Pursuing Holiness

@reformedn


You can find old series by searching
The Pilgrims Progress (30 parts)
Reflection on 1st Peter (13 Parts)
Intro to the book of Job (5 Parts)
ኑዛዜ ፩- ፩፪
መፅሀፈ ምሳሌ (12+)
For daily devotions follow posts by https://t.me/WongeluMinistries

Pursuing Holiness

22 Oct, 05:57


ከማይደረስበት
ከቅድስናው ጥግ በሞቱ አድርሶኝ
ፀድቀሻል አለኝ..
ካለሁበት ሸለቆ
ህያው ቃሉን ልኮ ዳግም ሰው አ'ርጎኝ
አንቺ ብርቱ አለኝ...
እዩልኝ እዩልኝ..ደግነቱን እዩልኝ።
አስቱ 💙

Pursuing Holiness

19 Oct, 18:46


ወሰን የሌለው ትዕግሰት..
“ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑና የዘላለምን ሕይወት ለሚቀበሉ ወሰን የሌለው ትዕግሥቱን ከኀጢአተኞች ዋና በሆንሁት በእኔ እንደ ምሳሌ አድርጎ ያሳይ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ።” 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥16

እግዚአብሔርን ስለ ትዕግስቱ ማን አመስግኖት ይዘልቃል? The fact that He waits for us ወደቀልባችን እስክንመለስ.. ከውድቀታችንም ከስኬታችንም ተምረን ያለ እርሱ ህይወት ትርጉም የለሽ መሆኗ ያለጥርጥር እስኪገባን ድረስ መታገሱ..

ስንቅበዘበዝ፣ አትሂዱ ወደተባልንበት ስንደረደር፣ ጎስቁለን ደግሞ እንደጠፋው ልጅ ተስፋ ቆርጦ ወደተስፋችን ቶሎ እንደመመለስ when we try to make it by ourselves until we recover enough to pretend like we can be fine without him.. ያኔም አይ የልጅ ነገር እያለ ይታገሳል፣ ነፍሳችንን የሚመልሳት (restore) የሚያደርጋት እርሱ ብቻ እንደሆነ እንዲገባን ይታገሳል።

Its hard for me to believe that whenever I ask for forgiveness for the millionth time on the same sin, His attitude isn't "ኤጭ..ደግሞ መጣች። አሁንም?... I taught you this lesson በቅርቡ እኮ.. ከመቼው ተመልሰሽ ገባሽበት.."

የእርሱን ትዕግስት በጥሩ ሁኔታ የሚያንፀባርቅ template የለንም። ቤተሰብ ብንል ጓደኛ ትዕግስት መሳይ ነገር ቢኖረውም ገደብ አበጅቶ ነው። ተሟጦ ያለቀ ዕለት ምንም ማስተባበያ የለውም። "ቆረጠልኝ" ካለ አበቃ። እግዚአብሔር በኛ በልጆቹ ቢቆርጥለት ምን ይውጠን ነበር?

ለእኛ extended የሆነው የእግዚአብሔር ቸርነት እራሱ ጌታ ኢየሱስ ነው። ወሰን የለውም። አይነጥፍም። የእስከዛሬው ነው አይደል የሚገርመን? ገና እስከፍፃሜው የሚሸከመን ራሱ ነው።


"ደግሞም እንዲህ ሲል ይህን ምሳሌ ተናገረ፤ “አንድ ሰው በወይኑ ዕርሻ ቦታ የተተከለች አንዲት የበለስ ተክል ነበረችው፤ እርሱም ፍሬ ሊፈልግባት መጥቶ ምንም አላገኘም። የወይን አትክልት ሠራተኛውንም፣ ‘እነሆ፤ ፍሬ ለማግኘት ልፈልግባት ሦስት ዓመት ወደዚህች በለስ መጥቼ ምንም አላገኘሁም፤ ስለዚህ ቍረጣት፤ ለምን ዐፈሩን በከንቱ ታሟጥጣለች?’ አለው። እርሱ ግን እንዲህ ሲል መለሰለት፤ ‘ጌታ ሆይ፤ ዙሪያዋን እስክኰተኵትላትና ፍግ እስከማደርግላት ድረስ ለዘንድሮ ብቻ ተዋት፤ ለከርሞ ካፈራች መልካም ነው፤ አለበለዚያ ትቈርጣታለህ።’ ሉቃስ 13:6-9

በለሲቱን አትቁረጣት
ለአንድ አመት ታገሳት
🎶 ቤቲ ተዘራ

Pursuing Holiness

18 Oct, 18:12


እንኳን ያንተ ሆንኩኝ አወኩህ እንኳን
እንዳልችል ሆኛለሁ ለሌላ እንዳልሆን
የማምነው እውነት በፍቅር ይዞኛል
ሌላ ሌላ እንዳላይ ውስጤን ሞልተኸዋል
አሰብኩት እራሴን ከአንተ ውጪ
አሰብኩት ወጥቼም ከቤትህ
ባዶ ነኝ ቅብዝብዝ የሌለኝ እረፍት
እኔ አልችልም ሰው አልሆንም በሌለህበት 🎶

Pursuing Holiness

17 Oct, 15:14


ደስታ አማራጭ አይደለም

ይሁን እንጂ ደስተኛ አይደለሁም

‘ደስተኞች ሁኑ’ የሚለውን ትእዛዝ፣ አንዳንዶች ‘ይቻላል’ በሚል ስሜት ሲቀበሉት፣ ሌሎች ግን ችግር ሆኖ ይታያቸዋል። ሁለቱም ምላሾች ግን በምክንያት የተደገፉ ናቸው። እኛ ከፍጥረታችን የሞትን ኀጢያተኞች ነን (ኤፌሶን 2፥1-3)። አብዛኛውን ጊዜም፣ ስሜታችን የሚዋዥቅና ለመንፈሳዊ ነገር የደነዘዝን ነን። በክርስቶስ ውስጥ ሆነን እንኳ እያለ፣ ዥዋዥዌ ላይ እንዳለ ሰው፣ በየዕለቱ፣ ከደደነዘዘ ልብ ወደ ተነቃቃ መንፈስ፣ ከዚያም መልሰን ወደ ድርቀት በመሄድ እንዋዥቃለን።

ራሳችንን የምናውቅና እውነታን ተቀብሎ መኖርን እየተማርን ያለን ሰዎች ከሆንን፣ ከልብ ደስተኞች የምንሆንባቸው ጊዜያት ምን ያህል ጥቂት እንደሆኑ በማመን፣ አባታችንን ደግመን ደጋግመን፣ «የማዳንህን ደስታ መልስልኝ» እያልን እንማጸናለን (መዝሙር 51፥12)።

እንደነዚህ ላሉ ሰነፍና ራሳቸውን ለሚያውቁ ሰዎች፣ ደስታ አማራጭ እንዳልሆነ መስማት፣ ‘ይቻላል’ ከሚል ስሜት ይልቅ ኩነኔን ይፈጥርባቸዋል። በብዙ ሸክም ተዳክሞ ባለ ትከሻ ላይ ሌላ ተጨማሪ ቀንበርን እንደመጫን ነው።

ነገር ግን፣ ደስታን ያጡ ሰዎች መሆናችን የታሪኩ መደምደሚያ አይደለም። በስሌቱ ውስጥ አንድ ከመጠን በላይ ዋጋ ያለው ነገር ይቀራል።

ተጨማሪ ለማንበብ...

Telegram | YouTube | Facebook | Instagram | TikTok | Website

#Articles

Pursuing Holiness

15 Oct, 04:41


Psalms 136 (Sermon Notes)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
The focus of this psalm isn't hard to find. Its repeatedly emphasized with the phrase "His love endures forever." The word translated as love is the hebrew word chêçêd. Its an incredibly hard word to translate due to its wide range of possible meanings. The main ones can be summarized with these ways.
1, Steadfast Love: ፅኑ፣ የማይወድቅ ፍቅር
2, Indescribable tenderness: motherly softness and gentleness
3, Heart melting faithfulness and loyalty : ተስፋ የማይቆርጥ፣ አስተማማኝ ታማኝነት
4, Astonishing magnanimity: generosity and mercy that the victorious side of war shows to the defeated. (ከሚጠብቃቸው አደጋ ፍፁም ተቃራኒ የሆነ ምህረት)

This is the love this psalm tells us to count on. It presents it as an indispensable part of the picture of God we see revealed in scripture. Being believers on the other side of the cross, we have more evidence of His love and mercy. This chêçêd wasn't substituted by grace in the New Testament. Jesus is the chêçêd of God. Jesus is the love of God made visible and concrete for us. If we miss this when we see God we have a distorted view of God.

Who is this God (Verse 1-4)

¹ Give thanks to the Lord, for he is good. His love endures forever.
² Give thanks to the God of gods. His love endures forever.
³ Give thanks to the Lord of lords: His love endures forever.
⁴ to him who alone does great wonders, His love endures forever.

The Lord is Good and The Lord is Great. He is the first of all beings. He alone does miracles and wonders. Though we see more details to describe His greatness its significant that His goodness was mentioned first. Its much better to be good than great! How tragic would it be if a great God was anything but good?

How did He show His love?
1, Creation (verse 5-9)
Continuing and unchanging existence of sun, starts, moon and the land we stand on are proof of enduring steadfast love. “Every good and perfect gift is from above, coming down from the Father of the heavenly lights, who does not change like shifting shadows.”Jam 1:17

2, Redemption ( verse 10-24)
The bible tells a story with a pattern of Gods redemption of His people. We can see the story of our salvation in these stories. This section shows us a journey with a fantastic rescue in a challenging pilgrimage despite the opposition of hell.
²³ to the One who remembered us in our low estate His love endures forever.
²⁴ and freed us from our enemies, His love endures forever.
Believers can and should sincerely say this about their own salvation!

3, Providence (verse 25)
“and who gives food to every creature. His love endures forever.”
His providence is His upholding, sustaining and directing of all things for His glory. The one who feeds every creation will surely not deprive His own people.

“Give thanks to the God of heaven. His love endures forever.”Ps 136:26
The phrase "God of heaven" is only mentioned here is the Psalms. Its meant to emphasize on the transcendence of God. The Good and Great God is not of this earth. He is not of our world. Heaven isn't the clouds we see above us. Its a realm where He alone reigns in. Its unseen, immaterial and eternal reality. የመጠቀ እና ከእኛ የተለየ ነው። And yet, He is not too far for us to start doubting the reliability of His love. We can trust that it will not have an expiration date. We know His love endures forever for He is an eternal God.

Pursuing Holiness

14 Oct, 04:06


ቆጠርከኝ እንደባለማዕረግ
ሳልለፋ ምንም ሳላደርግ
ምህረትህ በዝቶልኝ በላዬ
ኸረ ደግ እኮ ነህ ጌታዬ!
ልናገር እኔስ ቸርነትህን
አላውቅም ክፉ መሆንህን..

እኔማ ይገርመኛል ሁልጊዜ ይደንቀኛል
እኔማ ይገርመኛል ሳስበው ይደንቀኛል

ሹመት ሆኖልኝ ነው ከአብ የተወሰነ
ማንም የማይቀያይረው ከላይ የሆነ
ልጄ ነህ ብሎኛል ምን ልበል ይህ ማዕረጌ ነው
ውስጤን መደነቅ ሞልቶታል ለእኔ በሆነው

በህልሜ በእውኔም አስቤ የማላውቀውን
ብዙ አድርገህልኛል ያልጠበኩትን
ልዘምር በገናዬን ላንሳ ቅኔን ልደርድር
ግሩምና ድንቅ የሆነውን ስራህን ልናገር

አይቆጠር እንዲሁ አይባል ቸርነትህ
የማይለወጠው ፍቅር የአባትነትህ
ኧረ እንዴት ብዬ እገልጸዋለው ያረክልኝን
ከቁጥር በላይ የበዛው የዋልክልኝን

Pursuing Holiness

12 Oct, 08:12


በርጠሚዮስ ነኝ አይነ ስውር ሚስኪን
ከሩቅ የሰማሁኝ የጌታዬን ድምፁን
ከብዙ ሁካታ ጉርምርምታ መሀል
የክርስቶስ ድምፁ ከሩቅ ይሰማኛል..

የከበበውን ሰው ገለል በሉ እያለ
በደሌን በደሙ ዋጋ እየከፈለ
ስለኔ የሞተው ኢየሱስ ይመጣል
የልቦናዬን አይን ገልጦ ያሳየኛል..

አብዝቼ እጮሃለው ጌታ ማረኝ ብዬ
በግልፅ እየታየኝ ሲምረኝ ጌታዬ
በውስጤ  በደልስ ህይወቴ ዝላለች
ባምላኬ ቸርነት ህይወት ካላገኘች!
ይልማ 🎶


ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ከብዙ ሕዝብ ጋር ከኢያሪኮ ሲወጡ ዐይነ ስውሩ የጤሜዎስ ልጅ በርጤሜዎስ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር።

እርሱም የናዝሬቱ ኢየሱስ መሆኑን በሰማ ጊዜ፣ “የዳዊት ልጅ፣ ኢየሱስ ሆይ፤ ማረኝ!” እያለ ይጮኽ ጀመር።

ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤

እርሱ ግን፣ “የዳዊት ልጅ ሆይ፤ ማረኝ!” እያለ የባሰ ጮኸ።

ኢየሱስም ቆም ብሎ፣ “ጥሩት” አላቸው።

እነርሱም ዐይነ ስውሩን፣ “አይዞህ፤ ተነሥ፤ ይጠራሃል!” አሉት። እርሱም ልብሱን ጥሎ ብድግ በማለት፣ ተነሥቶ ወደ ኢየሱስ መጣ።

ኢየሱስም፣ “ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?” አለው።

ዐይነ ስውሩም፣ “መምህር ሆይ፤ እንዳይ እፈልጋለሁ” አለው።

ኢየሱስም፣ “ሂድ፣ እምነትህ አድኖሃል” አለው።

ወዲያውም ዐይኑ በራለት፤ በመንገድም ኢየሱስን ተከትሎት ሄደ።
ማርቆስ 10:46

Pursuing Holiness

10 Oct, 13:56


መከራዬ በአብዛኛው አንተን ከመርሳቴ ይመነጫል። ጥበብህን እየረሳሁ እጨነቃለሁ። ፀጋህን እየረሳሁ እለግማለሁ። ምህረትህን እየረሳሁ ቂም ይዛለሁ። እባክህን ማንነትህ ዘወትር አስታውሰኝ!

Pursuing Holiness

07 Oct, 23:11


እስራኤል እንዲህ ይበል፦ “ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ። በርግጥ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤ ዳሩ ግን ድል አላደረጉኝም። ዐራሾች ጀርባዬን ዐረሱት፤ ትልማቸውንም አስረዘሙት።
እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ነው፤ የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለው።
ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣ ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ፣ በጣራ ላይ እንደ በቀለ ሣር ይሁኑ፤ ደግሞም ለዐጫጅ እጁን፣ ለነዶ ሰብሳቢ ዕቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ። መንገድ ዐላፊዎችም፣ “የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤ በእግዚአብሔር ስም እንባርካችኋለን” አይበሉ። (መዝ 129)

ይህ ክፍል ፀረ እግዚአብሔር የሆኑ አሳዳጆች በእግዚአብሔር ህዝብ ላይ ስላስነሱት መከራ ፣ ስለመከራው ፅኑነትና መራርነት፣ በስደቱ ውስጥ ስለነበረው የእግዚአብሔር ታማኝነትና ታዳጊነት እንዲሁም ስሉአሳዳጆች የመጨረሻ እጣፈንታ ያትታል።

የምንኖርበት አለም የእግዚአብሔርን ነገር የሚቃወቀም እንደመሆኑ ደግሞ በፅድቅ ከእግዚአብሔር ጋር የማንወግን ከሆነ የሚኖረን ሌላ አማራጭ ወደድንም ጠላንም ከእርሱ ጋር ተፃራሪ በሆነ system ውስጥ መሰንበት ነው። Unfortunately there is no middle ground. There is no neutrality.

ይሄ ነው እንግዲህ የሰውን ልጅ ህይወት ሰልፍ የሚያበረታው፡፡ የክርስቲያን የመናኝ ጉዞ አሸነፍን ሲሉ ብዙ ጊዜ የሚወድቁበት ፤ አንድ ተራራ ወጣው ሲሉ ያልታየ ሸለቆ ውስጥ የሚወረወሩበት ብዙ ጥጋጥግ አለው፡፡ እረፍትና መረጋጋት በጦርነት ኬላ ስለማይገኝ መባዘን የደከመው ሁሉ ዝለቱን ተሸክሞ ይጋደምና በአዕምሮው ደግሞ እዚ እዛ እያለ ወደሌላ አይነት እንግልት ይሸጋገራል።

የሠራዊት ጌታ የሆንከው እግዚአብሄር፤ አንተ ጣቶችን ለሰይፍ ማስታጠቅ ብቻ ሳይሆን ዘለቄታዊ የሆነ እፎይታ መስጠትን ታውቅበታለህ። ይህን የሚያውቅ ልቤ ነው እንግዲህ አንተን ጌታዬን ትቶ ሊያጠፉኝ የሚመኙ የአንተ ጠላቶች (ገና ከአንተ መንግስት ጋር በአግባቡ መራመድ ሳልጀምር በልጅነቴ ከሚያስጨንቁኝ) ጋር ይላመዳል፣ አንፃራዊ ሰላም ይመሰርታል።

ያም ሆኖ ግን መከራው አልቀረልኝም። ቃልህ እንደሚል መከራ ቃል ከተገቡልን ነገሮች መሀል ነው። መነጫነጭ ለምዶብኝ እንደ self fulfilling prophecy ራሴ ላይ ማመጣው ነገር ቢሆን እንደአንዳንዶች እኔም ችግሬን መካድ እስኪያምረኝ ድረስ ነው የደከመኝ.. አቤቱ ሸክም የደከማቸውን ድኩማን ልታሳርፍ የምትጠራው፣ መንፈሳቸው ለተሰበረ ቅርብ የሆንከው ጌታ ሆይ ፈጥነህ ድረስልኝ፡፡ የማዳንህን ደስታ መልስልኝ እንዳለ ባርያህ ባንተ ረክቼ ደስታህ ሀይል ሆኖኝ ውጊያውን በታደሰ ሀይል ልቀጥል..

ቃልህ እንደሚል አንተን ሊመስል የሚወድ ሁሉ ይሰደዳል፡፡ ታድያ የኔ ስደት እንደአባቶቼ ስለመንግስትህ፣ ስለተሸከምኩት ስምህ ከጠላቶችህ የሚመጣ ሆኖ በመከራዬ ምመካው መቼ ነው? እንዲሁ ከራሴ ጋር ስታገል- ስሸነፍ ለመቀደስ ስፍጨረጨር- ስሰንፍ .. ስጋዊ ምኞቴን መግደል ተስኖኝ ስጋዬ እኔን እያሳደደኝ እኔም እየተሸነፍኩለት እንድኖር ለምን ፈቀድክ? አንድ ወንድሜ እንዳለ ከውጪ ስለስምህ መከራን መቀበል ቅንጦት ሆኖብኝ ይቅር?

በእርግጥ መከራዬ ከምንም በላይ አቅሜን አሳይቶኛል፡፡ እስትፋሱ አፍንጫው ላይ ያለን ሰው አትደገፍ ከቶ ምን የሚበጅ ነገር አለው የሚለው ጥቅስ እኮ ስለ ሌላ ምስኪን ስጋ ለባሾች እንጂ ስለኔ አይመስለኝም ነበር.. ትዕቢት ክፉ ነው። ስብዕናንም ያስረሳል፡፡ ህይወቴ ላይ ምንም ስልጣን እንደሌለኝ  ከመከራ በላይ ማን አስረዳኝ?

When things relatively went well I had the illusion that I was in control..ቃልህ እንደሚል ትንፋሽና መንገዴን የያዘው ማን እንደሆነ የተረዳሁትን ግን  በሰላሙ ጊዜ እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ እንድመስልህ ያለኝ ፍላጎት ከመከራ የማረፍ ጉጉቴ እንዲበልጥ ልቤን አበርታልኝ፡፡ ልፍስፍስ ምሳሌዎች የሉኝምና አጀግነኝ፡፡

ምስጋናዬን አዘርፌ ድባቴ እንዳይወርሰኝ በምህረትህ በጎነት አገልግለኝ፡፡ አባቴ ነህና የፍቅርህን ልክ ለአፍታም ጥያቄ ውስጥ መክተት አልፈልግም፡፡ ይልቁንስ እንደቀድሞ በአንተ እንድረካ ድምፅህን ወደምሰማበት እግርህ ስር አሳርፈኝ፡፡ የሚያፀናውን ፀጋ ተቀብዬ እንድነሳ እግሮቼን ለመንበርከክ አስቸኩል፡፡

አልታዘዝ ባዩን ልብ መስበር እንደምትችል ምስክር ነኝና ሳስቸግር ገስፀኝ ፤ እንዳላሳዝንህም ጠብቀኝ፡፡ ከአንተ ሌላ ሀብት የሌለኝ ፤ ለዘለዓለሜ የታመንኩህ የምጠብቅህም አለኝታዬ አንተ ብቻ ነህ፡፡ ምድር ልትቸር የምትችላቸውን በረከት ሁሉ ማግኘት ለአንድ ቀን የአንተ ባርያ ከመሆን አይወዳደርም፡፡

አንተ ፍፁም ፃዲቅ ፣ ፍፁም ፍቅር ፣ ፍፁም ታማኝ ፣ ፍፁም በጎ እጅግ ታላቅና ቅዱስ ነህ፡፡ አንተን ማወቅ ራሱ መታደል ነው፡፡ ስምህን መጥራት በረከት ነው፡፡ እንዲቀልብኝና እንድለምደው አልፈልግም፡፡

የከበርከው አምላኬ ሆይ በእኔ ሁኔታ የማይገመት ጥበብ እንዳለህ አውቃለው፡፡
“ብንነቃም ሆነ ብናንቀላፋ ከእርሱ ጋር በሕይወት እንድንኖር" የሞትክልን ኢየሱስ የአንተ እጅ ስለያዘው ህይወቴ አብዝቼ መጨነቄ ከንቱነቱ ገብቶኛል፡፡ እምነቴን አበርታውና ከዚህ በላይ ጥገኛህ ሆኜ ልደገፍህ፡፡ እረፍቴ ፣ ብርታቴ ሰላሜም ቃልኪዳንህን የምትጠብቀው ቸሩ እረኛዬ የነፍሴ ንጉስ ክርስቶስ ነህ፡፡

ከአንተ ጋር ወግኖ መሰደድ ክብር ነው። የአንተ ሰልፍ ውስጥ ገብቶ መቁሰል ትምክህት ነው። ጌታ ሆይ ከሁሉ አስበልጬ መንግስትህን እንድሻና ከዚህ በረከት እንዳልጎድል ጣቶቼን ለሰልፍ አሰልጥን።

Pursuing Holiness

06 Oct, 05:05


https://m.youtube.com/playlist?list=PLKNx68410nPXKxLqRbQ5FWHte-cOCN1Lg

Pursuing Holiness

04 Oct, 20:34


There is this cool insight I got from Dane Ortlund.

በተደጋጋሚ ስለእግዚአብሔርና ስለእስራኤል መስተጋብር ስናነብ በአመፃችሁ ምክኒያት "ቁጣዬን አነሳሳችሁት" ወይንም "ቀሰቀሳችሁት in other words provoke አደረጋችሁት ይላቸውና በተቃራኒው ደግሞ በሚያሳዩት ማንኛውም አይነት የልብ ስብራትና ራስን ማዋረድ ምህረት ለማድረግ ሲቸኩል፣ ቸርነትን ሊያደርግ ወደእነርሱ ቶሎ ሲመለስ እናያለን። ለልጆቹ የሚቀናው መልካምነት ነው። Its easy for Him to be gracious. ቁጣውን በእምቢተኝነታቸው ካልቀሰቀሱት በቀር...

በተቃራኒው እኛ ሰዎች ደግሞ አመፅ ይቀናናል። ሁላችን ለራስወዳድነት የተጋለጥን ነን። የምንቸኩለው ለጥፋት ነው። ቶሎ የምንመለሰው ወዳልገደልነው አለማዊነታችን ነው። This is why it says in hebrews that Hebrews 10:24 "Let us consider one another to provoke unto love and to good works: Not forsaking the assembling of ourselves together, as the manner of some is; but exhorting one another: and so much the more, as ye see the day approaching."

ከቅዱሳን ጋር ባለን ህብረትና በሌሎቹ የፀጋ መሳርያዎች (በቃሉ፣ በፀሎት፣ በጌታ እራት.." ካልተነቃቃን (provoke ካልተደረግን) በስተቀር ከፍቅርና ከመልካም ስራ እጅግ የራቅን ነን። This is why godly friendships are very very crucial. I hope and pray we don't take it for granted.

ምክኒያቱም እንደክርስቲያን አለም አልተገባችንም። ከሷ መወዳጀት ከእውነተኛው ወዳጃችን ጋር ጠላትነት ነው። በደፈናው አማኝ ነን ከሚሉትም መሀከል የኛ ቢጤ ናፍቆት፣ የኛ ቢጤ ጉጉትና መሻት ያላቸውን እንድንፈልግ የሚመራን ደመነፍስ አለ። ሰውን ገንዘብ የምናደርገው የሆነ መስፈርት አውጥተንለት ያንን ስላሟላ ሳይሆን የጋራ አባት፣ የጋራ ታላቅ ወንድምና የጋራ አፅናኝ ስላለን ነው። አብ የመረጣቸው፣ ወልድ የተቤዣቸው፣ መንፈስ ዳግም የወለዳቸው ሁሉ (ወደድንም ጠላን) የኛ ወገን ናቸው። If you have to be tribal, belong and be thrilled that you get to be in that tribe.

እነዚህ ወንድሞቻችን ደግሞ ወደምንወደው ጌታ የሚገፉን፣ ጣርያ ገንጥለው ኢየሱስ ጋር የሚያደርሱን ብቻ ሳይሆኑ አንዳንዴ የሚያቆስሉን አካሎቻችን ናቸው። ምን ያህል ቢያበሽቁን ቆርጠን አንጥላቸውም። ምንም ቢሆን እነርሱ ከበደሉን በላይ እኛ ንፁሁን እግዚአብሔር በድለነዋል። ምንም ቢሆን በአንድ ወቅት በእነርሱ በኩል የምንወደውን ጌታ ድምፅ ሰምተነዋል። ስለዚህ ስለተጠሩበት "ክርስቲያን" የሚል የቤተሰብ ስም፣ ስለምንጋራው እግዚአብሔርን የመምሰል መሻት ስንል ራሳችንን የሁሉ አገልጋይ፣ ይቅር ባይ፣ ሆደ ሰፊ በማድረግ lets treasure our brethren. ምክኒያቱም ያለእነርሱ provocation መልካም የምንሰራ የፍቅር ሰዎች አንሆንም። ፍቅር by definition object ይፈልጋል። ለብቻችን የምንማረው ትምህርት አይደለም። Genuine የሆነ መልካም ስራ ለመስራት የግድ ትክክለኛ የሆነ ጉድለትን የሚያስተውሉ ሩህሩህ አይኖች ያስፈልጉናል። ይህም ለብቻ ምሽግ በመግባት አይመጣም። ለነዚህ ሁሉ በረከት ምንጭ ስለሆኑ ወንድምና እህቶቻችን እግዚአብሔር ይመስገን ለማለት ነው 😊

Pursuing Holiness

02 Oct, 19:52


we have a God who has chosen to be known as the God of Abraham, Isaac, and Jacob. oh how each of these three figures embodies distinct characteristics that reflect different aspects of faith and human experience! Abraham stands out as an exceptional figure of unwavering faith, a true giant in faith. Isaac, on the other hand, exemplifies obedience and innocence…… he accepted his father's will without question when he was bound for sacrifice ( he is old enough to say no or cry out for help but he didnt), he lived harmoniously with those around him, avoiding conflict, and receiving a wife as a divine gift. In contrast, Jacob's life was marked by disobedience and cunning; he often relied on his flawed intellect to navigate challenges. And yet, despite his flaws, he was embraced and redeemed by the Lord. This is a powerful reminder that God is not only the God of the relatively faithful Abraham and the obedient Isaac but also of Jacob, who represents the flawed and the redeemed like me. I love God!

Pursuing Holiness

02 Oct, 12:35


ኢየሱስ : ስንደክም ተስፋችን
(Repost)

የተቀጠቀጠ ሸምበቆ አይሰብርም፤ የሚጤስም የጧፍ ክር አያጠፋም፤ ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።” ኢሳይያስ 42፥3

ለራሴ ከተውከኝማ እንደሸንበቆ እንኳ ረዘም ብዬ አልታይም። እንደተቀጠቀጠ ሸንበቆ እንኳን ሰው ላስደግፍ ለራሴም የማላስተማምን ድኩም ነኝና እንደሰው ስልቹ ብትሆን ሰብረህ ትጥለኝ ነበር ፤ አልጠቅምህምና።

ጧፍ ነዶ ነዶ እያለቀ ሲመጣ ይጤሳል። የዛኔ የሰሙ ክርፋት መከራ ነው ፤በዛ ላይ ብርሀንም አይኖረውም። ጌታዬ እንደሰው  ብትሆን ጭላንጭሉን ብርሀን ታጠፋው ነበር።

የቃልህ መዶሻ ሲያደቀኝ የሀጥያቴን ሀያልነት ተመልክቼ ስለኔ የተሰቀለው ኢየሱስ ወንጌል ሲበራልኝ ድህነት በጭራሽ እንደማይገባኝ ተረድቼ ነበር። የተዘፈቅሁበትን ሀጥያት እያወቅሁት በየትኛው ፅድቄ እመካለሁ? በአመፅ የምቅበዘበዘዋን ፈልገህ ባዳንከኝ ሰሞን ላስደስትህ ታትር ነበር።

የሚያሳዝንህን ሀጥያት ተጸይፌ ላሸንፍ እታገል ነበር። ክቡር ቃልህን ማንበብ በፀሎት የልብ መሻትህን መፈለግ ስላንተ ማውራት አንተን ማዋራት ቀንበር አይመስለኝም ነበር ። ዛሬ የጉልበቴ መታሰርና የልቤ ዝለት ያኔ ከተፀየፍኩት ሀጥያት ጋር በድርድር የመወዳጀቴ ውጤት መሆኑንም አውቃለሁ።

ታድያ እኔ ራሴ ባለችኝ ትንሽዬ እውቀት መሳቴን ተረድቼ ድካሜን ከጠላሁ ነውርና እንከን ፈፅሞ የሌለብህ ቅዱሱ እግዚያብሄር ደግሞ ይብሱኑ እንዴት ሀጥያቴን ትጠላው ይሆን? ደክሜ ከስጋ ጋር እንደወትሮ መታገል ሲያቅተኝም የኔ ደግ መሲህ አትሰብረኝም ፤ አታጠፋኝም!

ከሀይማኖተኞቹ ፈሪሳውያን ይልቅ በሀጥያቱ ለሚሸማቀቀው ትራራለህ። የኔ መልካም! የኔ ብርቱ! ደካማውን ጥለህ ሀይልህን ከመግለጥ ይልቅ አፅንተኸኝ የምህረት ማሳያ ታደርገኛለህ። ሰላሜ ተናግቶ እምነቴ ሲላላ ከምንም በላይ የምወደው ቃልህን ለማንበብ ከእስትንፋሴ ይልቅ የምትቀርበኝን አባቴን ለማዋራት ተስኖኝ እንዲሁ ስምህን ስጠራ ታዝንልኛለህ።

በሀጥያት ደክሜ ፤ ንስሀ መግባት ሲያታክተኝ ማድረግ የምፈልገውን ፅድቅ ማድረግያ አቅም ያጣሁ ቀን አያጠፋኝም። የፀጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ እስከፍፃሜው ያፀናኛል። ሀያሉ ድካሜን ያግዛል።

አዲስ ፍጥረት መሆኔን እስክጠራጠር እንኳን ብደክም.. በበረቱ ሰዎች ምን ያህል ብቀና..በርትቼ እሮጥ የነበረበትን ጊዜ እያሰብኩ አሁን መንፏቀቅ እንኳን እንደተሳነኝ አይቼ ባነባ ድካሜን አይቶ የሚራራልኝ ደግ ካህን አለኝ።

ምህረቱ የበዛ! የሀጥያተኛውን ጥፋት የማይወድድ አባት አለኝ። ዘይቱን ሲጨምርልኝ ዳግም ብርሀኔ ይታደሳል። የደከሙትን ልጆቹን በፀጋው ደግፎ ያቆማል እንጂ እንደሰው ሸንበቆ አይሰብርም። እንደሰው ከብርቱዎቹ ጋር ወግኖ በሀጥያቴ ዝዬ ሳዝን አያጠፋኝም። ጠወልጋለች ብሎ አይሰብረኝም በፀጋው ባለጠግነት ያፀናኛል እንጂ!

ሸክሜ ሲከብድብኝ ወደኔ ነይ ይለኛል። አባት ነውና ሳይጠየፍ ቁስል ማከም እረፍትን መስጠት ያውቅበታል! ባርያህ ልሆን እንኳ አይገባኝም ብዬ እግሩ ስር ስደፋ ሙት የነበረች ልጄ መጣች ብሎ ቀለበቱን አድርጎልኝ ድግስ ያዘጋጃል።

Pursuing Holiness

30 Sep, 16:57


ፈልጌህ መጥቻለው ፈልጌህ
ላገኝህ መጥቻለሁ ኢየሱስ ላገኝህ
ናፍቀኸኝ መጥቻለሁ ልሰማህ ልሰማህ
ፈልጌህ መጥቻለው ኢየሱስ ላደምጥህ

አንተ ብቻህን እንድትደመጥ
የስጋዬ ጩኸቱ ረጭ ይበል ፀጥ
ተናገር ተናገረኝ አባ ድምፅህን አሰማኝ
በእጆችህም ዳሰኝ ልጄ አለው ይኸው በለኝ

የልብህን ሀሳብ እስቲ አጫውተኛ
ሁንልኝ የህይወቴ መካከለኛ
ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች
በኔም ላይ እንድትሆን ለሀሳብህ ልመች ለአንተ ልመች

ብቸኛ አቅሜ 'ምታደርገኝ ቀና
በአንተ ካልሆነ ከቶ አልድንምና
ምትለኝን ሁሉ ላደምጥ ፈልጌ
በፊትህ ሆናለው ራሴን ባዶ አድርጌ

Pursuing Holiness

30 Sep, 14:14


The amount of times I've heard this song... its one of those songs that I might hear after 10 years and remember exactly the season of life I was in when I first heard it.

Pursuing Holiness

28 Sep, 08:48


.

Pursuing Holiness

26 Sep, 04:12


ካልቪን ለዚህ የሚሆን ጥሩ መለኪያ አለው። (Worship የሚለው ትልቅ ሀሳብ በውስጡ Adoration, Trust, Invocation and Thanks giving አሉት።)
1, የምንደመመው፣ ትልቁን ውዳሴ የምንሰጠው ለማን ነው?
2, የምንታመንበት፣ በሞት ሸለቆ ስንሆን እንደማይተወን እርግጠኛ የምንሆንበት ማን ነው?
3, ችግር ውስጥ ስንሆን የምንጣራው ማንን ነው?መልስ መፍትሄ ወይ ምሪት ስንሻ ወዴት እንሄዳለን?
4,ነገሮች እንዳሰብነው፣ ካሰብነውም በላይ መልካም ሲሆኑ የምናመሰግነውና credit የምንሰጠው ለማን ነው?

Pursuing Holiness

26 Sep, 04:12


ትዕዛዝ 1

“ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ።” ዘጸ 20፥3

ዋናው ነገር የእምነታቸው ጥንካሬ ወይ ትልቅነት ሳይሆን የምናምንበት አካል ነው። በተለይም ደግሞ ሀበሻ በግርድፉ ሀይማኖተኛ ስለሆነ ምናልባትም ስሜታዊ ሆኖ የሚያወራለት እምነት ይኖረዋል። ይበቃኛል በሚለው አቅም የሚተጋበት sincere አምልኮ አለው። የእግዚአብሔር demand ደግሞ ከሌሎቹ ጣዖታት በተለየ መልኩ ለብቻው መመለክን demand ያደርጋል። Only He has divine rights over all. ይህ ለእኛ 3 ዋና ዋና implications አሉት

1, እግዚአብሔርን ብቻ ማምለክ አለብን

ከእግዚአብሔር በቀር አምልኮ የተገባው የለም። Henotheism ወይንም ደግሞ ካሉት አማራጮች መሀከል እግዚአብሔርን መምረጥ አይደለም የሚበቅብን። Monotheism begins by acknowledging that all the other "gods" have no ontological existence.

ከእስራኤል የጀመረ syncretism የሚባል ቅዱሱን የእግዚአብሔር ሀይማኖት ከሀሰተኛ ጣዖታት ጋር የመቀየጥ ልምድ አለ። (ኢያሱ 24:14, 1 ነገስት 18:21, ማቲ 6:24) ይሄ ዛሬ ላይም የቀጠለ ልምምድ ነው። ብዙዎቻችን እግዚአብሔር በህይወታችን ውስጥ በመኖሩ ደስተኞች ነን። የህይወታችንን የሆነ ክፍል በመስጠታችን አይደብረንም። የምንሰጥበትን መጠን የምንወስነው እኛው ነን። ደፍረን አንለውም እንጂ managable የሆነ በሰጠነው ክፍል ብቻ የሚመለክ አምላክ ነው የምንፈልገው።

Calvin commented on "You shall have no other gods before me" as God forbidding us from showcasing our idols  before his face just as a husband would never want to see his wife bringing the guy she is cheating with.

ከካልቪን ጋር በዚህ አተረጓጎም ባንግባባ እንኳ ለአምልኮ ትዳር ጥሩ analogy ነው። ማንም ሚስቱን እወድሻለው ካለ በኋላ ሌላ የምወዳትን ልጅ ስላገኘው ከእርሷም ጋር የተወሰነ ጊዜ አሳልፋለው። ግን  አንቺም ለኔ ቦታ አለሽ። ሁለታቹም ለኔ ዋጋ አላቹ ቢል ምላሿን መገመት አይከብድም።

If she's gracious she will rightfully give him an ultimatum to leave her or the new woman he is interested in. Who would condemn her for being cruel, emotional, jealous, intolerant or unfair? ትዳር የሚጠይቀውን መሰጠት የሚረዳ ሰው ታድያ አምልኮን ከዚያ አብልጦ መገንዘብ አለበት። እግዚአብሔርን እንወዳለን ካለን በእርሱ ልክ የምንወደው ነገር መኖር የለበትም። ስለፍቅር ስናወራ ደግሞ ከስሜታዊነቱ በስቲያ ያለውንም ውሳኔና ድርጊት ዳራ መገንዘብ አለብን።( ዘዳግም 6:4-5)

2, ጣዖታትን አስወግዱ
የምንወደው የheidelberg ካታኪዝም ጣዖትን ሲያብራራ  "having or inventing something in which one trusts in place of alongside of the only true God who has revealed himself in his word." በማለት ነው። በቃሉ ውስጥ ከምናውቀው ያህዌ ውጪ ያሉ መታመኛዎቻችን ሁሉ ጣዖታት ናቸው። እዚህ ላይ ከሰው ባህሪ የማይገባኝ ነገር ነበር። አንድ rational የሆነ ሰው እንዴት በራሱ እጅ የሰራውን ቁስ ወይ ደግሞ ሰው ሰራሽ እንደሆነ በሚረዳው ነገር ለመታመን ይፈተናል? Doug Stuart በዚህ ጉዳይ ላይ ጣዖታት offer የሚያደርጉትን መሳቢያቸውን ያብራራል።

1, ዋስትና ይሰጣሉ: የተቀመጠውን ቀመር ተከትለን ከታዘዝን እና መስዋዕቱን በትክክል ካቀረብን ይሰራልናል የሚል እርግጠኛነት

2, ራስ ወዳድ motivation: አማልክቱ መስዋዕት ካልበሉ ይጠፋሉ። ስለዚህ ሰውን የሚተባበሩት ለራሳቸው በማሰብ መሆኑ አምልኮውን mutually beneficial ውል ያደርገዋል። 

3, ቀላል ነው : ምንም አይነት moral code ወዮ ቅድስና አይጠይቅም። መስዋዕቱን እና የተቀመጠውን ritual የተገበረ ሁሉ ተቀባይነት አለው።

4 Convenient ነው: ከእዮርባም ጀምሮ የተዘረጋው system ጣዖታትን ማምለክ የተመቸና ድካም አልባ እንዲሆን አስችሏል። God restricted sacrifice to the tabernacle and later in the temple. አሁን ደግሞ አምልኳችን በእውነትና በመንፈስ መሆን አለበት የሚል መለኪያ አለው። አብዛኞቹ የአምልኮ ቀን መርሀግብሮች በቃሉ define ተደርገዋል።

5, Culturally normal ነበር: በዙርያቸው የነበሩ ሀገራት ሁሉ በስም ለየት ላሉ ጣዖታት ተመሳሳይ አምልኮን ያቀርቡ ነበር። ስለዚህ ከጎረቤቶቻቸው ጋር fit እንዲያደርጉና እንዲቀላቀሉ፣ እንዲጋቡ በር ይከፍታል። በዛን ጊዜ monotheist መሆን ከባድ ነበር። 

6, logical ይመስላል: ለተፈጥሯዊው አዕምሮ አንድ አሞላክ አንድን ነገር ብቻ ይቆጣጠራል የሚለው ሀሳብ ትርጉም ይሰጣል።

7, ስጋን ደስ ያሰኛል: የሚታዩ ብዙ ቆንጆ እና አጓጊ ነገሮች ነበሩት።

8, indulgent ያደርጋል : በዘወትር ህይወቱ እያረደ የማይበላውን ሰው የመስዋዕቱን ድግስ እንዲበላ እድል ይሰጣል። ምርጥ ምርጡን ምግብና ወይን እንዲለምዱ ያደርጋል።

9, erotic ነበር: አማልክቱ ሀሰተኛ በመሆናቸውና በዘመናችንም ስለተለያዩ cults እንደምናውቀው ሁሉም አይነት ወሲባዊ ሀጥያትን ከመጠን በላይ promote የሚያደርግ ነው። 

ትልቁ ጣዖት አምልኮተ ራስ ይመስለኛል። ከላይ ያለውን ዘጠኙንም motivation ያሟላል። በዛ ላይ ደግሞ እኛው ለእኛው እንዲመች አድርገን የፈጠርነው ጣዖት ነው። በራስ መተማመንና በራስ መታመን መሀል ያለው ቀጭን መስመር ብዙዎችን ወደዚህ አምልኮ ከቷል። ለስጋው የሚያዝናናን የሚያስደስትን ነገር፣ የማያጉላላና ብዙ ዋጋ (ራስን መካድን) የማይጠይቅ፣ አፋጣኝና predictable የሆነ practical እርዳታ ሌላ ከየትም አናገኝም።

3, እግዚአብሄርን በክርስቶስ በኩል ማምለክ

አስርቱ ትዕዛዛት የተሻሩ የሚመስላቸው ብዙ ሰዎች አሉ። ትዕዛዞቹ ግን kevin በሙዚቃዊ መንገድ እንደሚያብራራው አልተሻሩም። But they have transposed። ማለትም አሁንም እንጠብቃቸዋለን ግን የምንታዘዛቸው ለየት ባለ መንገድ ነው።( In a different key.)እኔን ብቻ አምልኩኝ ያለው እግዚአብሔር አዲስ ኪዳን ላይ ኢየሱስን እንድንሰማ ነግሮናል። ማቲ 17:5 ክርስቶስ አምልኳችን እንደሚገባው የተለያዩ ክፍሎች ይነግሩናል።
“እርሱ የእግዚአብሔር ክብር ነጸብራ ቅና የባሕርዩ ትክክለኛ ምሳሌ ሆኖ፣ በኀያል ቃሉ ሁሉን ደግፎ ይዞአል፤ የኀጢአት መንጻት ካስገኘ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ።”ዕብ 1:3
“ይኸውም በሰማይና በምድር፣ ከምድርም በታች፣ ጒልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይንበረከክ ዘንድ፣” ፊልጵስዩስ 2፥10
“እኔን ብታውቁኝ ኖሮ አባቴንም ባወቃችሁት ነበር። ከአሁን ጀምሮ ግን ታውቁታላችሁ፤ አይታችሁታልም።” ዮሐንስ 14፥7
የዚህ አንድምታ ምንድነው? እግዚአብሔርን የምናውቀውም ሆነ የሞናመልከው በክርስቶስ በኩል ካልሆነ የምናመልከው ያህዌን አይደለም።

Pursuing Holiness

21 Sep, 16:39


We can always count on Him. He might be silent. He might let things happen. But He will always be there. We might not know much about Him but we know that He is loyal. He is faithful and He is here 😊