Ministry Of Education Ethiopia

@minstery_of_education


For more info Web :- moe.gov.et
To contact us Mail :- [email protected]
+251 11 156 5529
We are promoting Educational Achievements

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:26


YONAS NUGUSE GEBREMARIAM

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:26


Ethiopian Secondary School Leaving Certificate Examination (ESSLCE)
--------------------------------
YONAS NUGUSE GEBREMARIAM
Admission No: 5667384
Gender: M
Stream: Natural Sc.
School: QELAMINO PRE.
--------------------------------
・ Chemistry: 96
・ English: 95
・ Physics: 97
・ Biology: 98
・ Mathematics: 100
・ Scholastic Aptitude Test: 91
・ Civics & Ethical Edu.: 98
---------------------------------
Your total score is 675

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:26


ABDI HUSSEIN HEBO

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:26


Ethiopian Secondary School Leaving Certificate Examination (ESSLCE)
--------------------------------
ABDI HUSSEIN HEBO
Admission No: 3765376
Gender: M
Stream: Social Sc.
School: ABDI BORU
--------------------------------
・ Mathematics: 78
・ English: 78
・ Geography: 90
・ Scholastic Aptitude Test: 73
・ History: 94
・ Economics: 88
---------------------------------
Your total score is 501

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:24


የ12ኛ ክፍል ውጤትዎን ይመልከቱ!

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል።

በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ተመልከቱ፦

► በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

► በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

► በቴሌግራም ቦት 👉 https://t.me/EAESbot

ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማተም እንደምትችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መሔድ ሳያስፈልጋችሁ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

አገልግሎቱ በቅሬታችሁ ላይ ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል።

@Minstery_of_education

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:24


በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 5.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ።
-------------------------------------------------
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሚኒስትሩ እንደገለጹት ለአገር አቀፍ ፈተና ከተቀመጡ 674,823 ተማሪዎች ውስጥ 36, 409 ወይም 5.4 በመቶ የማለፊያው ውጤት ማግኘታቸውን ገልጸዋል። የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ በ9,114 ተማሪዎች ብልጫ እንዳለውም ተናግረዋል።

በዚህም በተፈጥሮ ሳይንስ 28,158 ወይም 9 በመቶ በማህበራዊ ሳይንስ 8,251 ወይም 2 በመቶ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አመላክተዋል።

በፈተናው 1,221 ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን የገለጹ ሲሆን በባለፈው ዓመት ከተመዘገበው 220 አንጻር የተሻለ ውጤት መሆኑም ተገልጿል። ቀደም ሲል በነበረው የመሰናዶ ትምህርት በትግራይ ክልል ፈተናቸውን ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል ከ700 በተፈጥሮ ሳይንስ ከትግራይ ቀላሚኖ ት/ቤት አንድ ተማሪ 675 ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ፈተናቸውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከ600 በተፈጥሮ ሳይንስ ከአዲስ አበባ አግዚሊየም ካቴድራል ት/ቤት 575 (በሴት ተማሪ) በማህበራዊ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ኢትዮ ፓረንትስ 538 (በሴት ተማሪ) ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል ።

በዚህ ዓመት ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከአምናው በተሻለ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ 1,363 ት/ቤቶች ግን ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ጠቁመዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም 50 በመቶና በላይ ያመጡት በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ ጠቅሰው የተወሰኑ ተማሪዎችም በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:24


የ12 ተኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ማታ ለሊት 6 ሰዓት ላይ ይፋ ይደረጋል

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:24


የ12 ተኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ማታ በ https://eaes.edu.et/ reals ይደረጋል

ለመላው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኞች መልካም እድል

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:23


ነገ መጨረሻ ሳይሆን አዲስ ጅምር ነው። መጪው ጊዜ ምንም ቢሆን ብሩህ ነው። ነገን በተስፋ፣ በእምነት እና በጽናት እንጠብቅ - ሁል ጊዜ ወደፊት ብዙ መንገዶች አሉ እና የልጆቻችን አቅም ገደብ የለሽ ነው። በተነገረን መንገድ ብቻ አይደለም። እዚህ ስንደርስ በራሳችን መንገድ ነው የተጓዝነው እንጂ የቤተሰባችን መንገድ አይደለም። ስኬት ለልጆቻችን ከምንጠብቀው ይልቅ ልናደርገው የምንችለው ነገር ነው። በሚችሉት ከጎናቸው እንቆማለን። ተስፋ አንቆርጥም.



ለነገ መልካሙን ሁሉ እመኛለሁ! ”

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:23


የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይለቀቃል እስከዚያ ድረስ ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:21


የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ይፋ ይደረጋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም እንደሚገለጽ አሳውቋል።

የዘንድሮው ብሔራዊ ፈተና በቅይጥ ማለትም በወረቀት እና በኦንላይን መሰጠቱ ይታወሳል።

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:13


#12_ክፍል

ከ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጋር በተያያዘ አሁን ያለው ሂደት ከመገናኛ ብዙሀን ከትምህርት ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ገለጻ ተደርጓል።

ከቢሮው የተገኘ የመገናኛ ብዙሃን ምንጭ እንደገለጸው "ባለፉት ዜናዎች በቲክ ቶክ, ቴሌግራም እና ፌስቡክ ላይ ያለውን ግራ መጋባት እናያለን.

የፈተና ዉጤቱ የሚገለፅበትን ቀን በተመለከተ እስካሁን የፈተና ውጤቶችን ማረጋገጥ አለመጠናቀቁን ምንጫችን ገልጿል።

"እንደሚታወቀው በዚህ አመት ፈተናው በኦንላይን እና በወረቀት የተሰጠ ሲሆን ሁሉም ፈተናዎች ኦንላይን መሆን የሚችሉበት ሁኔታ ሲመቻች ውጤቱን ለማስታወቅ ጥቂት ቀናት ይወስዳል" ብሏል።

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:07


በ2017 የትምህርት ዘመን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸሁና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

አመልካቾች በየተመደባችሁበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው የሚሰጥ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ለፈተና ወደ ማዕከላት ስትሔዱ የተሰጣችሁን User Name and Password እንዲሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይጠበቃባችኋል።

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:04


#Grade_12

የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤትን አስመልክቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚተላለፉ የውሸት ዜናዎች ተማሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ግራ ሲጋቡ ሚዲያዎቻችን አይተዋል።

የኛ ሚዲያዎች ከፈተና ውጤቱ ጋር ተያይዞ ለብዙ አመታት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ፣ አላስፈላጊ ውዥንብርን እንድታስወግዱ እና መልካም ጊዜ እንዲያሳልፉ አሳስባለሁ።

ትክክለኛ መረጃ እንደደረሰን እናሳውቆታለን!

=========================

Our media has seen that students and their families are being confused by the spread of false news on various social media regarding the results of the grade 12 examination.

As our media has been doing for many years in connection with the examination results, I urge you to avoid unnecessary confusion and have a good time.

We will keep you informed as soon as we receive actual information!

Ministry Of Education Ethiopia

20 Jan, 23:03


የትምህርት ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
----------------------------------------
በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።

በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ ወረዳ ዋሬርሶ ማሌማ ቀበሌ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አሻራቸውን ያኖሩት የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አረንጓዴ አሻራችንን በማኖር አርአያነታችንንና ቁርጠኝነታችንን ለትውልድ በተግባር ማሳየት ይገባናል ብለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በጉጉት ስንጠብቀው ለነበረው ለዚህ ቀን ደርሰው አረንጓዴ አሻራቸውን በማስቀመጣቸው ደስ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሀገራችን ለዓለም አስተዋጽኦ ያደረገችበት መርሃ-ግብር መሆኑን ተናግረዋል።

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ችግኞቹን የተከሉት በተራቆተ ቦታ በመሆኑ ከአቻ መስሪያ ቤቶች ጋር በመተባበርም የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የግድ መሆኑን ተናግረዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች አገር ለትውልድ ለማውረስ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ኃላፊነታችንን ልንወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ አካባቢ በተካሄደው አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ ግብር የትምህርት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

2,096

subscribers

76

photos

26

videos