብ ቢኾንም፣ በዘመነኞቹ የይሁዲ ቤተ እምነት አማኒያን ዘንድ፣ ምዕራፉ እየተናገረ ያለው ስለ መሲሑ ሳይኾን፣ ሕዝበ እሥራኤል በዓለም ስለሚደርስበት መከራ የሚመለከት ትንቢት ነው ብለው ይከራከራሉ፤ ኾኖም ግን የዚህን ትርጓሜ ትኽክለኝነት ለማጣራት ከምዕራፉ ዐውድ ውጪ ወጣ በማለት እንደ ሚሽና፣ ታልሙድ፣ ሚድራሺም...ወዘተ ያሉ ጥንታዊ የይሁዲ መዛግብቶችን ብንመለከት ትንቢቱ ስለ ሕዝበ እሥራኤል ሳይኾን፣ በተቃራኒው ስለ መሲሑ የሚናገር መኾኑን ከትበው አስቀምጠዋል። ይህ ብቻም አይደለም፣ ከመኻከለኛው ክፍለዘመን በፊት የነበሩ የአይሁድ ሊቃውንት ዘንድ ስለ ሕዝበ እሥራኤል የተነገረ ነው የሚለው አንድምታ የማይታወቅ ባዕድ ትርጓሜ ነበር ። ለምሳሌ በ1050 ዓ.ም አካባቢም ረሺ ኢሳይያስ 53፣ ስለ ሕዝበ እሥራኤል የተነገረ ትንቢት እንደኾነ ሲናገሩ፣ እንደ ማይሞኒደስ ያሉ ስመጥር የአይሁድ ረቢዎች ይህ ዐዲስ ትርጓሜ እንጂ የጥንታዊ ሊቃውንትን አንድምታ ያላገናዘበ መኾኑን በመናገር ስሕተት መኾኑን አረጋግጠዋል። ጥንታዊ ረበናተ አይሁድ ይህ ትንቢት ለነጠላ አካል እንጂ፣ ለብዜት የተነገረ አለመኾኑን ከተናገሩት መኻከል የተወሰኑትን ለመመልከት ያኽል፦

°ታርጒም ዮናታን ኢሳይያስ 53 ስለ መሲሑ መኾኑን ተናግሯል፤ (ለነጠላ አካል መኾኑን ልብ ይሏል)።

°ታልሙድ በዐውዱ የተጠቀሱትን ዐሳቦችን ከመዘርዘር ባለፈ በአንድም ቦታ ላይ ኢሳይያስ 53 ሕዝበ እሥራኤልን የሚመለከት ነው አላለም።

°የኢየሩሳሌም ታልሙድ ኢሳ. 53፥12 ለረቢ አኪቫ የሚመለከት ሲኾን(Tractate Shekalim 5:1)፣ የባቢሎናዊው ታልሙድ ደግሞ ኢሳ.53፥4 ለመሲሑ(Sanhedrin 98b)፣ ቍጥር 10 (Berakhot 5a) እና ቍጥር 12 (Tractate Sotah 14a) ደግሞ ለሊቀ ነብያት ሙሴ ይጠቀማል። ሚድራሽ ራባህ ደግሞ ኢሳ.53፥5 መሲሓዊ ትንቢት መኾኑን ሲናገር (Ruth Rabbah 2:14)፣ ዐውደ ንባቡ ሕዝበ እሥራኤልን የሚመለከት ነው አላለም።

ይቀጥላል።

@Who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 02:27


የኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት 👈

I. ኢየሱስ ማን ነው? ፦
https://t.me/who_is_jesus/379

II. የክርስቶስ ህይወት ፦

ከታሪክ መጻሕፍት፦
https://t.me/who_is_jesus/389

➡️ ከወንጌላት፦
https://t.me/who_is_jesus/401

➡️ ኢየሱስ የኖረበት መልክዓ ምድር
https://t.me/who_is_jesus/410

III. ስለ ኢየሱስ የመማር አስፈላጊነት
https://t.me/who_is_jesus/420

IV. የኢየሱስ መለኮታዊ ማንነት

4.1 ➡️ ኢየሱስ "የእግዚአብሔር ቃል"
[The word of God]
https://t.me/who_is_jesus/435

1ኛ፦ [ዘላለማዊ]
[ETERNAL]
https://t.me/who_is_jesus/439

2ኛ፦ [የራሱ የሆነ ማንነት]
[PERSONALITY]
https://t.me/who_is_jesus/446

3ኛ፦ [ፍጹም አምላክ]
[GOD]
https://t.me/who_is_jesus/462

4.2 ➡️ "ኢየሱስ ጌታ ነው"
[JESUS IS LORD]
https://t.me/who_is_jesus/502


የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ:-
https://t.me/who_is_jesus/521


"የእኛ ሰፈር ይለያል"
https://t.me/who_is_jesus/523


"ዋጋን ማወቅ"
https://t.me/who_is_jesus/529


"ማቴ 28:19"
https://t.me/who_is_jesus/533


"ጥያቄዎቻችሁ እና መልሶቻቸው"
▶️ ክፍል 1
https://t.me/who_is_jesus/538

▶️ ክፍል 2
https://t.me/who_is_jesus/539


"ከእኔ አብ ይበልጣል?"
https://t.me/who_is_jesus/540


"ቅዱስ/ቅዱሳን - ቃዶሽ/ቄዶሽይም"
https://t.me/who_is_jesus/545


"ስላሴ"
https://t.me/who_is_jesus/546


"ክርስቶስ ሰው መሆኑ ፍጡር መሆኑን ያሳያልን?"
https://t.me/who_is_jesus/547


ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ባህሪ አምላክ መቀበል ለደኅንነት ግድ ነው?
https://t.me/who_is_jesus/548


1ኛ ቆሮንቶስ 8:6
https://t.me/who_is_jesus/549


"ግብረ- ሰዶም"
https://t.me/who_is_jesus/550


"ኢየሱስ ዘላለማዊ አምላክ ወይስ ሰው ብቻ?" 🎵🔊
https://t.me/who_is_jesus/551


"አስደናቂው መሲሐዊ ትንቢት"
https://t.me/who_is_jesus/552


"ከታሪክ ማህደር"
https://t.me/who_is_jesus/556


"ሰማያዊው እና ምድራዊው ያህዌ"
https://t.me/who_is_jesus/563


"መዳን በሌላ በማንም የለም" ሐዋ 4:12
https://t.me/who_is_jesus/564


"የማይገባ ደግነት"
https://t.me/who_is_jesus/566


"ማንኛውም ነገር በስሜ ብትለምኑ. . ." ዩሐ 14:14
https://t.me/who_is_jesus/569


"የዘላለም አባት"
https://t.me/who_is_jesus/570


"የህዝቡን ኃጢአት የተሸከመ አምላክ"
https://t.me/who_is_jesus/571


"ምን ይሻለን ይሆን?" ከተስፋዬ ሮበሌ
https://t.me/who_is_jesus/572


"የእግዚአብሔር ልጅ ክብር በዕብራውያን ፩"
https://t.me/who_is_jesus/573


"ልጁን ሳሙት"
https://t.me/who_is_jesus/574


"አእማሬ ኩሉ ኢየሱስ"
https://t.me/who_is_jesus/575


"ያህዌ ጽድቃችን"
https://t.me/who_is_jesus/576


"ሁሉ በእርሱ፤ ሁሉ ለእርሱ" ቆላስያስ 1:16
https://t.me/who_is_jesus/579


"በመልካችን እንደ ምሳሌአችን. . ." ዘፍ 1:26
https://t.me/who_is_jesus/580


"ወልድ ትንሹ ብርሃን ተብሏልን?"
https://t.me/who_is_jesus/588


"እውን ቅዱስ 'መላጥዮስ ዘሰርዴስ' አርዮሳዊ ነበርን?"
https://t.me/who_is_jesus/589

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:51


"ኢየሱስ : የእግዚአብሔር : ልጅ : እንደሆነ : ከሚያምን : በቀር : ዓለምን : የሚያሸንፍ : ማነው?"

፩ኛ ዮሐ ፭፥፭

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:36


እውን ቅዱስ መላጥዮስ ዘሰርዴስ አርዮሳዊ ነበር?
( ሚናስ)

አውሳቢዮስ ዘቄሳሪያ በተባለው የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ታሪክ ጸሓፊ ዘገባ መሠረት፣ ቅዱስ መላጥዮስ ከ ፻፳ እስከ ፻፹፭ ዓ.ም በምድር ላይ የኖረ፣ በዘመኑም የሰርዴስ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የነበረ አባት ነው[፩]፤ እናም በመላጥዮስ ዘሰርዴስ የእምነት አቋም መሰረት፣ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “በማንነቱ ፍጹም አምላክ እና ፍጹም ሰው(θεός ὡς φύσει καί ἄνθρωπος)” የሆነ [፪]፣ “አልፋና ኦሜጋ”፣ ደግሞም “በአብ ቀኝ የተቀመጠ”[፫]፣ ቅድመ-ሥጋዌ በሰማያት የነበረ፣ ስለ ሰዉ ልጆች ኃጢአት ሲል ከድንግል ሥጋን ለብሶ (σαρκόω) መከራን የተቀበለ [፬]፤ የዓለማት ገባሬ ፈጣሪ የኾነ [፭]...ወዘተ፣ መኾኑን በተደጋጋሚ ገልጿል። ሆኖም ግን ቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶች በተጠቀሱ ቍጥር “የኛ ናቸው” በሚል ትርክት ከሚታወቁት የነጠላ አሓዳውያን (''Biblical'' Unitarian) ‛ሊቃውንት’ መካከል አንዱ የኾነው ዶ/ር ዳል ታጊ፣ መላጥዮስ ዘሰርዴስ በክርስቶስ አምላክነት በፍጹም እንደማያምን፣ እንዲያውም የአርዮሳውያን አይነት ምን*ቅና እንደሚያዜም አድርገው እንዲኽ በማለት ይገልጹታል፦

“መላጥዮስ ‛ኢየሱስ የእግዚአብሔር በኵር የሆነና ከንጋት ኮከብ በፊት የተወለደ ነው’ ሲል ይናገራል። ስለዚኽ በሜሊቶ እምነት መሰረት ወልድ ኹለተኛ ደረጃ ያለው መለኮት ነው። አምላክ የመፍጠር ጊዜው በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ይኽን ኹለተኛ እና ትንሹን መለኮታዊ አካል (ወልድን) እንደ ፈጠረም ያምን ነበር ”[፮] ይላሉ።

እኒህ አርዮሳዊ ጸሓፊ የመላጥዮስ ሓሳብ እንዴት አጣመው እንዳቀረቡት በቀጥታ እንመልከት፤ መላጥዮስ ጌታችንን “የእግዚአብሔር በኩር” (πρωτότοκος τοῦ θεοῦ) ማለቱ፣ የጌታን ፍፁም የበላይነትን የሚያመለክት እንጂ የፍጡርነት መጠሪያ ሊሆን የማይችልበት የመጀመሪያው ምክንያት ፣ ዐውዱ ፍጥረታት የኢየሱስ ግኝት እንደሆኑ የሚገልጽ በመኾኑ ነው[፯]፤ ኹለተኛው ምክንያቱ ደግሞ “በኵር”( ጽርእ πρωτότοκος “ፕሮቶቶኮስ”) የሚለው ቅጽል፣ አስቀድሞ የተወለደን ልጅ ሊያመለክት የሚችልበት አግባብ ቢኖርም፣ በዐውዱ መሰረት ሥልጣንን፣ የበላይነትን፣ ተወዳጅነትንና፣ ልዩ የሆነ ግንኙነትንም ለማሳየት የሚገባ ቃል ነው። ለአብነት ተከታዮቹን ጥቅሶች እንመልከት፣ “ያዕቆብም። በመጀመሪያ ብኵርናህን (πρωτοτόκιά) ሽጥልኝ አለው።”[፰]፤ በዚኽ ክፍል በሰብዓ ሊቃናት የብሉይ ኪዳን ትርጕም πρωτοτόκιά “ፕሮቶቶኪያ” የሚለው ብኩርናን የሚያመለክተው ቃል የገባው ሥልጣንን ለማሳየት እንጂ መጀመሪያ መወለድን ለማሳየት አይደለም። በትንቢተ ኤርምያስ ውስጥም ተመሳሳይ ሓሳብ እናገኛለን፤ “በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም *በኵሬ* (πρωτότοκός) ነውና።” [፱] ፤ ልብ ይበሉ ኤፍሬም ሁለተኛው የዮሴፍ ልጅ መኾኑ በሌላ የመጽሓፍ ቅዱስ ምንባብ ተጠቅሷል[፲]፡፡ ከዚህ ክፍል የምንረዳው የኤፍሬምን ቀድሞ መፈጠር ወይንም መወለድ ሳይሆን እግዚአብሔር ኤፍሬምን ልዩ በሆነ ዓይን እንደሚያይና ከሌሎች በላይ እጅግ በእግዚአብሔር የተወደደ መሆኑን ነው።  ስለዚኽ መላጥዮስ ዘሰርዴስ “በኵር” (πρωτότοκος “ፕሮቶቶኮስ”) የሚለውን ቃል ለክርስቶስ መጠቀሙ፣ አርዮሳውያን እንደሚያምኑት ቀድሞ የተፈጠረ ለማለት ሳይሆን፣ ክርስቶስ የፍጥረታት ሁሉ ወራሽና ባለቤት መሆኑን ለመግለጽ የታለመ ነው፡፡  “ከንጋት ኮከብ በፊት የተወለደ” የሚለውን መላጥዮስ የጠቀሰው፣ ከመዝሙር 109፥3 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ሲሆን፣ ይኽ ጥቅስ መላጥዮስ የተጠቀመው የወልድን ጅማሬ ለማሳየት ሳይኾን ከመወለዱ በፊት ስላለው ዘላለማዊ ሀልዎቱ ለመግለጽ ነው፤ “..የአብ አንድያ ልጅ በሚሆን፣ ዓለም ሳይፈጠር ከአብ በተወለደ..” (..τοῦ Θεοῦ τὸν Μονογενῆ,τὸν ἐκ τοῦ Πατρὸς γεννηθέντα πρὸ πάντων τῶν αἰώνων..) የሚለውን የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ ልብ ይሏል! ስለዚኽ በአጠቃላይ መላጥዮስ ዘሰርዴስ ርቱዕ የኾነውን፣ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮትነት የሚያምን አባት እንጂ፣ መናፍ*ቃን እንደሚሉት አርዮሳዊ አቋም አልነበረውም።

ዋቢ መዛግብት
----------------------
፩.Eusebius, Church HistoryV.24
፪.Peri Pascha v. 8.
፫.ዝኒ ከማሁ v. 105.
፬.ዝኒ ከማሁ v. 70.
፭. ዝኒ ከማሁ v . 66.
፮.Dale Tuggy. 09/14/2020. “Podcast 303: Rauser’s review of Is Jesus Human and not Divine?,” Trinities. https://trinities.org/blog/podcast-303-rausers-review-of-is-jesus-human-and-not-divine/
፯.Peri Pascha v. 104
፰.ዘፍ 25:31
፱.ኤርሚያስ 31፥9
፲.ዘፍጥረት 49፡13-19

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:32


ወልድ ትንሹ ብርሃን ተብሏልን ?
(በወንድም ሚናስ )

“በሥላሴ ማመን ይገባሀልን?” በሚል ርዕስ ፣ የመጠበቂያ ግንብ የመጽሐፍ ቅዱስና የትራክት ማሕበር ያሳተመው አነስተኛ መጽሓፍ ላይ ፣ ከኒቂያ ጉባኤ በፊት የነበሩ ፣ ቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶች ፣ የክርስቶስን አምላክነት የማይቀበሉ አርዮሳውያን መኾናቸውን ይገልጻል ። እናም ይኽ ድርጅት ፣ የክርስቶስ መለኮትነት አይቀበሉም ብሎ ከዘረዘራቸው የቤተክርስቲያን አበው መካከል ስመጥሩ የእስክንድርያው ሊቅ አርጌንስ ተጠቃሽ ነው፤ ድርጅቱ ሊቁን አስመልክቶ የሚከተለውን ጽሑፍ አስፍሯል፦

“ በ250 ዓ.ም የሞተው ኦሪገን ከአብ ጋር ሲወዳደር ወልድ በጣም ትንሹ ብርሃን ነው ሲል ገልጿል”[፩]

ይኽ Against Celsius ከተሰኘው ፣ የአርጌንስ መጽሓፍ የተወሰደ ሲሆን ሙሉ ዐውዱን እንመልከት፣

“እነዚያ ፀሐይን፣ ጨረቃን እና ከዋክብትን የሚያመልኩ፣ ብርሃናቸው ብሩህ ስለሆነ ፣ በምድር ላይ ላለ ለእሳት ብልጭታ አይሰግዱም ፤ ምክንያቱ ደግሞ ክብር ይገባቸዋል ፣ ተብለው የሚታሰቡት ፀሐይና ጨረቃ በአንጻራዊነት ወደር የለሽ ብልጫን ስላዩ ነውና ። ታዲያ እግዚአብሔር ብርሃን እንደሆነ ፣ እንዲሁም ልጁ ፣ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ” ማለቱን የተረዱ ፣ የእውነተኛው ብርሃን ምንጭ ከኾነው ከእግዚአብሔር ጋር ሲወዳደር በፀሐይ፣ በጨረቃና በከዋክብት መመካት ኢምንት የሆነ ትንሽ ብርሃን ነው ።”[፪]

የመጠበቂያ ግንብ ጸሓፊያን የአርጌንስ ዘእስክንድርያ ነጥብ ኾነ ብለው በተሳሳተ መንገድ ተርጉመውታል ። ይኸውም ፣ አርጌንስ እየተናገረ ያለው ፀሐይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን የሚያመልኩ ከእውነተኛውና ከከበረው ከአብና ከወልድ ብርሃን ጋር ሲነጻጸሩ ኢምንትና እጅግ አነስተኛ ብርሃንን እያመለኩ ነው እያለ ነው ። ሊቁ አርጌንስ በማስከተል ወዲያውኑ እንዲህ ይላል፦

“የእግዚአብሔር እና የአንድያ ልጁ መለኮትነት ከሌሎች ነገሮች ሁሉ የላቀና የማይገለጽ መሆኑን እናስተውላለን።”[፫]

በመጨረሻም አርጌንስ፣ አረማውያን ከዋክብትን ከማምለክ እንዲመለሱ በማሳሰብ ክፍሉን እንዲኽ በማለት ያጠናቅቃል፦

“ማዳን ወደሚችለው ወደ እግዚአብሔር ቃል (ወልድ) እንዲሁም ወደ አባቱ ጸልዩ፤ የቀደሙት ጻድቃን ‘ቃሉን ላከ፣ ፈወሳቸውም፣ ከጥፋታቸውም አዳናቸው’። ተብሏልና”[፬]

ልብ ይበሉ ! አርጌንስ ከላይ ባለው ንግግሩ ወደ ወልድ (የእግዚአብሔር ቃል) እንዲሁም ወደ አብ መጸለይ እንዳለባቸው እያሳሰበ ነው ። ስለዚኽ ይኽ ክፍል የክርስቶስን አምላክነት ከማስተባበያነት ይልቅ መለኮትነቱን የሚያረጋግጥ ሆኖ እናገኘዋለን ።

ዋቢ መዛግብት

፩.በሥላሴ ማመን ይገባሃልን ገጽ ፯
፪.Origen, Against Celsus, Book 5, Chapter 11
፫.ዝኒ ከማሁ
፬.ዝኒ ከማሁ

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:27


የተቀደሰ ስም ያለህ እግዚአብሔር አብ ሆይ የብርሃንህ ጎርፍ፣ የፍቅርህ ጠል፣ የበረከትህ ዝናብ በእኔና የእኔ በሆኑት ላይ ይፍሰስ። አንተ እንዴት እንደምታስተዳድር ለአስተዳዳሪዎች ፣ እንዴት እንደምታኖር ለአባወራዎች ፣ እንዴት እንደምታሳድግ ለሞግዚቶች ፣ እንዴት እንደምትጠብቅ ለጠባቂዎች ፣ እንዴት እንደምታፈቅር ለአፍቃሪዎች ፣ እንዴት እንደምትሰጥ ለለጋሾች ግለጥላቸው ። በልጅህ በወዳጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ያለ ከሃሊነትና ክብር ላንተ ለመንፈስ ቅዱስም ይገባል ለዘላለሙ አሜን።

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:27


ይኽ መጣጥፍ ፣ የይሁዳ መልዕክት ምዕራፍ ፩ ላይ በመንተራስ ፣ የክርስቶስ አምላክነትን ፣ የሚያትት ዐዲስ ጽሑፍ ነው ። ሊንኩን በመጫን ሙሉ መጣጥፉን ያንብቡ ። http://ewnetlehulu.net/jude-christology/

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 01:08


የክርስቶስን አምላክነት አስመልክቶ የዕብራይስጥ ቅዱሳት መጻሕፍትን ዋቢ በማድረግ ያቀረብኳቸው አራት ተከታታይ መጣጥፎች እነሆ! የመጣጥፎቹ ዓላማም መሲሑ በሥጋ የተገለጠ ያህዌ መሆኑን ማሳየት ሲሆን፣ አርዮሳውያን፤ ነጠላ አሐዳውያን('Biblical' Unitarian) ከመሳሰሉት የኑፋቄ ቡድኖች ወይም ከሙስሊም ወገኖቻችን ጋር፣ ስለ እምነታቸው መወያየት የሚፈልጉ ክርስቲያኖችን ለመጥቀም በማለም የተዘጋጁ ናቸው። እርስዎም ይህንን መጣጥፍ በማካፈል ሌሎች ወገኖች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የበኩለዎን ይወጡ ዘንድ እጋብዛለሁ። ተባረኩ!

ክፍል ፩፦ http://www.ewnetlehulu.org/am/deity-of-the-messiah-hebrew/

ክፍል ፪፦ http://www.ewnetlehulu.org/am/deity-of-the-messiah-hebrew-2/

ክፍል ፫፦ http://www.ewnetlehulu.org/am/deity-of-the-messiah-hebrew-3/

ክፍል ፬፦ http://www.ewnetlehulu.org/am/deity-of-the-messiah-hebrew-4/


@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:52


የእግዚአብሔር ልጅ ክብር
የዮሐንስ ወንጌል 5 ሐቲት፥ ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦ http://ewnetlehulu.net/the-glory-of-the-son/

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:48


እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።”
— ዘፍጥረት 1፥26

የእግዚአብሔርን ሥሉስ አሓዳዊነት ከሚያመለክቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል አንዱ ከላይ ያነበብነው ጥቅስ ነው። እግዚአብሔር አብ ዓለማትን በልጁ መፍጠሩን (ዕብ1፥2፤ ዮሐ1፥3፤ ቆላ1፥16-17) እንዲሁም ደግሞ ፍጥረትን በማስገኘት ሒደት መንፈስ ቅዱስ ጉልሕ አስተዋጽኦ እንዳለው ቅዱሳት መጻሕፍት አበክረው ይነግሩናል (ዘፍ 1፥3 ፤ ኢዮ33፥4)። በዘፍጥረት 1፥26 ላይም በብዙ ቁጥር ግስ “እንፍጠር” (נַעֲשֶׂה “ናዓሳህ”) በብዙ ቁጥር ስሞች “በመልካችን” (בְּצַלְמֵ֖נוּ ቦጼሌሜኑ) እንዲሁም “ምሳሌአችን” ( כִּדְמוּתֵנוּ ” ኪዴሙቴኑ”) ማለቱ አሐዱ ሥሉስን እንደሚያመለክት ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሑራን የሚስማሙበት እውነታ ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህንን እውነታ የተቃወሙ የእምነት ቡድኖችም ሆኑ ግለሰቦች አልታጡም። ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦ http://www.ewnetlehulu.org/am/genesis-1-26/

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:42


በእንተ ቆላስይስ 1፥16
(በወንድም ሚናስ)

የአይሁዳውያን መሠረተ እምነት ከሆኑት ዶግማዎች መካከል በቀዳሚነት የሚሰለፈው የእግዚአብሔር ብቸኛ ፈጣሪነት ነው። የብሉይ ኪዳንም የመጀመሪያ ክፍል የእግዚአብሔርን አስገኚነት በመናገር የሚጀምረው በዚህ አግባብ ነው(ዘፍ 1፥1)። ኢሳይያስም በትንቢቱ የዘፍጥረት 1፥1 ምንባብ በሚያጸና መልኩ ይኽን ይላል፣ “ብቻዬን ሰማያትን የዘረጋሁ፣ ምድርን ያንጣለልሁ፣ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤”(ኢሳ. 44፡24)። ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ ደግሞ ሁሉም ነገር የተፈጠረው በእግዚአብሔር ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ እንደሆነ ንዋይ ሕሩይ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ያረጋግጥልናል፦

“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለ ሥልጣናት፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16

ከላይ ባለው በጥቅሱ ውስጥ ሐዋርያው “ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል”(ἐν αὐτῷ ἐκτίσθη τὰ πάντα ) ይለናል፡፡ ይኸውም በእግዚአብሔር አብ ልጅ ዓለማት መፈጠሩን እናም ልጁ ኢየሱስ ልክ እንደ አባቱ የአምላክነት ተግባርን ይከውን እንደነበር ያስገነዝበናል። ሆኖም የክርስቶስን አምላክነት የማይቀበሉ ወገኖች በሚከተለው ሙግት በቆላስይስ 1፥16 የተጠቀሰውን የጌታችንን ፈጣሪነት ለማስተባበል ይሞክራሉ። ይኸውም፤ “' ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል' የሚለው አዲስ ፍጥረትን የሚያመለክት እንጂ ክርስቶስ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣቱን የሚያመለክት አይደለም” የሚል ነው።
 
ከላይ የሚገኘው ሙግት ቢያንስ ሶስት መሠረታዊ ነጥቦችን ያላገናዘበ ነው። ይኸውም፤

1ኛ. መናፍቃን ይህ ትርጓሜያቸው የቋንቋ (Linguistic approach) ድጋፍን መሠረት ያላደረገ ነው። ምክንያቱም ἐκτίσθη “ኤክቲስቴ” የሚለው ቃል ቊማዊ ፍጥረትን እንጂ በፍጹም ተምሳሌታዊ ገለጻን ለማመልከት ግልጋሎት ላይ አይውልም[1]። ይህ ማለት የመና*ቃን ሙግት ከጅምሩ ወንዝ የማያሻግር ሆኖ ይቀራል ማለት ነው።

2ኛ.ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ 11፥36 የአብ ፈጣሪነትን የገለጠበትን ምንባብ ከቆላስያስ 1፥16 ጋር በትይዩ ተመልከት፤

አብ፦
“#ሁሉም(τὰ πάντα) ከእርሱ፣ #በእርሱ(δι’ αὐτοῦ)፣ #ለእርሱ(εἰς αὐτὸν) ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— ሮሜ 11፥36 (አዲሱ መ.ት)

ወልድ፦
“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለ ሥልጣናት፣ #ሁሉም(τὰ πάντα) ነገር #በእርሱና(δι’ αὐτοῦ) #ለእርሱ(εἰς αὐτὸν) ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16 (አዲሱ መ.ት)

በሁለቱም ጥቅሶች ውስጥ “ሁሉም” (τὰ πάντα “ታ ፓንታ”) ፤ “በእርሱ” ( δι’ αὐτοῦ ዲ አውቱ)፤ “ለእርሱ” (εἰς αὐτὸν ሔይስ አውቶን)፤ የሚሉትን ቃላቶችን ተጠቅሞአል። ስለዚህ ቆላስይስ 1፥16 ላይ የወልድን ፈጣሪነት አያሳይም ካሉን፣ በተመሣሣይ የሮሜ 11፥36 ምንባብም እንዲሁ የአብን ፈጣሪነት አያሳይም ብለው መደምደም ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ሐዋርያው ለሁለቱም አካላት ተመሣሣይ ሰዋስዋዊ ውቅር ተጠቅሞአልና።

3ኛ.የመናፍቃን ችግር ሐዋርያው በክርስቶስ ተፈጠሩ የሚለን በሰማይ የሚኖሩ ገዢዎች እና ሥልጣናትን መሆኑን አለማስተዋል ነው።

“ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሮአል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት፣ ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ *ገዦች*(ἄρχαι) ቢሆኑ ወይም *ባለ ሥልጣናት*(ἐξουσίαι)፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል።”
— ቆላስይስ 1፥16

ጳውሎስ በሌላ ጽሑፉ ላይ ክርስቲያኖችን የሚዋጉ ዓመፀኛ መናፍስት ፍጥረታትን በሚመለከት “ገዦች ” እና “ሥልጣናት” የሚሉትን ቃላት ተጠቅሟል።

“ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን ከዚህ ከጨለማ ዓለም *ገዦች*(τὰς ἀρχάς)፣ *ከሥልጣናትና*(τὰς ἐξουσίας) ከኀይላት እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው።”
— ኤፌሶን 6፥12 (አዲሱ መ.ት)

ይኽም ማለት ኢየሱስ ቅዱሳን ሆነ እርኩሳን መናፍስትን የፈጠረ አምላክ መሆኑን በግልጽ ያመለክታል።በአጠቃላይ ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስን የበላይነት፣ አድራጊ ፈጣሪ መሆኑን በግልፅ እየተረከልን ነው። እርሱ ተራ መልአክ ወይም ተራ ሰው አይደለም፣ ነገር ግን ከሁሉም በላይ የሆነ፣ ሊመለክ የሚገባው ፈጣሪ ነው። ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘለዓለም ክብር ይሁን! የሚያመልከው አሜን ይላል።


[1] መጽሐፈ ጥበብ 1፥14፤ 10፥1፤ 11፥18፤ ዘዳግም 4፥32፤ ዘፍጥረት 6፥7; ሲራክ 24፥9፣ ሲራክ 15፥14፤ መጽሐፈ ኢዮብ 13፥18፤1 ቆሮንቶስ 11፥9፤ ኤፌሶን 3፥9፤ ሮሜ 1፥25፤ ራእይ 10፥6፣ ራእ 14፥7

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:41


ከዚህ ቀደም “ያሕዌ ጽድቃችን” በሚል ርዕስ ያዘጋጀሁትን ጽሑፍ በማሕበራዊ ሚድያዎች ላይ ያነበበ አንድ ሙስሊም ሰባኪ ለጽሑፉ መልስ ብሎ ያዘጋጀውን መጣጥፍ አንድ ወዳጄ ልኮልኝ አንብቤያለሁ። ጽሑፉ በመጀመሪያው መጣጥፍ መልስ የተሰጠበትን ነጥብ የሚደግም ቢሆንም የክርስቶስን አምላክነት የሚክዱ ወገኖች እንዴት ያሉ ስሁት ሙግቶችን እንደሚጠቀሙ ለማሳየት ጥሩ ምሳሌ ሆኖ ስላገኘሁት መልስ ሰጥቼበታለሁ። የቀድሞ ጽሑፌን እንዲሁም ለሙስሊሙ ሰባኪ የሰጠሁትን ምላሽ በአንድ ላይ በዚህ ሊንክ ይገኛሉ፦ http://ewnetlehulu.net/yahweh-our-rightousness/

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:32


<<ያሕዌ ጽድቃችን>> ❗️
(በወንድም ሚናስ)

እንደሚታወቀው ብሉይ ኪዳን፣ ስለ መሲሑ አያሌ ትንቢቶችን የሸከፈ መጽሐፍ ነው። በብዙኃን ዘንድ በዋነኝነት በመዝሙረ ዳዊት እና በትንቢተ ኢሳይያስ ያሉ ክፍሎች በተደጋጋሚ ቢጠቀሱም፣ ሌሎች ምንባባትም ስለ መሲሑ በርካታ ትንቢቶችን እንዳሰፈሩ መዘንጋት የሌለበት እውነት ነው። ከእነዚህም ውስጥ የነብዩ ኤርምያስ ትንቢት ተጠቃሽ ነው። ለዛሬ በምዕራፍ 23፥5-6 ያለውን ጥቅስ እንመለከታለን፦

ኤርምያስ 23፥5-6፦ “እነሆ፤ ለዳዊት፣ ጻድቅ ቅርንጫፍ(צָמַח) የማስነሣበት ጊዜ ይመጣል፤ እርሱም ፍትሕንና ጽድቅን የሚያደርግ፣ በጥበብ የሚገዛ ንጉሥ ይሆናል” ይላል እግዚአብሔር። በእርሱም ዘመን ይሁዳ ይድናል፤ እስራኤልም በሰላም ይኖራል፤ የሚጠራበትም ስም፣ 'ያህዌ ጽድቃችን'( יְהוָה צִדְקֵנוּ) የሚል ነው።”

እንግዲህ በዚህ አነስተኛ መጣጥፍ ውስጥ፣ “ቅርንጫፍ” የሚለውን ቃል ትርጓሜ፣ እንዲሁም “ያህዌ ጽድቃችን” የሚለው ቃል መሲሑ አምላክ መሆኑን እንዴት እንደሚያመለክት እናትታተን፤

1. “ቅርንጫፍ” (צֶ֣מַח) የሚለው ቃል ትርጉም።

በብሉይ ኪዳን በተለይም በትንቢተ ኤርሚያስ እና በመዝሙረ ዳዊት ላይ “ቅርንጫፍ” (በዕብራይስጥ፦ צֶ֣מַח “ጻማዕ”) የሚለው ስም መሲሑን ለማመልከት የሚያገለግል ተምሳሌታዊ ቃል መሆኑን ብዙ ሊቃውንት የሚስማሙበት ጉዳይ ነው[1]። ለምሳሌ መዝሙረኛው የተናገረውን እንውሰድ ፦

““በዚህም ለዳዊት ቀንድ *አበቅላለሁ*(אַצְמִ֣יחַ)፤ ለቀባሁትም ሰው መብራት አዘጋጃለሁ።”
— መዝሙር 132፥17 (አዲሱ መ.ት)

“አበቅላለሁ” ለሚለው የገባው የዕብራይስጥ ቃል אַצְמִ֣יחַ “ኣፄሚያ” የሚል ሲሆን የ צָמַח “ጻማዕ” አንደኛ መደብ ነጠላ ሲሆን፣ ዋና ትርጉሙም “ቅርንጫፍ” የሚል ነው። ይህንን ጥቅስ ሚድራሽ ታንኹማ የተሰኘ ጥንታዊ የአይሁድ መዛግብት፣ ይህ ቅርንጫፍ መሲሑ ነው ይለናል፤

“ለዳዊት ቀንድን አበቅላለሁ በዚያም ለቀባሁት መብራትን አዘጋጃለሁ (መዝ. 132:17) መባሉ መሲሑን ያመለክታል።”[2]

በተጨማሪም፤ በአረማይክ ታርጉም ላይ “በዚያን ቀን የእግዚአብሔር ቅርንጫፍ ያማረና የከበረ ይሆናል”(ኢሳ 4፥2) የሚለውን “በዚያን ቀን የእግዚአብሔር መሲሕ ያማረና የከበረ ይሆናል”፤ ሲል “እነሆ፤ ባሪያዬን ቊጥቋጡን አመጣለሁ።”(ዘካርያስ 3፥8) የሚለውንም “እነሆ፤ ባሪያዬን መሲሑን አመጣለሁ።” ብሎ አስቀምጧታል።

2.የሚጠራበት ስም “ያህዌ ጽድቃችን” ነው።

ኤርምያስ መሲሑን “ጻድቅ ቅርንጫፍ” ብሎ ከጠራው በኋላ፣ “ያህዌ ጽድቃችን” (ኤር 23፥6) መሲሃዊ ኑባሬውን ጠቅሷል። ይኼ በግልጽ የመሲሑን መለኮትነት እየተናገረ ነው። ሆኖም የመሲሑን አምላክነት የማይቀበሉ አይሁዳውያን ሆነ ሌላ የእምነት ቡድኖች የሚከተለውን ሙግት አዘውትረው ይጠቀማሉ። “ያህዌ ጽድቃችን” የሚለው የያህዌ ስም አጫፋሪ ስም ሆኖ የመጣበት መጠሪያ ነው፥ “ያህዌ ” አጫፋሪ ስም ሆኖ መግባቱ አምላክነትን ካሳየ፣ “ኤልያህ” (ያህዌ አምላኬ ነው)፤ “ኤርሚያህ”(ያህዌ ከፍ ያደርጋል)፤ “ኢሳይያህ ”(ያህዌ ያድናል)፤ ወዘተ... በመሰል ስሞች የተጠሩ ግለሰቦች ያህዌ ሊሆኑ ነው” ይሉናል። ይህ ግን ድኩም ሙግት ነው፣ ምክንያቱ ደግሞ ከላይ የተዘረዘሩት መጠሪያዎች “ያህ” በሚለው የያህዌ ምህፃረ ቃል ጋር የተጫፈሩ ስመ-ያህዌን የተሸከሙ መጠሪያ ናቸው።ይኸውም የኤልያስን፤የኢሳይያስን ወይም የኤርሚያስን ባህሪ ለመግለጽ የታሰቡ ሳይሆን፣ያመኑትን አምላክ የሚገልጹ ስሞች ናቸው። ነገር ግን በትንቢተ ኤርሚያስ መሲሑ “ያህዌ ጽድቃችን” መባሉ “ያህ” በሚል ከተጫፈሩት መጠሪያዎች ፈጽሞ የተለየ ነው። ምክንያቱ ደግሞ ኤርሚያስ በክፍሉ ባህሪው ጻድቅ መሆኑን እየነገረን ያለው መሲሑን እንጂ ሌላን ማንነት አይደለምና። ጥቅሱን በትኩረት እናንብብ፤

ኤርምያስ 23፥5-6 “እነሆ፤ ለዳዊት፣ #ጻድቅ _ቅርንጫፍ የማስነሣበት ጊዜ ይመጣል፤ እርሱም ፍትሕንና #ጽድቅን_ #የሚያደርግ፣ በጥበብ የሚገዛ ንጉሥ ይሆናል” ይላል እግዚአብሔር። በእርሱም ዘመን ይሁዳ ይድናል፤ እስራኤልም በሰላም ይኖራል፤ የሚጠራበትም ስም፣ ‘እግዚአብሔር_ #ጽድቃችን*’ የሚል ነው።” (አዲሱ መ.ት)

በአጭሩ ነብዩ እያለን ያለው መሲሑ በኑባሬው(በባህሪው) ጻድቅ ስለሆነ ጽድቅን ያደርጋል። ምክንያቱ ደግሞ እርሱ ጽድቃችን የሆነ ያህዌ በመሆኑ። ስለዚህም በትንቢተ ኤርሚያስ ውስጥ ያለው ክፍል መሲሑ ስሙ በትክክል የሚወክለው መለኮት መሆኑን እንገነባለን።

____
[1]The Moody Handbook of Messianic Prophecy, pg. 1014
[2] Midrash Tanchuma, Terumah 7:1

@who_is_jesus

ነገረ ክርስቶስ 🅒🅗🅡🅘🅢🅣🅞🅛🅞🅖🅨

20 Jan, 00:29


<<አእማሬ ኲሉ ኢየሱስ>> ❗️
(በወንድም ሚናስ)

እግዚአብሔር አምላክ ለነብያት ሆነ ለሌሎች ፍጥረታት በሚገልጥላቸው መጠን የተወሰኑ ያለፉ፤ ያሉ፤ እና መጻኢ ክንውኖችን ሊያውቁ ቢችሉም የፍጥረታትን ውስጠ-ምስጢር ሊረዳና ሊያውቅ የሚችለው ኤልሻዳይ ያህዌ ብቻ ነው። ሆኖም በሐዲሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሁሉ ልብ እንደሚያውቅ ይናገራሉ፤

ዮሐንስ 16፥30-31፦“አሁን *ሁሉን ነገር እንደምታውቅ* (ὅτι οἶδας πάντα) ማንም ሊጠይቅህ እንደማያስፈልግ ተረድተናል፤ ይህም ከእግዚአብሔር እንደ ወጣህ እንድናምን አድርጎናል። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “አሁንስ አመናችሁ ማለት ነው?”

ዮሐንስ 21፥17፦“ሦስተኛም ጊዜ፣ “የዮና ልጅ፣ ስምዖን ሆይ፤ ትወደኛለህን?” አለው። ጴጥሮስም ሦስተኛ ጊዜ ኢየሱስ፣ ‘ትወደኛለህን?’ ብሎ ስለ ጠየቀው ዐዝኖ፣ “*ጌታ ሆይ፤ አንተ ሁሉን ታውቃለህ*(κύριε, πάντα σὺ οἶδας)፤ እንደምወድህም *ታውቃለህ*(σὺ γινώσκεις) ” አለው። ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “በጎቼን መግብ።” (አዲሱ መ.ት)

“አሁን ሁሉን ነገር እንደምታውቅ(νῦν οἴδαμεν ὅτι οἶδας πάντα) እና ማንም ሊጠይቅህ እንደማያስፈልግ ተረድተናል(καὶ οὐ χρείαν ἔχεις ἵνα τίς σε ἐρωτᾷ ἐν τούτῷ πιστεύομεν)፤ ይህም ከእግዚአብሔር እንደ ወጣህ እንድናምን አድርጎናል።””
— ዮሐንስ 16፥30 (አዲሱ መ.ት)

ልብ በል ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ኹሉን አዋቂ መሆኑን ማመናቸው ብቻ ሳይሆን የማንም ሰው ጥያቄ አስፈላጊ አይደለም ወደሚል መደምደሚያ ደርሰዋል። ይህ የሚያሳየው ኢየሱስ ሁሉንም ነገር እንደሚያውቅ እርግጠኛ ስለሆኑ እውቀቱን ለመፈተሽ ተጨማሪ ጥያቄ ማቅረብ ከንቱ ድካም መሆኑን ስለተረዱ ነው። ታዲያ ቅዱስ ዮሐንስ የእግዚአብሔርን ኹሉን አዋቂነት ሲገልጽ ተመሳሳይ አገላለጽ ተጠቅሞአል፡-

1ኛ ዮሐንስ 3 ፥19፥20 “እኛ የእውነት ወገን መሆናችንን በዚህ እናውቃለን፤ ልባችንንም በፊቱ እናሳርፋለን፣ ይህም ልባችን በእኛ ላይ በሚፈርድብን ነገር ሁሉ ነው። እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና *ሁሉን ነገር ያውቃል*(καὶ γινώσκει πάντα) ።”(አዲሱ መ.ት)

አቡቀለምሲስ ቅዱስ ዮሐንስ ብቻም አይደለም፣ አዋልድ የአይሁድ መጻሕፍትም ሁሉን አዋቂ እግዚአብሔር ነው ይሉናል፦

መጽሐፈ ባሮክ3፥29-32 ““ወደ ሰማይ ወጥቶ ሕግን የተቀበላት ከደመናትና ያወረዳት ማነው።ባሕሩን ተሻግሮ ሄዶ ያገኛት በቀይስ ወርቅ ገዝቶ ያመጣትስ ማነው። ጐዳናዋን የሚያውቅ ፍለጋዋንም የሚያስብ ማነው። *ሁሉን የሚያውቅ*(ἀλλὰ ὁ εἰδὼς τὰ πάντα γινώσκει) ጌታ ያውቃታል ሰማይንና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔር በእውቀቱ አገኛት።”

ስለዚህ፣ “ሁሉ”የሚለው ቃል (በግሪኩ πᾶς“ፓስ”) ኢየሱስ ኹሉን ያውቃል ማለት ካልሆነ ኤልሻዳዩ ያህዌ ሁሉንም አያውቅም ወደሚል ድምዳሜ መድረሳችን ግድ ነው፤ ምክንያቱ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት የተጻፉ ቅዱሳት መጻሕፍት እና የአይሁድ አዋልድ መዛግብት እንደሚጠቁሙት የእግዚአብሄርንም ሆነ የክርስቶስን አዋቂነት ለመግለጽ ተመሳሳይ ቋንቋ ተጠቅመዋልና። ስለዚህ ከዚህ የምረዳው ከእግዚአብሔር ልዩ ባሕሪያት መካከል አእማሬ ኲሉ(ኹሉን ማወቅ) የክርስቶስ ኑባሬ መሆኑን እንረዳለን። ሆኖም ግን የክርስቶስን አምላክነት እንቅልፍ የነሳቸው የእምነት ጎራዎች “ሁሉን አዋቂነት ማለት የፍጥረታትን ውስጠ ምስጢር መረዳት ከሆነ ክርስቲያኖችም ሁሉን አዋቂ ተብለዋል (1ዮሐ 2፥20) እነርሱስ መለኮት ናቸውን?” ይሉናል። ሆኖም ግን ይኼ ስሁት ሐቲት(Eisegesis) ነው። ምክንያቱም የ 1ኛዮሐንስ 2፥20 አውድ ስንመለከት የአማኞች “ሁሉን” አዋቂነት ሐሰተኛ መምህራንን ለይተው ከማወቃቸው አንጻር የተነገረ እንጂ ስለ ሁሉም ጉዳዮች የተነገረ አለመሆኑን ከፍ ብለን 1ኛዮሐንስ 2፥19ን ስናነብ እንረዳለን። በአጭሩ በጥቅሱ ውስጥ “ሁሉንም” የሚለው ከአማኞች ተለይተው የወጡ “ሁሉንም” ሐሰተኞች ለማለት እንጂ እንደ መለኮት ያለ ሁሉን አዋቂነትን የሚያሳይ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ግን ኹሉን አዋቂ ጌታህ ነው❗️

@who_is_jesus
@zw2we