House of Peoples' Representatives of FDRE

@parlamanews


የህዝብ ተወካይ የህዝብ አገልጋይ

House of Peoples' Representatives of FDRE

23 Oct, 07:59


ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማረጋገጥ ላይ መሆኗ ተመለከተ
---------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 13 ቀን ፣2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን እምርታ በማምጣት ላይ መሆኗን ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ አመላከቱ። 

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረገድ የረጅም ጊዜ ባለ ታሪክ መሆኗንም ገልፀዋል።

የዛሬው የሥልጠና ርዕሰ ጉዳይ "የፀጥታና ደህንነት እመርታ" የሚል ሲሆን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤቶች አመራሮች የሥልጠናው ገለፃ በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ቀርቧል።

ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ባቀረቡት ገለፃ ሀገራችን የፀጥታና የደህንነት ተቋማትን በመገንባት ረጅም አመታትን ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን እነዚህ ተቋማት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከማስጠበቅ አልፈው እንደ ኮሪያ፣ ኮንጎ እና በሌሎች ሀገራት በመሰማራት ሰላም የማስከበር ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት የቻሉ ናቸው ብለዋል።

ተቋማቱ የየራሳቸው ጥንካሬ ቢኖራቸውም የነበረባቸው ክፍተት ሊያርም በሚችል መልኩ አሁን ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አነሳሽነት ወቅቱን በሚመጥን ደረጃ የሪፎርም ሥራ በመሠራቱ ከፍተኛ አቅም ለመፍጠር ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።

ዘመኑ የኢኮኖሚ፣ የቴክኖሎጂ የበላይነት ፉክክር የሚታይበት ብቻ ሳይሆን የጦርነትም በመሆኑ ኢትዮጵያም ከየትኛውም አካል የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል የራሷን የፀጥታና ደህንነት ተቋማትን የመገንባትና በሪፎርም የማጠናከር ሥራ ሠርታለች፤ ትሰራለችም፤ ሲሉ አስገንዝበዋል።

በመሆኑም መከላከያን ጨምሮ በፀጥታ ተቋማት፣ በኢትዮጵያ የመረጃና ደህንነት፣ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት እና በፋይናንስ ደህንነት የተጠናከረ የሪፎርም ሥራ መሰራቱንም ነው ክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ ያብራሩት።

የክቡር ም/ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለፃ ዛሬ 6ኛ ቀን ባስቆጠረው ሥልጠና ላይ ቀጥሏል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

22 Oct, 17:21


"የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ሀገራዊ ጥቅሟንና የጎረቤት ሀገራትን የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የሚያተኩር ነው"

--- ክብርት ሙፈሪያት ካሚል--
              
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 12 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ ሀገራዊ ጥቅምን በጠበቀና የጎረቤት ሀገራትን የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የሚያተኩር ነው ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል አስገነዘቡ።

ሀገራዊ ጥቅምን በጠበቀና የጎረቤት ሀገራትን የጋራ ተጠቃሚነት እና ትብብርን መሠረት አድርጎ ጠንክሮ በመሥራት የውጭ ግንኙነት እመርታዋን እንደምታረጋግጥም ገልፀዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት "ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተማመን እና በትብብር በመስራት የውጭ ግንኙነት እመርታዋን ታረጋግጣለች" ሲሉ በአጽንኦት ተናግረዋል ።
              
ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ይህን ያሉት "የውጭ ግንኙነት እመርታ፤ ከገፅታ ግንባታ ወደ ተፅዕኖ ፈጣሪነት" በሚል ርዕስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች የቀረበ ገለጻን አስመልክቶ ከተሳታፊዎች ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት መድረክ ነው።

ኢትዮጵያ እራሷን ከተረጅነት በማውጣትና ያላትን አቅም በመጠቀም በኢኮኖሚ፣ ፖለቲካና ዲፕሎማሲ እምርታ በማምጣት በዓለም መድረኮች ላይ ተፅዕኖ የመፍጠር ደረጃ ውስጥ መግባት ያለባት በመሆኑ ከሀገራት ጋር ባላት ግንኙነት ላይ ጠንክሮ መሥራት ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነቱ ስራ የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ ሥራ እየሠራች እንደምትገኝ የገለፁት ወ/ሮ ሙፈሪያት፤ የብሪክስ ሀገራት ህብረት አባል መሆኗ የዚሁ አካል ነው ብለዋል።

እንዲሁም ኢትዮጵያ ከተረጅነት ወደ ረጅነት የሚያሸጋግራትን ሰፊ ሥራዎች በመሠራት ከገፅታ ግንባታ ባለፈ በዓለም አቀፍ ግንኙነት ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን ይገባታል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ዜጋ ተኮርና የልዕልና መር የውጭ ግንኙነት ፖሊስ የምትከተል መሆኗን አንስተው ከቅርብና ከሩቅም ካሉ ሀገራት ጋር በጋራ ትሠራለች ብለዋል። ይህም በመሆኑ የሀገሪቷን ተፅዕኖ ፈጣሪነት አቅም ማስደግ የሁሉም አካላት ርብርብን የሚጠይቅ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

አያይዘውም ኢትዮጵያ ከቅርብ ጎረቤት ሀገራት እንዲሁም ሌሎች በዙሪያዋ ካሉ ሀገራት ጋርም በቅርበት መሥራት እንደሚያስፈልግ የገለፁት ወ/ሮ ሙፈሪያት፤ ከዚህ በተጨማሪም በዘርፈ ብዙ ዲፕሎማሲ መድረኮች አባልነቷን በማጠናከር ድምጿ እንዲሰማ የማድረግ እንዲሁም አህጉራዊ በሆኑ ጉዳዮችም በንቃት መሳተፍ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

እንደ እሳቸው ገለፃ የሀገራችን ዕጣ ፋንታ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የመልማት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ይህንን ተግባራዊ የሚያደርጉ ፓሊሲዎችን ከመቅረፅ ጨምሮ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል።

ለዚህም የታላቁን የህዳሴ ግድብ ለአብነት አንስተው የህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ አልፎ በርካታ የጎረቤት ሀገራትን ያስተሳሰረ መሆኑን እንዲሁም በንግድና በሌሎች ዘርፎችም በትብብር እየሰራች መሆኗን አስረድተዋል። ለዚህም ዋነኛ ምክንያት የመደመር ዕሳቤ ላይ የተመሠረተ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲያችን ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ጂኦ ፖለቲካ እና ጂኦ ስትራቴጂክ ጉዳዮችን በጥልቀት የመረመረ መሆኑን ጠቁመው፤ ሀገሪቱ ጥቅሟን ከሚያስጠብቁ ሀገራት ጋር በትብብር የመሥራት ፍላጎት እንዳላት አብራርተዋል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት እንደገለፁት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ትልቁ የሥልጣን ባለቤት እንደመሆኑ የሀገራችንን ጥቅምና ተፅዕኖ ፈጣሪነት መሠረት በማድረግ የድርሻውን መወጣት ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል።

ስለዚህም የኢትዮጵያን ገፅታ ከመገንባት ያለፈ ሥራ በመሥራት የሀገሪቷን ተፅዕኖ ፈጣሪነት አቅም ከፍ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ምክር ቤቱ የሀገራችን ትልቁ ህልማችን ዕውን እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ ሊወጡ ይገባል ብለዋል ።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

22 Oct, 17:02


ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካና በአካባቢው አገራት ሠላምና መረጋጋት ለማስፈን ጉልህ ሚና እንዳላት የጀርመን ፖርላማ ልዑካን ገለፁ
-----------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ም፤ በኢትዮጵያና በአካባቢው አገራት ወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ከጀርመን ፖርላማ የሰብዓዊ መብት ኮሚቴ ልዑካን ጋር ተካሂዷል።

የውጪ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዲማ ነገዎ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን በአገር ውስጥና በአካባቢው ለማስፈን እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የአገር ውስጥ ግጭቶችን በውይይት ለመፍታት የአገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በሱማሊያና በሱዳን ሰላምና መረጋጋት ኢትዮጵያ በርካታ ሥራዎችን ማከናወኗን ጠቁመዋል።

አሁንም ሰላምና መረጋጋትን በውይይት ለማስፈን የበኩላችንን በመወጣት ላይ እንገኛለን በርካታ የጎረቤት አገራት ስደተኞችን ኢትዮጵያ ተቀብላ በማስተናገድ ላይ ትገኛለች ብለዋል።

በዓለም ላይ የሚደረጉ ጦርነቶች የአገራትን ዕድገት ወደ ኋላ የሚጎትቱ በመሆናቸው በውይይትና በንግግር መፍታት እንደሚገባ የተከበሩ ዲማ ነገዎ ዶ/ር ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ጉልህ ሚና እንዳላት ልዑካኑ ገልጸዋል።

በአካባቢው አገራት ሰላምን ለማስፈንና ግጭቶችን በውይይት ለመፍታት በኢትዮጵያ በኩል የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ተብሏል።

(በ በለጠ ሙሉጌታ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

22 Oct, 14:25


በኢትዮጵያና በሞንጎሊያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኝኑነት ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ
-----------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ም. ፤ በኢትዮጵያና በሞንጎሊያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል።

በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሞንጎሊያው የምክር ቤት አባል ሚስተር ባት ኡልዚ ባት-ኤርዴኔ የተመረውን የልዑካን ቡድን ተቀብሎ አነጋግሯል።

በምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዲማ ነገዎ (ዶ/ር)፤ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የቀጠለው የኢትዮጵያና የሞንጎሊያ ወዳጅነት የሁለቱን ሀገራት ሕዝቦች ጥቅምና ፍላጎት መሠረት ያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበርና የጋራ ጥቅምን መሰረት ያደረገ ግንኙነት በመፍጠር አካባቢያዊ ሰላምና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲረጋገጥ ጠንክራ እየሰራች ነው ሲሉም ሰብሳቢው ተናግረዋል፡፡

የሞንጎሊያው የምክር ቤት አባል ሚስተር ባት ኡልዚ ባት-ኤርዴኔ በበኩላቸው ሁለቱ ሀገራት በአህጉራዊ እና በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሁለቱን ሀገራት ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ በሚያስችሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በውይይቱ፤ በሁለቱ ሀገራት  የዲፕሎማሲ፣ የህዝብ-ለህዝብ ግንኙነት ፣ በምክር ቤቱ ስልጣንና ተግባራት  እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡ 

(በሚፍታህ ኪያር)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

22 Oct, 07:54


የዓለምን ነባራዊ ሁኔታዎች እና ጫናዎችን በመረዳት የውጭ ግንኙነት እምርታ ማምጣት የግድ አንደሚል ተገለጸ
-------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 12 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የዓለምን ነባራዊ ሁኔታዎችና ጫናዎችን በመረዳት የኢትዮጵያን የውጭ ግንኙነት እምርታ ማምጣት የግድ አንደሚል ተገለፀ። የዓለምን እጅግ ውስብስብ ሁኔታና  የሁኔታዎችን በፍጥነት መለዋወጥ በመረዳት ሀገሪቷ  የውጭ ግንኙነት ሥራዎቿን ማጠናከር እንዳለባት በአፅንዖት ተገልጿል።

ይህ የተገለፀው "የውጭ ግንኙነት እምርታ፤ ከገፅታ ግንባታ ወደ ተፅእኖ ፈጣሪነት" በሚል ርዕስ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች ለ6ኛ ቀን እየተሰጠ ባለው ሥልጠና በክቡር ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አስቀስላሴ እና በቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር ክቡር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በቀረበ ገለፃ ነው።

አሁን ላይ በዓለም በተፈጠረው ዘርፈ ብዙ የእርስ በርስ ትስስር፣ የተፈጥሮ ሀብትን በከፍተኛ ደረጃ መጠቀም እና ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ዕድገትና ጥቅም ላይ መዋል ዓለም በፉክክርና እና በውጥረት ላይ እንድትጠመድ ማድረጉም ተመላክቷል።

በቅርቡ በራሺያና በዩክሬን መካከል በተፈጠረው ጦርነት ታዳጊ ሀገራት የምግብ ግብአቶችን እና ማዳበሪያን ወደ ሀገራቸው እንዳያስገቡ በማድረጉ የኢኮኖሚ ጫና መፍጠሩ ተገልጿል።

ኢትዮጵያም በተፈጠሩ ዓለም አቀፍ ጫናዎች ውስጣዊ አቅሟን በማጠናከር በተለይ ስንዴንና ሌሎች የሀገር ውስጥ ምርቶችን በከፍተኛ ደረጃ በማምረት መቋቋም የተቻለ ቢሆንም በቀጣይም በቀጠናው በተለይ በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተገቢው መንገድ በመረዳት ከጊዜው ጋር የሚመጥን የራሷን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚኖርባትም ነው የተብራራው።

አሁን ላይ በኢኮኖሚው እና በውጭ ግንኙነት ረገድ የተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኙት እንደ ቻይና፣ ሕንድ፣ ቱርክና ሌሎች ቀደምት ሥልጣኔ ያላቸው ሀገራት መሆኑ ተጠቁሟል።

ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያም ቀደምት የስልጣኔ ሀገር ከመሆኗም ባሻገር በቅኝ ያልተገዛች፣ በኢኮኖሚ እያደገች የመጣችና የብሪክስ ሀገራት አባል መሆን የቻለች፣ ከአፍሪካ ትልቅ ሕዝብና የመልማት አቅም ያላት፣ በቀጠናው ተቀባይነት ያላትና ተፅእኖ ፈጣሪ የሆነች እንዲሁም ከፍተኛና ጥብቅ ማህበራዊ ትስስር ያላት ሕዝብ ባለቤት እንዲሁም በአፍሪካ አንድነት ጉልህ ድርሻ ያላት በመሆኗ በዓለም ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀገር የመሆን ዕድሏ ሰፊ መሆኑ ተብራርቷል።

ስለሆነም ኢትዮጵያ በውስጥ ያሉባትን ትንንሽ አለመግባባቶችን በጠረጴዛ ዙሪያ በውይይት በመፍታት ገጽታዋን መገንባት እና የውጭ ግንኙነት እመርታዋን ማረጋገጥ እንደሚኖርባት እየቀረበ ካለው ገለፃ ለመረዳት ተችሏል ።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

21 Oct, 16:41


የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የምክር ቤቱ ድጋፍ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት ተገለፀ
-----------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 11 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ በኢትዮጵያ የተጀመረው የኢኮኖሚ ሪፎርም የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የምክር ቤቱ ድጋፍ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ክቡር ካሣሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።


ክቡር ካሣሁን (ዶ/ር) የኢኮኖሚ አምርታ ለማምጣት ሰፊ ሥራዎች በመንግሥት እየተሠሩ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ይህንንም ከዳር እንዲደርስ ምክር ቤቱ በሕግ አወጣጥ፣ በክትትልና ቁጥጥር፣ ፖሊሲዎች እንዲወጡና ተፈፃሚ እንዲሆኑ ድጋፍ በማድረግ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል ።

ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ጎፌ ይህን የገለፁት "የምጣኔ ሀብት እመርታ - ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ተሟላ ብልፅግና" በሚል ርዕስ የፕላንና ልማት ሚንስትር በሆኑት በክብርት ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች የቀረበ ገለጻን አስመልክቶ ከተሳታፊዎች ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት መድረክ ላይ ነው።

ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ከኢኮኖሚ ዕድገቱ፣ ከዋጋ ግሽበትና ከኑሮ ውድነት እንዲሁም ከንግድ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ሲሰጡ ከለውጥ ወዲህ ባሉት ስድስት አመታት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳየቷ ጥርጥር የሌለው፣ የሚታይና የሚጨበጥ መሆኑን አስገንዝበዋል ።

ይህን የኢኮኖሚ ዕድገት የአለም ባንክና የገንዘብ ተቋማት ሁሉ የመሰከሩለት ነው ያሉት ክቡር ዶ/ር ካሣሁን፤ የዕድገቱ መነሻዎች የለውጡ መንግሥት ያሳየው ቁርጠኝነት እና የፖሊሲ ለውጦች መሆናቸውን በዋናነት ጠቅሰዋል።

አያይዘውም አሁን ላይ የተጀመሩ የኢኮኖሚ፣ የንግድ፣ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት በተለይ በስንዴ፣ በሩዝና ሌሎች ምርቶች ከፍተኛ የማምረት አቅም፣ የመደበኛና ትይዩ ንግድ ላይ የነበረውን ሰፊ ልዩነት በማጥበብ  እና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያዎች በመንግሥት ማድረግ በመቻሉ በአጭር ጊዜ በሀገራችን ኢኮኖሚ ላይ እያሳዩት ያለው ውጤት እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ ከዚሁ ጋር ተያይዞ በ2025 ዓ.ም. ኢትዮጵያ በዓለም ኢኮኖሚያቸው በከፍተኛ ደረጃ ካደጉ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ትገባለች፤ ከአፍሪካ ደግሞ በቀዳሚነት ተርታ ትሰለፋለች ሲሉ አብራርተዋል።

የኢኮኖሚ ዕድገቱ እንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም ዜጎች የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ተፅእኖ እንዳለባቸው ክቡር ዶ/ር ካሣሁን ጠቁመው፤ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ያለውን ጫና በመረዳት የደመወዝ ጭማሪ በማድረግ እና በሌሎች ልዩ ልዩ ድጎማዎች እንዲሁም እንደአጠቃላይ የሕዝብን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ በማምረት የገበያውን ሁኔታ በማስተካከል ኑሮን ለማቃለል መንግሥት እየሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

በቀጣይም መንግሥት ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ዜጎች በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መንገድ እየቀየሰ እንደሚሰራም ነው የገለፁት።

ከንግድ ሥርዓቱ ጋር በተያያዘ በርካታ ማነቆዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት መንግሥት ነፃ የንግድ ቀጠናን ጨምሮ በርካታ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑንም ክቡር ዶ/ር ካሣሁን አመላክተዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

21 Oct, 06:37


ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት የኢኮኖሚ እመርታ እንደምታስመዘግብ ተገለፀ
-----------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 11ቀን ፣2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ አራት አስርተ አመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ እመርታ እንደምታስመዘግብ የፕላንና ልማት ሚንስትር ክብርት ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለፁ።

የትንበያ ጥናቱ ከሀገራችን የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ባሻገር የውጭ ሀገራት ባለሙያዎችም ያረጋገጡት ነው ብለዋል።

ክብርት ዶ/ር ፍፁም ይህን የተናገሩት "እመርታ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ተሟላ ብልፅግና" በሚል ርዕስ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽህፈት ቤቶች አመራሮች እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ባቀረቡት ገለፃ ነው።

ሀገራት ባላቸው የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ ከሚያመርቱት ምርትና ከሚጠቀሙት ቴክኖሎጂ አንፃር ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ተብለው በሶስት እንደሚከፈሉ አብራርተዋል።

ክብርት ዶ/ር ፍፁም ሀገራችን አሁን ላይ በአፍሪካ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ካስመዘገቡ ሀገራት በ5ኛ ደረጃ፣ ከሰሃራ በታች ካሉት ሀገራት በ3ኛ እና ከምስራቅ አፍሪካ ደግም ቀዳሚውን ደረጃ መያዟን አስገንዝበዋል።

በአለም ባንክ በተደረጉ ጥናቶች ኢትዮጵያ በ2021 እና በ2022 ዓ.ም. በአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ዕድገት ከሚያስመዘግቡ ሀገራት 2ኛ ደረጃን እንደምትይዝ መጠቆሙን አብራርተዋል።

ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሁን ላይ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ሀብት፣ የሰው ሀይል፣ ይሄንን ማስፈፀም የሚችል መንግስት አኳያ ህልሟን እውን የማታደርግበት አንዳች ምክንያት እንደማይኖርም ነው ያስረዱት።

ስልጠናው ዛሬም ለ5ኛ ቀን ቀጥሏል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

20 Oct, 17:07


" የፖለቲካ ሪፎርሙ ለዘመናት የተከማቹ የፖለቲካ ባህል ችግሮቻችንን ለመፈታት የሚያስችለን ነው"
                    
--- የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ---

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 10 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ በመንግሥት እየተደረገ ያለው የፖለቲካ ሪፎርም ለዘመናት የተከማቹ የፖለቲካ ባህል ችግሮቻችንን ለመፈታት የሚያስችለን ነው ሲሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚንስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለፁ።

የፖለቲካ ሪፎርሙ በሀገር ደረጃ የተያዘውን የጋራና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል።

በዚህ ረገድ የምክር ቤት አባላት በሀገራችን ኢትዮጵያ የተጀመረውን የፖለቲካ ሪፎርም አጠናክረው የማስቀጠል ኃላፊነት እንዳለባቸው የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚንስትሩ አሳሰበዋል ።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ ይህን ያሉት በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ "የፖለቲካ እመርታ፤ ከዲሞክራሲ መብት ወደ ሀገራዊ ኃላፊነት" በሚል ርዕስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች ያቀረቡትን ገለፃ አስመልክቶ ከተሳታፊዎች ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ነው።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ የሥልጠናው ተሳታፊዎች የፖለቲካ ሪፎርም ለምን አስፈለገ? ሪፎርሙ ከተጀመረ ወዲህ ምን ምን ለውጦች ተገኝተዋል? በዚህ ሒደት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ምን ምን ናቸው? ተግዳሮቶቹን ለመቅረፍ ምን ምን ተሰርቷል ? በቀጣይስ የተገኙ ውጤቶችን እንዴት እናስቀጥላለን?  ፈተናዎችንስ እንዴት ተሻግረን ፖለቲካዊ እመርታ እናመጣለን? ከእኛ ከአባላትስ ምን ይጠበቃል? የሚሉ ነጥቦች በአግባቡ መታየት አለባቸው ብለዋል።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ የፖለቲካ ሪፎርም ያስፈለገበት ዋነኛ ዓላማ ቀደም ሲል በሀገራችን የነበረው ፖለቲካ የፅንፈኝነት አመለካከትን የተከተለ በመሆኑ፣ ፖለቲካዊ ባህል በበቂ ሁኔታ ባለመጠናከሩ እና ቅቡልነት ያለው ሀገረ መንግሥት ባለመገንባቱ የተነሳ እንደሆነ አብራርተዋል።

በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ የፖለቲካ ሪፎርም ሥራ ተጀምሯል፤ በዚህም በርካታ ውጤቶች ተመዝግበዋል ያሉት የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ፤ ፖለቲካውን ከፅንፈኝነት አላቆ ኅብረ ብሔራዊ የሆነውን የብልፅግና ፓርቲን መመሥረቱን፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በኃላፊነትና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ማሳተፍ መቻሉን፣ ሁሉን አካታች ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ወደ ሥራ መገባቱን ለአብነት አንስተዋል።

ከሥልጠናው ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥም ፓርቲው የመሀል ፖለቲካን ለምን ተከተለ?  የመሀል ፖለቲካን የተከተሉ ሀገሮችስ አሉ ወይ? የፖለቲካ እመርታን ማምጣትስ ይቻላል? የሚሉት በዋነኛነት ይገኙበታል።

ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ ማብራሪያ ሲሰጡ የምንከተለው የመሀል ፖለቲካ የወላዋይነት ሳይሆን ፅንፍና ፅንፍ የቆሙ አመለካከቶችን የሚያስታርቅና ወደ መሀል የሚያመጣ፣ ሁሉን አካታች፣ ኅብረ ብሔራዊነትን የሚያጠናክር፣ መግባባትን እና አንድነት የሚፈጥር ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

አክለውም የመሀል ፖለቲካን የሚከተሉ ሀገራት መኖራቸውን ጠቁመው፤ እኛ የምንከተለው የመሀል ፖለቲካ ግን ሀገር በቀል ከሆነው የመደመር ዕሳቤ የተቀዳ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም የፖለቲካ እመርታን ማምጣት ይቻላል ወይ? ለሚለው ጥያቄ፤ ህልማችንን እና የወል ትርክታችንን በአግባቡ ተረድተን ወደ ሕዝቡ ካሰረፅን፣ ነፃነትን በአግባቡ ማስተናገድ እና ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ከቻልን የፖለቲካ እመርታ ማምጣት እንችላለን ሲሉ የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አስገንዝበዋል። የምክር ቤት አባላት የተጀመረውን የፖለቲካ ሪፎርም አጠናክረው የማስቀጠል ኃላፊነት አለባቸው! በዚህ ረገድ የምክር ቤት አባላት ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን በመጠቆም።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

20 Oct, 08:48


የሕዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የፖለቲካ እመርታን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተጠቆመ
----------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 10 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የዲሞክራሲ፣ የፍትህና የመልካም አስተዳደር፣ የኢኖኮሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ወቅቱን የዋጀ ህዝብን ሁለንተናዊ ጥያቄዎችን የሚመልስ ፖለቲካ እመርታን ማረጋገጥ እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ ገለፁ።

ክቡር አቶ አደም ይህን የገለጹት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራርና አባላት እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች ለ4ኛ ቀን እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ "የፖለቲካ እመርታ፤ ከዲሞክራሲ መብት ወደ ሀገራዊ ኃላፊነት" በሚል ርዕስ ባቀረቡት ገለፃ ነው።

ክቡር አቶ አደም በሀገራችን ቀደም ባሉት ጊዜያት በነበሩ የመንግስት ስርዓቶች የህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ ያልተረጋገጠበት፣ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ምላሽ ያላገኙበት፣ ቁልፍ ፓለቲካዊ ተቃርኖዎችና ችግሮች ያልተፈቱበት ነበር ብለዋል።

ስለሆነም እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የፖለቲካ ሪፎርም ማካሄድ ይገባል ብለዋል። ይህ የፖለቲካ ሪፎርምም ተቃርኖዎችን ሊያስታርቅ የሚችል የመሀል ፖለቲካን የሚከተል፣ የህዝቦችን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች የሚመልስ፣ የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት እንዲሁም ብልፅግናዋን ሊያረጋግጥ የሚችል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ይህ ዕውን ይሆን ዘንድም ጠንካራ የዲሞክራሲ ስርዓትን እና ተቋማትን መገንባት እንዲሁም ይህን መምራት የሚችል ለፈተናዎች የማይንበረከክ ፅኑ እና ፈተናዎችን ወደ እድል እየቀየረ የሚሰራ አመራር እንደሚያስፈልግም ነው ክቡር አቶ አደም ፋራህ ባቀረቡት ገለፃ ያሳሰቡት።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

19 Oct, 15:32


"የምክር ቤት አባላት ለተቋማት እና ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል"

-- ምክትል አፈ-ጉባኤ ---

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 09 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የምክር ቤት አባላት ለብሔራዊነት፣ ለተቋማት እና ለጠንካራ ሀገር መንግሥት ግንባታ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አሳስበዋል።

የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ይህን ያሉት "ተቋማዊ ግንባታ፤ ለሀገር እመርታ" በሚል ርዕስ በክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ የቀረበውን ገለፃ አስመልክቶ ከሥልጠናው ተሳታፊዎች በቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።

የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ዋነኛ ተዋናይ የፖለቲካ አመራሩ ቢሆንም የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ፣ ሚዲያዎች፣ እያንዳንዱ ተቋም እንዲሁም ግለሰቦች የራሳቸው ሚና መወጣት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሀገረ መንግሥት ግንባታው የተዛቡ አመለካከቶችን ከማስተካከል፣ የራስ አቅምን ከመገንባት፣ በትብብር መንፈስ ከመስራት ይጀምራል ያሉት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ፤ የተቋማት ግንባታ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት በመሆኑ የተቋማት ግንባታ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል።

አያይዘውም የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሒደት እንጂ በአንድ ጊዜ የሚጠናቀቅ ባለመሆኑ የምክር ቤት አባላት፣ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት እና የእያንዳንዱን ዜጋ ርብርብን እንደሚጠይቅም ነው ያመላከቱት።

የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ከለውጡ ወዲህ በኢትዮጵያ የተገነቡ ጠንካራ ተቋማት መኖራቸውን አንስተው በተለይ በፀጥታ ተቋማት፣ በሚዲያ ተቋማት፤ በፍትሕ ተቋማት እንዲሁም በምክር ቤቶች የተሻሉ የሕግ ማዕቀፎች እንዲወጡ ማድረግ እንደተቻለ አብራርተዋል ። እንደ ወ/ሮ ሎሚ ገለፃ በቀጣይም እንደ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ያሉ ሁሉን አካታች ጠንካራ ተቋማት ሆነው እንደሚገነቡ እና የሌሎችም ተቋማት ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።

በቀጣይም ምክር ቤቱ ለጠንካራ ተቋማዊ ግንባታ አጋዥ የሆኑ ሕጎችንና ፓሊሲዎችን የማውጣት፣ ተፈፃሚነታቸውን በክትትልና በቁጥጥር ማጠናከር፣ ራስን ፈትሾ ለሥራ መዘጋጀት እንደሚጠበቅበትም ነው ያሳሰቡት።

ሚዲያዎችም የተሰሩ ሥራዎችን እና ብሔራዊ አንድነትን የሚሰብኩ ትርክቶችን ወደ ሕዝቡ ማስረፅ እንዳለባቸው የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ተናግረዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

19 Oct, 12:52


ስልጠናው ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር ተመላከተ
--------------------
(ዜና ፓርላማ)ጥቅምት 09 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለምክር ቤቱ አመራሮችና አባላት እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አመላክተዋል፡፡  

ስልጠናው ምክር ቤቱና የምክር ቤት አባላት ሀገራችንን ከወቅታዊ አለምዓቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማገናዘብ በህገ-መንግስቱ የተሰጠንን የህግ አወጣጥ፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የህዝብ ውክልና ስራችንን በሙሉ አቅምና ብቃት ለመወጣት ያስችላል ብለዋል፡፡

የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አክለውም ስልጠናው ሀገራችን በተጨባጭ እያስመዘገበች ያለውን እመርታ፣ ያጋጠሟትን ተግዳሮቶችን እና እነዚህን ተግዳሮቶች በአንድነት በመቆምና በትብብር መንፈስ በጋራ በመስራት መወጣት እንደሚቻል ያሳየም ነው ብለዋል፡፡

ከለውጡ ወዲህ በሀገራችን ብዙ ማሻሻያዎች ተደርገዋል፤ ሰፋፊ ስራዎች ተሰርተዋል ያሉት የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እኛም እንደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና እንደ ምክር ቤት አባል ተሳትፏችን የጎላ ነበር ሲሉ አብራርተዋል፡፡

ስለሆነም በቀጣይ ምክር ቤቱም ሆነ የምክር ቤት አባላት ከስልጠናው የሚገኘውን ዕውቀት፣ ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም፣ ከተቋማት ጋር በመቀናጀትና ተናቦ በመስራት፣ እንዲሁም የሚሰጡ ቀጣይ ሀገራዊ አቅጣጫዎችን በአግባቡ በመያዝ ሀገራችንን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች በማጠናከር ወደተሻለ ከፍታና ብልጽግና የማሸጋገር ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅብናል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ‹‹የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት›› የሚለው አለማቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ጥቅል የሆነ ሀሳብን የያዘ በመሆኑ የነበራቸውን ግንዛቤ ይበልጥ እንዳሳደገላቸው ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ዛሬ ላይ አደጉ የሚባሉት ሀገሮች የራሳቸውን ህልም አስቀምጠው እንዳሳኩ ሁሉ ሀገራችንም ወደ ብልፅግና የሚሻግራት ህልም ማስቀመጥ በመቻሏ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ያገኙት ይህ ህልም ዕውን እንዲሆንም ለመራጭ ህዝባቸው በአግባቡ በማስገንዘብ ሀሳቡ እንዲሰርጽ ማድረግ እና በክትትልና ቁጥጥር ስራቸው ውስጥ በማካተት እንዲሰሩም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል፡፡

የተሰጡንን ሀገራዊ ተልዕኮዎችን በአግባቡ በመወጣት፣ ከግጭት እና ከፅንፈኝነት አመላከት በመውጣት፣ ችግሮቻችንን በጋራ በመፍታት እንዲሁም ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር ሀገራችንን ወደተሻለ ከፍታ ማሻገር ይጠበቅብናልም ነው ያሉት፡፡

በመጨረሻም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላት በቀጣይም በሚሰጡ የስልጠና ርዕሶች ላይም በአግባቡ እንዲሳተፉና የተሻለ ዕውቀትና ግንዛቤ እንይዛለን ብለው እንደሚጠብቁም ገልጸዋል፡፡  

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

19 Oct, 06:10


"ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ ነው"

------ ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ -----

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 09 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ አስገንዝበዋል።

ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ለኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመሮችና አባላት ዛሬ ለሶስተኛ ቀን በቀጠለው ስልጠና "ተቋማዊ ግንባታ፤ ለሀገር እመርታ" በሚል ርዕስ ገለፃ እያደረጉ ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ በገለፃቸው ሀገራችን ከብዙ አመታት በፊት የዲሞክራሲ መገለጫ የሆነውን የገዳ ስርዓትን እና ወታደራዊ መዋቅሮችን ጨምሮ ሌሎች ተቋማትን የመገንባት ጅምሮ ቢኖራትም እስከመጨረሻው ድረስ ባለመዝለቁ ሀገራችንን ማሳደግ አልቻልንም ብለዋል።

ስለሆነም ይህ ትውልድ ኢትዮጵያን ለማሳደግ ጠንካራ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ጀምሮ እስከ ማጠናቀቅ ድረስ ረጅም ርቀትን በቁርጠኝነት ሊሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

18 Oct, 17:20


የጋራ ትርክት ሀገራዊ ህልምን ዕውን ለማድረግ አጋዥ መሆኑን አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን ለማድረግ የጋራ ትርክት መፍጠር አስፈላጊና አጋዥ ነው ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ።

ክቡር አቶ ዛዲግ ይህን የገለፁት "የትርክት እመርታ፤ ከታሪካዊ ስብራት ወደ ሀገራዊ ምልአት" በሚል ርዕስ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተሰጠው የሥልጠና ርዕስ ጉዳይ ላይ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ማጠቃለያ በሰጡበት ወቅት ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍ ላይ በሚነሱ አንዳንድ ክፍተቶች ምክንያት የጋራ ታሪክና የወል ትርክቶች መፍጠር አለመቻሉን ገልፀዋል ።

በመሆኑም እነዚህ አሉ የሚባሉ የታሪክ አተራረክ ክፍተቶችን በማረቅ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና የጋራ የሆነ ትርክት መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የታሪክ አለመግባባቶች አሉ ማለት ግን ሁሉንም ታሪኮች አሽቀንጥሮ መጣልና ትክክለኛ ያልሆኑ ታሪኮች መነሻ በማድረግ ወደ ግጭት መግባት ማለት አለመሆኑን የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ ጥሩ ጥሩ ታሪኮችን መቀበልና ከተዛቡ ታሪኮች ደግሞ ትምህርት መውሰድ ያስፈልጋልም ነው ያሉት።

የታሪክ አለመግባባት በሚኖርበት ሁኔታ የጋራ ትርክትን ለመፍጠር እንደችግር የሚታይ  እንደሆነ የገለፁት  ክቡር አቶ ዛዲግ፤ ዋናው ጉዳይ ግን በእውነት ላይ ያልተመረኮዙና በምናብ በተፈጠሩ ታሪኮች ሳቢያ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ለመከላከል የጋራ እውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት መገንባት ይገባል ብለዋል። በታሪክ የተነሳ የሚፈጠሩ  አለመግባባቶችንም  በቀጣይ  ለመቅረፍ እንደ ሀገራዊ የምክክር መድረኮች የመሳሰሉ ዕድሎች መፍትሔ እንደሚሆኑም አመላክተዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ህልም ዕውን ይሆን ዘንድም የጋራ እና አሰባሳቢ የሆነ ትርክትን መፍጠርና በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት እና የምክር ቤት አባላት በዚህ ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)


ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

18 Oct, 12:05


የትርክት እምርታ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየተሰጠ ነው
-----------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የትርክት እምርታ- ከታሪካዊ ስብራት ወደ ሀገራዊ ምልዓት በሚል በሀገር ደረጃ የትርክት እምርታ ለማምጣት ያለመና  የጋራ መግባባትንና አንድነትን ለመፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እየቀረበ ባለ የሥልጠና ገላጻ በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመሮችና አባላት ዛሬ  አየተሰጠ ነው።

የዕለቱ ሥልጠና  በዋናነት የወል ትርክት እንዲኖር መሥራት እንደሚገባና ይሔም የጋራ መግባባትንና አንድነትን የመፍጠር ኃይል እንዳለው ተጠቁሟል።

ሥልጠናው ዛሬም ለሁለተኛው ቀን ቀጥሏል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)


ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

18 Oct, 07:59


"ሀገራዊ ህልም ዕውን እንዲሆን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የራሳቸውን ገንቢ ሚና መወጣት አለባቸው"

-------- ክቡር አደም ፋራህ -------

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ሀገራዊ ህልም ዕውን እንዲሆን እንደሀገር ባስቀመጥናቸው የጋራ ህልም ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የራሳቸውን ገንቢ ሚና መወጣት አለባቸው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ ገለፁ።

የምክር ቤት አባላት ካለባቸው ሕዝባዊ ኃላፊነት አኳያ የሀገር ህልም እንዲሳካ ከፍተኛ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ  በሚከታተሏቸውና በሚቆጣጠሯቸው ተቋማት እና በመራጭ ህዝባቸው ውስጥ እንዲሠሩ ያስፈልጋል፤ ይህን መነሻ በማድረግ ኃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ሲሉ አስረድተዋል።

ክቡር አቶ አደም ይህን የገለጹት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤቶች አመራሮች እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ነው።

ክቡር አቶ አደም ለሰልጣኞች በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) "የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ ዕድገት"  በሚል መሪ ርዕስ  በቀረበው ገለፃ ላይ  ከሰልጣኞች ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ክቡር አቶ አደም ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ከፍታ የሚያደርሳትን እና ለትውልድ የሚሻገር ህልም ተልማለች፤ ይህ ህልም እውን ይሆን ዘንድም ምቹ ነባራዊ ሁኔታዎች አሏት ብለዋል።

በመሆኑም የሀገራችንን መበልፀግ እውን ለማድረግ የጋራ ህልም ሊኖረን የሚገባ ሲሆን፤ ህልማችን በረጅም ግዜ  የሚሳካ በመሆኑ ህልማችን እውን ይሆን ዘንድ ኃላፊነታችንን በተገቢው ደረጃ መወጣት አለብን ሲሉ ገልፀዋል።

ህልምን ህያው ከሚያደርጉ ነገሮች ውስጥ አንዱ ትክክለኛ ሐሳብ መሆኑን የገለፁት ክቡር አቶ አደም የመደመር ሐሳብ ኢትዮጵያን ከማሻገር አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ጭምር የሚተርፍ መሆኑንም አብራርተዋል።

አያይዘውም ሀገሪቱ ያላት እምቅ የተፈጥሮ ሀብት፣ ከዓላማው ጎን የሚሰለፍ ሕዝብ እንዲሁም የተገነቡ ተቋማት የሀገራችንን ህልም ዕውን ለማድረግ አስቻይ ሁኔታዎች ከሚባሉት ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱ መሆኑን አስረድተዋል።

ህልም የጋራ መረዳትና ርዕይ ጋር የተገናኘ እንደሆነና በምናቅዳቸው ዕቅዶች፣ ልዩ ልዩ ስትራቴጂዎችና በምንሠራቸው ሥራዎችና ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል ይህን ህልም ዕውን ለማድረግ በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥ በርካታ ተግዳሮቶች እንዳሉ ክቡር አቶ አደም ጠቁመው፤ እነዚህን ተግዳሮቶች ለመቋቋም የአመራሩ ፅናት፣ የሐሳብና የተግባር አንድነት መኖር፣ ከሕዝብ ጋር በትስስር መሥራት እና የጋራ ህልማችንን በመደመር ዕሳቤ በሕዝብ ዘንድ እንዲሰርጽ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መሥራት ወሳኝ ናቸው ሲሉም ነው ክቡር አቶ አደም ያስገነዘቡት።

በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር,) ህልምን አስመልክቶ በቀረበው ገለፃ መሠረት ቻይናን ጨምሮ በኢኮኖሚ ያደጉ ሀገራት ለእድገታቸው መሠረት የሆነ ህልም እንዳላቸው ሁሉ ኢትዮጵያም ወደ ብልፅግና የሚያሻግራት የጋራ የሆነ ህልም አስፈላጊ መሆኑ ተብራርቷል።

ህልም ከትላንት ይልቅ ዛሬ ላይ፣ ከዛሬ ይልቅ ደግሞ ነገ ላይ የሚያተኩር፣ አንዱ ትውልድ የሚጀምረው፣ ቀጣዩ ትውልድ የሚኖረው እንደሆነም ነው የተገለፀው።

የሀገሪቱ ህልም ዕውን የመሆን ትልቅ ተስፋ ከወዲሁ እየታየ መሆኑ፣ ለዚህም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በለውጡ ውስጥ የገጠሙንን ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ ከፍተኛ ዕድገት እያሰመዘገበ መምጣቱን በተለይም ከባለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ እንደሆነም ነው የተገለፀው።

ክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ አክለውም ቡናን ጨምሮ የሀገሪቱ የግብርና ምርቶች በዓለም እና በአፍሪካ የቀዳሚነት ደረጃን እየያዙ መምጣታቸው፣ አለምን ያስደነቀ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች መሠራቱ፣ የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ መድረሱ፣ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች፣ የኮሪደር ልማት መስፋፋት ማሳያዎች መሆናቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ህልም ዕውን እንዲሆን በጋራ መሥራት እንደሚገባም አንስተው የአመራሪ ፅናት፣  ቁርጠኝነት፣ በመተማመን እና በትብብር መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

17 Oct, 14:41


"ሥልጠናው ሀገራዊ ጉዳዮችን ከዓለም እና ሀገር አቀፍ ነባራዊ  ሁኔታዎችን አንፃር ለመረዳት ትልቅ  ሚና አለው" ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚንስትር
------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 07 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና አመራሮች እየተሰጠ ያለው ሥልጠና ሀገራዊ  ጉዳዮችን ከዓለም እና ሀገር አቀፍ ነባራዊ  ሁኔታዎችን አንፃር ለመረዳት  ትልቅ  ሚና አለው ሲሉ  የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።  

የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ ሥልጠናው ከዓለም ዓቀፋዊ፣ አህጉራዊ እና ከሀገር አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር አስተሳስሮ ሀገራዊ ጉዳዮችን በተገቢው መገንዘብ እንደሚገባም ገልፀዋል።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ ይህን ያሉት የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ ዕድገት በሚል መሪ ርዕስ እየተሰጠ ባለው ሥልጠና ላይ ሲሆን ይህ ሥልጠና የሀገሪቷን የመበልፀግ ህልም ወደ እውነታነት የመቀየር ትልቅ አቅም የሚፈጥር   መሆኑን አመላክተዋል።

ሥልጠናውም ዋናውን ርዕስ ሊያጎለብቱ በሚችሉ በዘጠኝ ክፍሎች ተከፋፍሎ እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ በእነዚህ ክፍሎችም ሀገራዊ ህልሞቻችንን ለማሳካት በሄድንባቸው ርቀቶች የተገኙ ስኬቶች፣ ያጋጠሙን ተግዳሮቶች እና እነዚህን ተግዳሮቶች ለመወጣት ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ጉዳዮች የሚሸፍን መሆኑን  የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ ገልፀዋል።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ አክለውም በሥልጠናው ሒደትም የምክር ቤቱ አመራሮችና አባላት ተገቢውን ግንዛቤ የሚይዙበት፣ የካበተ ልምድና ተሞክሯቸውን የሚያጋሩበትና ተጨማሪ ግብአት የሚገኝበት፣ የሚጠበቅባቸውን ተግባርና ኃላፊነት ይበልጥ የሚለዩበት በመጨረሻም የጋራ ግብ እና የጋራ ዕይታ የሚፈጠሩበት ነውም ብለዋል።

የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ በቀጣይ ዘጠኝ ቀናት በሚሰጡ የሥልጠና ርዕሶች ዋናውን ርዕሰ ጉዳይ (የህልም ጉልበት ለእምርታዊ ዕድገት) የሚያጠናክሩ በትርክት፣ በፖለቲካ፣ በምጣኔ ሀብት፣ በውጭ ግንኙነት፣ በፀጥታና ደህንነት፣ በተቋማት ግንባታ፣ በሥነ-ምግባር እና ሰብዓዊ እምርታና በአመራር ግንባታ ለይ  ሰፋፊ ሐሳቦች እንደሚነሱ ገልፀዋል።

በመጨረሻም የተከበሩ ዶ/ር ተስፋዬ በስልጠናው አለም ዓቀፍ፣ አህጉራዊና ቀጠናዊ እንዲሁም ሀገራዊ ጉዳዮች በሚገባ የሚዳሰሱበት እና ብዙ ውጤት የሚጠበቅበት በመሆኑ ሁሉም አካል በንቃት እንዲሳተፍ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

17 Oct, 08:34


ምክር ቤቱ ለአመራሮችና ለምክር ቤት አባላት ሥልጠና መሰጠት ጀመረ
-------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 07 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አመራሮች "የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ ዕድገት"  በሚል መሪ ርዕስ ላይ በአፍሪካ የልህቀት ማዕከል ሥልጠና መሰጠት ተጀምረ።

ሥልጠናውን በንግግር የከፈቱት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሠ ጫፎ ለምክር ቤት አባላት አምና በተመሳሳይ ጊዜ ሥልጠና መሰጠቱን እና ምክር ቤቱ በክቡር ፕሬዝዳንቱ የመክፈቻ ንግግር ሥራውን መጀመሩን አስታውሰዋል።

ዛሬ በመጀመሪያው ቀን "የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ ዕድገት"  በሚል ርዕስ የሚሰጠው ሥልጠና አምና በተመሳሳይ ወቅት ለምክር ቤቱ ለአመራሩና ለአባላት ከሰጠው ሥልጠና ጋር  የተያያዘና የምክር ቤቱን ሥራ ይበልጥ የሚያጠናክር እንደነበር አንስተው ዘንድሮም በበጀት ዓመቱን የምክር ቤቱን ሥራ በስኬት ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን የሚፈጥር ሥልጠና እንደሚሆን አብራርተዋል።

የተከበሩ አፈ-ጉባኤው አያይዘውም ሥልጠናው በሀገሪቱ የተጀመረውን ሪፎርም የሚያፀና፣ የጋራ ግንዛቤን የሚፈጥር እና የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነትን የሚፈጥር መሆኑንም ገልፀዋል።

ሥልጠናው ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን በጥልቀት የሚዳስስ በመሆኑ ሁሉም የሥልጠና ተሳታፊ በትኩረት መከታተል እንዳለበት አሳስበዋል ።

እንደ ምክር ቤት አባልነት ከተሰጠን ሕዝባዊ ኃላፊነት አኳያ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ከፍታ ለማድረስ የጋራ ህልም አለን ያሉት አፈ-ጉባኤው ለዚህ ስኬትም ሁሉም አካል የሚጠበቅበትን ሚና በአግባቡ በመገንዘብ የተጣለበትን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ በማስገንዘብ ሥልጠናውን በይፋ አስጀምረዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

16 Oct, 13:51


ቋሚ ኮሚቴው በሁለት ረቂቅ አዋጆች ላይ ከአስረጂዎች ጋር ተወያየ
-------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 06 ፣ 2017 ዓ.ም፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በመድሀኒት ፈንድና የኢትዮጵያ የመድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ማቋቋሚያ እንዲሁም የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጆች ላይ ከአስረጂዎች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይቱም ከቋሚ ኮሚቴው ረቂቅ አዋጆቹን አስመልክቶ ከቴክኒክና ከትርጉም አንጻር በርካታ ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ሌሎችም የስራ ሀላፊዎች ረቂቅ አዋጆቹን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የጤና አገለግሎት ፍላጎት ለማርካትና በዘርፉ ያሉትን ተግዳሮቶች በአግባቡ ለመፍታት የመድሀኒት ፈንድና የኢትዮጵያ የመድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ዘመናዊ የአሰራር ስርአት መከተል እንደሚገባው ተገልጿል፡፡

በተለያዩ ህጎች ተበታትነውና ለአፈጻጸም ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ የሚገኙ የጤና አገልግሎቶችን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በአንድ ማዕቀፍ ሕግ እንዲወጣላቸው አስፈላጊ ስለመሆኑም ተጠቁሟል፡፡

ወቅቱ ከደረሰበት ደረጃ የተጣጣመ አዳዲስ የጤና አገልግሎት ድንጋጌዎችን በማካተት በስራ ላይ የነበሩ ድንጋጌዎችን በማሻሻል ወጥ እና ለአፈጻጸም ግልጽ የሆነ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ የህግ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግም ተብራርቷል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ሌሎች የስራ ሀላፊዎች ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ወርቀሰሙ ማሞ የተነሱ ጥያቄዎችና የተሰጡ አስተያየቶችን እንደ ግብአት በመጠቀም ማስተካከል እንደሚገባና ረቂቅ አዋጆቹ በቀጣይም ውይይት የሚደረግባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

(በ ፋንታዬ ጌታቸው)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

House of Peoples' Representatives of FDRE

16 Oct, 08:13


ዜና ዕረፍት

የቀድሞ የምክር ቤት አባል ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞ የምክር ቤት አባል የነበሩት ጌታቸው መለሰ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ዶ/ር ጌታቸው መለሰ ከአባታቸው ከአባሆይ መለሰ በላይ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ እማዋይሽ ጫኔ በአማራ ብሔራዊ ክልል፤ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ወረዳ ክበበ ገብርኤል ቀበሌ የካቲት 11 ቀን 1962 ዓ.ም. ተወለዱ።

ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስም በየደረጃው የተከታተሉ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከዓለማያ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ሳይንስ፣ ሁለተኛ ጂግሪያቸውን በአለም አቀፍ ግንኙነት እንዲሁም 3ኛ ወይም የዶክተሬት ዲግሪያቸውን በፖለቲካ ሳይንስ አግኝተዋል።

ዶ/ር ጌታቸው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን በተለያዩ ሀላፊነቶች ያገለገሉ ሲሆን ካገለገሉባቸው ውስጥ ዋና ዋናዎቹ በ4ኛ እና በ5ኛ ዙር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአባልነት በመመረጥ በተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎች በሰብሳቢነት እንዲሁም ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በፌደራል የህብረት ስራ ማህበራት ኮሚሽን በኮሚሽነርነት ማገልገላቸው ተጠቃሽ ናቸው።

ዶ/ር ጌታቸው ባለትዳርና የሁለት ወንዶች ልጆች አባት ነበሩ።

በውጭ እና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ዶ/ር ጌታቸው መለሰ የቀብር ስነ-ስርዓታቸው ዛሬ ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ አበባ ከተማ ገርጂ በሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከቀኑ 9:00 ወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም የስራ ባልደረቦቻቸው በተገኙበት የሚፈጸም ይሆናል።

የኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በዶ/ር ጌታቸው መለሰ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

House of Peoples' Representatives of FDRE

14 Oct, 10:26


ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በድምቀት ተከበረ
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 4፣ 2017 ዓ.ም፤ 17ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን "ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን ፤ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪቃል በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በድምቀት ተከብሯል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ለ17ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓለማ ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በዓሉ ሰንደቅ አለማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፤ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪቃል በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በድምቀት ተከብሮ የሚውል መሆኑን ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ፕሬዘዳንት ክቡር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በዓሉን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ሰንደቅ ዓላማ የብሔራዊ አንድነታችን፣ የነጻነታችን እና የሉዓላዊነታችን መገለጫ አርማችን ነው ብለዋል።

ሰንደቅ ዓላማችን ጀግኖች ኢትዮጵያ አባቶቻችን በመተባበር በተለያዩ ጊዜያት የውጭ ወራሪዎችን ያሸነፉበት እና ሉዓላዊነታቸውን ያስከበሩበት የነጻትና የእኩልነት ደማቅ ምልክታችን ነው ሲሉ ፕሬዘዳንቱ አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ አንድ ሆና እንደብዙ ብዙሆና እንደ አንድ የምትገለጸው በሰንደቅ ዓላማችን ነው ያሉት ፕሬዘዳንቱ፤ ሉዓላዊነታችንን በማስከበር እና አንድነታችንን በማጠናከር የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልጽግና ልናረጋግጥ ይገባል ብለዋል።

ትውልድ የብሔራዊ አንድነት መገለጫ የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ አርማውን በማንገብ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ የማሸጋገር ትልቅ ሀላፊነት እንዳለበት ክቡር ፕሬዘዳንቱ አስታውቀዋል።

በሀገሪቱ የሚገኙ የፖለቲካ ሀይሎች ልዩነታቸውን ተቀራርበው እንዲፈቱ መንግስት ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ፕሬዘዳንቱ፤ በሌላ በኩል ብሔራዊ አንድነታችንን እና ሉዓላዊነታችንን በማስከበር ኢትዮጵያን በሁሉም ዘርፍ ከፍ ማድረግ የሚጠበቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በከብረ በዓሉ ሰነ-ስርዓት ክበር ፕሬዘዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ታዳሚያን በተገኙበት የኢትዮጵያን የሰንደቅ ዓለማ ከፍ አድረገው ሰቅለዋል።

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክቡር ፕሬዘዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ብሔራዊ ሰንደቅ ዓለማ በማክበር ኢትዮጵያ ወደ ተሻለ እድገት መሸጋገር እንድትችል የበዓሉ ተሳታፊዎች በተሰማሩባቸው የስራ ዘርፎች ተግተው እንዲሰሩ ቃለ ማህላ አስፈጽመዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።