✞ማርያም አማላጅ ናት✞

@maryam_maryam2127


✝️•✞•ከገነት የመውጣታችን ምክኒያት ሔዋን እንደሆነች ሁሉ•✞•✝️

✝️•✞•ዳግመኛ ወደ ገነት የመግቢያ በራችን ድንግል ማርያም ናት•✞•✝️

✝️ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ለዘለዓለም ትኑር✝️
💫እኛስ...ማርያምን እኖዳታለን🥰

❥ማርያምን የሚወድ ሁሉ ይቀላቀል
☟-☟-☟-☟-☟
https://t.me/Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

23 Oct, 05:50


💠 ንሰሀ መግባት🙏🏻

ንስሀ ማለት ምን ማለት ነው

🔸ሊሰሩት የማይገባ ስራ ወይም ኃጢአት ከሰሩ በኋላ ምነው ባልሰራውት ምነው ባላደረኩት ብሎ ማዘን መቆጨት ነው።

🔹በሰራነው ኃጢአት  ተፀፅተን የምንመለስበት ነው።
📖ማቴ 12፥31

ንስሀ እንዴት እንገባለን

🔹ካህናት ዘንድ ቀርበን መሆን እንዳለበት መጽሃፍ ቅዱስ ይነግረናል።
📖ኢያ 7፥16፤
📖ማቴ 18፥13

🔸ኃጢአታችን በመናዘዝ ማለትም የሠሩትን ኃጢአት በመዘርዘር ልቡናን ታዛቢ አንደበተን ከሳሽ፣ ካህኑን ዳኛ አድርጎ ራስን መውቀስ ማለት ነው፡፡

👌በተጨማሪም በጸሎትና በመራራ ልቅሶ፣ በስግደትና በምጽዋት መሆን አለበት።
📖ማቴ 26፥75

💠በንስሃ ከተመለስን በኋላ

🔸ዳግመኛ መበደል አይኖርብንም።

🔹ንሰሃ የሚደገም ቢሆንም ከኃጢያት መራቅ አለብን።      📖ዩሐ 5፥14፤ 
📖ሮሜ 6፤14

🔸ሥጋ ወደሙን መቀበል ይገባናል።
📖ዩሐ 6፥56፤
📖1ኛ ቆሮ 11፥26

🔹ፍጹም ሰላምን እናገኛለን። 📖ዩሐ 14፥27

‼️አስተውሉ

🔔ማንኛውም ክርስቲያን ነፍስ ካወቀ በኋላ የንስሃ አባት መያዝ አለበት፡፡

🔔የንስሃ አባት የሚሆነው ካህን በአጥቢያው ቢሆን ይመረጣል፡፡

👌ምክንያቱም በየጊዜው እየተገናኙ ለሠሩት ኃጢአት ቀኖና ለመቀበል እንዲሁም መንፈሳዊ ምክርን ለማግኘት ሲባል ነው፡፡

ቀኖና ማለት ምን ማለት ነው

🔸 መስፈሪያ፣ መለኪያ ማለት ነው።

👌በአንድ ሰው ንሰሃ መግባት በሰማይ ሳይቀር ደስታ እንደሚሆን ተገልጿል።
📖ሉቃ 15፥7፤
📖 ማቴ 9፥13                                   
እንማማር ሼር-JOIN ያደርጉ
👉ስለ ሃይማኖታችን መማር ይፈልጋሉ? ??
ከፈለጉ JOIN ያደርጉ በማርያም🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

23 Oct, 03:07


🌷🌷🌷

እንኳን ለመነኰስ ለአባ ዘካርያስ ለዕረፍት በዓልና ለታላቁ አባት ለቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለመታሰቢያው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቀሲስ አብጥልማኮስና ከወንድሞቹ በሰማዕትነት ከዐረፋ፣ ከአውስኖ ከአውሲኪስ ከታኦድራስ፣ ከአብላስከ ወንድሞቹ ከናውላውስና ከአቤላ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


🙏🏻🤲🤲🤲🙏🏻❤️

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

20 Oct, 17:06


💚ሰላሜ ነሽ ድንግል🥰

ሰላሜ ነሽ ድንግል ዋስትናዬ
ውበቴ ነሽ ማርያም አለኝታዬ
የጭንቀቴ ደራሽ የህመሜ
ተፈታልኝ ባንቺ ፅኑ ህልሜ

ወገን ዘመድ ያልኩት ሁሉ ራቀኝ
ሃዘን ፅልመት ችግር ገዝፎ ታየኝ
ብራብ ምግቤ ሆነሽልኝ አይቻለው
ሰላም ባጣም ባንቺ እፅናናለው
   ፍቅርን ወልደሽ ሰላምን አገኘው
   ድንግል በምልጃሽ ተፈውሻለው
አዝ___
የሰላም ምንጭ የነፃነት አርማ
ክብር የምትሰጭ ሞገስ ታላቅ ግርማ
አንቺን ተስፋአድርጌ ወጥቻለው
ቀንና ለሊት ነይ እልሻለው ላንቺ ልንበርከክ አይዛል ጉልበቴ
     ውዳሴሽ ይብዛ ከአንደበቴ
አዝ___
ሱላማጢስ ስልሽ እረካለው
በህይወቴ ሰላም አግንቻለው
እንደ ሰው ልጅ ቀን እያየሽ የማትርቂኝ
የአማኑኤል እናት ዛሬም ባርኪኝ
      ተባርኬዋለው ድንግል በፍቅርሽ
      እሄሁ ቆሜያለው ልዘምርልሽ

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ቻናል ይጋብዙ

♡ለመቀላቀል
👉 
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

20 Oct, 06:10


"ትሑት ሰው ምንጊዜም ቢሆን የእርሱን ድካም ስለሚያውቅና የእግዚአብሔርን እርዳታ ስለሚሻ የእግዚአብሔር ኃይል በእርሱ ላይ ያደርጋል።

💪በክንዱ ሳይመካ በእግዚአብሔር እርዳታ🙏ስለተመካም ያሸንፋል።"

✍️....ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

19 Oct, 17:01


ስድቤን አርቀሽ

ስድቤን አርቀሽ ነውሬን ሸፈንሽው
እመ አምላክ በአንች መቸም አላፍርም
ስምሽን ጠርቸ እጽናናለሁ
ሀዘኔን በአንች እረሳለሁ


ነውር አለብኝ ብዙ ስድብ
አንጀት የሚልጥ ልብ የሚያቆስል
ስሜን ለውጠው ቢያንቋሽሹኝ
በሀዘን በለቅሶ ድንግል መጣሁኝ
እንደሀና ሁኜ በቤተ መቅደስ
በመረረ ሀዘን ነው እኔ እማለቅስ
ፍረጅልኝ እና ልመለስ ከቤቴ
ሀዘኔን በደስታ ለውጭው እናቴ
በግራም በቀኜ ጠላት ቢከበኝ
አብዝቸ እጮሀለሁ እናቴ ስሚኝ

አዝ ======

መከራው በዝቶ ግራ ገብቶኛል
ድምጽሽን ልስማ ያረጋጋኛል
የሰው ህይወቱ ብርቱ ሰልፍ ነው
ደስታ እና ሀዘን የማይለየው
በእጃችን ወድቋል ሲሉ ጠላቶቸ
አመለጥኳቸው ስምሽን ጠርቸ
ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል
በቆፈረው ጉድጓድ እራሱ ይገባል
እናቴ እመቤቴ ብየ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጭያለሽ

አዝ ======

በምርኮ ሳለሁ በሰው ሀገር
ግፍ ውለውብኝ ስኖር በእስር
ምልጃሽ ደርሶልኝ ተፈትቻለሁ
በታምራትሽ እኔ ድኛለሁ
ቃልሽን ሰምቶ ፅንሱ ሰገደ
ብላለች ኤልሳቤጥ ነውሬ ተወገደ
የጌታየ እናት እኔን አሰበችኝ
ታሪኬን ቀይራ ይሄው ባረከችኝ
የእመቤቴ ከሆንኩ ማን ይቃወመኛል
ወጀቡም ማዕበሉም ይታዘዝልኛል

አዝ ======

ወይን እኮ አልቋል የዶኪማስ ቤት
ድንግል አማልጅው ነይ የኛ እመቤት
ስምሽ ሲጠራ በየቦታው
ይሞላልናል የጎደለው
ግራ የገባው የቸገረው
ድንግልን ይጥራት እንድትረዳው
ሳዝን ስተክዝ የምታጽናና
እናት አለችኝ ርህርህተ ልቦና
እናቴ እመቤቴ ብየ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጭኛለሽ

👉ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ግሩፕ ይጋብዙ

♡ለመቀላቀል
👉 
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

19 Oct, 06:01


📘ፃድቁ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ📕🌹

📌💫•••ወር በገባ በ 9 የጻድቁ አባታችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ወርሐዊ መታሰቢያው ነው፡ አባታችን የእስትንፋሰ ክርስቶስ ተአምር ይህ ነው ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ከእለታት በአንድ ቀን አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በዋሻ ውስጥ እየጸለዬ
ሣለ ሰይጣን በመነኩሴ ተመስሎ ወደ እርሱ መጥቶ አንተ መነኩሴ ለአንተ
ሰላምታ ይገባሃል በዚህን ዘመን አንቸንተ የሚጋደል መነኩሴ ማነው ማን አለ
ብሎ በውዳሴ ከንቱ ለመግባት ቢሞክር ያን ጊዜ አባታችን እስትፋሰ ክርስቶስ
በመስቀል ምልክት አማተበበት ወዲያውኑ እንደ ጢስ ተኖ እንደ ጉም በኖ ጠፋ
አንድ አንድ ቀን እየመጣ ደቀ መዛሙርቱን ይፈትናቸው ነበር።
ከዚህ በኋላ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱን መነኩሴ ይዞት ያሣብደው ጀመር
ወደ መምህራችሁ አትውሰዱኝ እርሱ ያጠፋኛል ያሳድደኛልና አለ ደቀ
መዛሙርቱም ይህን በሰሙ ጊዜ አሰረው ወስደው ከአባታችን ዘንድ አደረሱት
ሰይጣኑም ለምን ታሳድደኛለህ በቤትና በእንጨት ሥር በተራራ ላይና
በየኮረብታው በእንስሳና በሰው ላይ እዳላድር አሳደድከኝ ይል ጀመር አባታችን
እስትንፋሰ ክርስቶስም ከፀሎት የትኛውን ትፈሩታላችሁ ብሎ ጠየቀው እርሱም
መልሶ የምንፈራው በንፅህና ሆኖ የሚያገለግል ካህንን ነው ከመዝሙረ ዳዊት
እግዚአብሔር በሰባ ዘመን ይነሣ ጠላቶቹም ከፊቱ ይበተኑ የሚለውንና ኪዳናትን
ወንጌልን ስመ ሥላሴን ይህን ከሰማን አፍረን ከሰው ላይ ፈርተን ተንቀጥቅጠን
ሸሽተን እንሄዳለን አለው።
ያን ጊዜ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም የጸለየበትን ውኃን ረጨው አንተ እርኩስ
መንፈስ ውጣ እነሆ አወገዝኩህ በሐዋርያት ሥልጣን የተለየህ ሁን አለው በዚያን
ጊዜ እንደተናገረው ወጥቶ በኖ ሄደ አነደገና ታላቅ ድንጋይ ተሸክሞ መጥቶ
አጥፍቻለሁና ይቅር በለኝ ማረኝ አለው አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስም ለተንኮል
አመጣጡን አውቆበት ሄደህ ከገደሉ ወደታች ቁልቁል ወረወረውና ወስዶ ከገደሉ
በታች ቁልቁል ዘቅዝቆ ሰቅሎ በጸሎቱ አሰረው ሰይጣንም በእዚሁ በገደል
መካከል ተሰቅዬ የምኖረው እስከመቼ ድረስ ነው ብሎ እስትንፋሰ ክርስቶስን
ጠየቀው አባታችን እስተንፋሰ ክርስቶስም አምዬሀለሁ አሰርኩህ በአብ በወልድ
በመንፈስ ቅዱስ ሥልጣን አወገዝኩህ ከገደሉ በላይ ልጆቸ ካሉበት አትውጣ
ከገደሉም አትውረድ ፈጣሪዬ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ በዚሁ ኑር ብሎ ገዘተው
ፈጣሪዬ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ በዚሁ ኑር ብሎ ገዘተው ያም ሳይጣን እስከ
ዛሬ ድረስ በገደል መካከል ተሰቅሎ ይኖራል እንደዚሁ የሚዋጉንን አጋንንትን
ፈፅሞ እስከ መጨረሻው በጸሎቱ ይሠራቸው ያጥፋቸው በእውነት ያለ ሐሰት
ይደረግልን።

(ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

18 Oct, 06:02


​​እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለብዙ ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለበዛልኝ ምሕረቱ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለምጓደድበት አባትነቱ፣ ስለምደፍርበት ርኅራኄው፣ ጠይቄ ስለምቀበልበት ታላቅ ስሙ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ከእርሱ ስለተቀበልሁት ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለሰጠኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስላልሰጠኝና ስለከለከለኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለገለጠልኝና መረዳቱን ስለሰጠኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስላልገለጠልኝ፣ ስለሰወረብኝና ስለከለከለኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
የእኔ ስለሆነውና ለእኔ ስላደረገልኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለጠበቀኝ፤ ስለሚጠብቀኝም እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ከእጁ ስለተቀበልሁት የዕለት እንጀራዬ፤ በአፌ ውስጥ ስላጣፈጠልኝ ምግቤ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለማይቋረጥብኝ መግቦቱ፣ ስለ ጥበቃው፣ ስለመሰወሩና ስለመከለሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ከመነገር በላይ ስለሆነው በጎነቱ፣ ከቃላት በላይ ስለሆነው ብዙ ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እኔን እንዲሁ ስለመውደዱና ስለመቀበሉ፣ ለሞት ስላደረሰው ፍቅሩ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
በየዕለቱ ስለሚጨምርልኝ ዕልፍ ዕድሎች፣ በየቀኑ ስለምተነፍሰው ዐየርና በየነጋው ስለምኖረው ሕይወት እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እርሱን ስለማመሰግንባቸው ብዙ ምክንያቶች፤ በየደቂቃውና በየሰከንዱ ስለምደገፍበት ብርታቱና ኃይሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
አቅም ስላገኘሁበትና ስለምበረታበት ብርቱ ክንዱ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስላሳለፈኝ፣ ስላሻገረኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለትናንቱ ነገር እግዚአብሔር ይመስገን! ስለዛሬውም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን! ስለነገውም ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለብዙ ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!
.
ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እግዚአብሔር ይመስገን!
.
እግዚአብሔር ይመስገን!
💚💛❤️
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

17 Oct, 06:02


​​ የአብረሀሙ ስላሴ

በጎ ቢሆን ልቡ መልካም ቢሆን ግብሩ
ስላሴን ጠራቸው ትህትና ፍቅሩ
ሰይጣን በክፋቱ ሊጎዳው አስቦ
ሰዎችን ቢያጠምድ በተንኮሉ ከቦ
እምነት ቅንነቱ ሃይማኖቱን አይተው
ቤቱን ባረኩለት አንድም ሶስትም ሆነው

ወዳጅ መቼስ ሁል ጊዜ የአብረሀሙ ስላሴ ሲባል ትሰማለህ። ክርስቲያን ከሆንክ አንተም ከሚሉት መሀከል መሆንህ ሀቅ ነው። ነገር ግን ወዳጄ የአብረሀሙ ስላሴ የተባሉት ስላሴ የአብረሀም ብቻ ሆነው አይደለም። ይልቅ እርሱ መልካም ቅን የዋህ ታዛዥና ቃሉን አክባሪ በመሆኑና በመታዘዝ የስላሴን ተግባር በመፈጸሙ ነው።

አየህ ስላሴ ሁሉን የፈጠሩ፣ ሁሉን የሚመግቡ፣ ሁሉን የሚያለብሱ፣ ሁሉን የሚጠብቁ፣ ሁሉን የሚያኖሩና ሁሉን የሚያውቁ ናቸው። እናም ህጋቸውን የጠበቀ፣ ትዕዛዛቸውን የፈጸመና ቃላቸውን ያከበረ ሁሉ ቤቱ፣ ኑሮው፣ ስራው፣ ትዳሩ፣ና ልጆቹ ሁሉ ይባረኩለታል።

ታድያ ወዳጄ እኔና አንተ ግን ሀሳብ ምኞት ተግባራችን ሁሉ ከስላሴ ተቃራኒ ነው። እንኳን እንግዳ ልንቀበልና ሰዎችን ልንወድ ይቅርና በአንድ ማህጸን ከወጣንባቸው ቤተሰቦቻችን ጋር ኑሯችን ቂም በቀል ጥላቻ ሀሜት ቅናት ምቀኝነት ስድብ እልህ ከስ ቁጣ ንጽጽር ነው።

ሀሳባችን የአለም፣ ጠባያችን የዲያቢሎስ፣ ምግባራችን የእንሰሳት ነው። ስለዚህ ጸሎት የማያውቅ አእምሮ፣ ስግደት የማያውቅ ሰውነት፣ አስራት የማያውቀው ገንዘብ ይዘን ስላሴን እንጠራለን። ያው መጥራቱን አይከለክሉንም። ፍሬአቸውን ግን ፈጽሞ አናገኘውም።

አዎ ስላሴ በዛሬ ስንክሳራቸው "እንሰሳ አእዋፍ አራዊት ዛፍ ቅጠል ተራራ ወንዙ ሸለቆው ፍጥረት ሁሉ ሲያመሰግኑኝ። በራሳችን አምሳል የፈጠርነው፣ ክብር ሞገስ ሀይል ስልጣንን የሰጠነው የሰው ልጅ ግን አያመሰግነንም" ይላሉ። አዎ ወዳጄ በእውነት እግዚአብሔርን የሚያመሰግን ሰው ማን ነው።

🌺 እናቴ ማርያም ውድድድ የምታደርገኝ ትንሹ ሔኖክ ነኝ🌹

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

16 Oct, 06:01


ቅድስት አርሴማ ሰማዕት

እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ወርሃዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!

✝️ ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ጣኦታ አምላኪ ነገሥታት እና አሕዛብ ባየሉበት ዘመን ተወልዳ በክርስትና ያበበች ከቅዱሳን አንስት አንዷ ናት

✝️ ከቤተሰቦቿ እና ከቅዱሳት መጻሕፍት የተማረችውን እውነት በተግባር የተረጎመች እናት ናት

✝️ በውበቷ ተማርከው ዓለማዊ ቁስን እንደ መደለያ ያቀረቡላት ነገሥታትን ንቃ ለሰማያዊው መንግሥት ሕይወቷን መስዋዕት ያደረገች ቅድስት እናት አርሴማ

✝️ ቅድስት አርሴማ እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ በጾም፣ በጸሎትና ጌታዋን በማምለክ ጸንታለች

✝️ በገዳማዊ ሕይወት በድንግልና የኖረችው ቅድስት አርሴማ በብዙ መከራና ስቃይ ብትፈተንም በእምነቷ ከመጽናት ምንም አላገዳትም

✝️ በመጨረሻም በመስከረም 29 ቀን እምነቷን ጠብቃ ሰማዕትነትን ተቀበለች

የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ምልጃና በረከት ይደርብን። በጸሎቷ ታስበን🙏🏻🙏🏻🙏🏻🥰

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

15 Oct, 03:49


​​እንኳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን!🙏❤️

አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ (ግብጽ ) ነው። አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌያስ ይባላሉ። ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል።

አንድ ቀን አቅለያስ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከስዕለ ስላሴ ስር ወድቃ ስትማጸን "" ንስኢ ወልደ ዘይትሌአል ቅርኑ አምኑኅ ሰማይ ... ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበልጥ ልጅ እንኪ ተቀበዪ " የሚል ድምጽ ሰማች። በዚህም መሰረት አባታችን መጋቢት 29 ቀን ተጸንሰው ታህሳስ 29 ቀን ተወለዱ።

አይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ብለው ተነስተው "" ስብሐት ለአብ , ስብሐት ለወልድ , ስብሐት ለመንፈስቅዱስ ዘአውጻእከኒ እምጽልመት ውስተ ብርሐን >> ብለው በማመስገናቸውና ሀላም ምድራዊ መብል እና መጠጥ ሳይመገቡ : ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው በመኖራቸው መልአክትን ይመስላሉ

ሶስት አመት ሲሆናቸው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችንና በገነት ካሉ ቅዱሳን ዘንድ አስባርኮ ገዳማውያን ካሉበት ምኔት ወስዶ ከበሩ አኖራቸው :: አበመኔቱም አባ ዘመድብርሐን ምልክት ተነግሮት ቢሄድ ፍሱሐ ገጽ ሆነ አግኝተዋቸዋል። አበመኔቱም አሳድጎ አስተምሮ ከመአረገ ምንኩስና አድርሰዋቸዋል።

ከዚህ ቡሐላ ሐብተ ፈውስ ተሰጥቷቸውል። በአንድ ቀን እልፍ እውራንን እና እልፍ አንካሳ ፈውሰዋል። በዋላ ግን ኤጲስ ቆጶሳትና ካህናቱ ዝናቸውን ሰምተው እየመጡ ግብር የሚያስፈቱአቸው ቢሆን ቅዱስ ገብርኤል ነጥቆ ከጌታ ፊት አቀረባቸው።

በገድለህ : በትሩፋትህ : ከሞት ነፍስ ክርደት ገሀነም የሚድኑ ብዙ አሉና ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ግባ። ኑሮህም ከስልሳ አናብስትና ከስልሳ አናብርት ጋር ይሁን አለው። ጌታዬ ምን ተመግበው ይኖራሉ አሉት ? "ዘኬድከ ጸበለ - እግረከ ይልህሱ ወበ ውእቱ ይጽግቡ ... የረገጥከውን ትቢያ ልሰው ያ ምግብ ሆኗቸው ይኖራሉ። ብሏቸው ውሳጤ ገዳም ገብተው : ከአናብስትና ከአናብርት ጋር ይኖሩ ጀመሩ። ዳንኤል ከአናብስት ጉድጉዋድ በተጣለ ጊዜ አናብስቱ እንደ ድመት ከእግሩ በታች ሆነው እንደተገኙ : አባታችን የረገጡትን ትቢያ እየላሱ እየታዘዙዋቸው ይኖሩ ነበር።

በዚህ መልኩ 30 አመት ከቆዩ ቡሐላ ጌታ በአንድነት በሶስትነት ተገልጾ ምን ላደርግልህ ትሻለህ ? አላቸው። መጀመሪያ ላሉበት መጸለይ ይገባልና የምድር ገቦታን ሰዎች ማርልኝ አሉት። 3000 ሐጥአንን ከሲኦል አውጥቶ ገነት አግብቶላቸዋል። ከዚህ ቡሐላ ሁር ምድረ ኢትዮጵያ ወበህኒ አልውከ ነፍሳት ወታወጽኦሙ .... ወደ ኢትዮጵያ ሂድ አላቸው። ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ ነፍስ ጭኖ ምድረ ከብድ አድርሷቸዋል።

ዳግመኛም ወደ ዝቁዋላ (ደብረቅዱስ ) ወስዷቸው ከዚያ ሆነው በንጹሀ ልቦና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሐጢያት ከባህሩ ውስጥ ራሳቸውን ዘቅዝቀው ለ 100 አመት ይጽልዩ ነበር። 40 ቀን ሲሆናቸው መልአኩ መጥቶ ዘገብረ ተዝካርከ ወዘጽውአ ስምከ እምህር ለከ ብሎሀል አላቸው። እሳቸው ግን መላ ኢትዮጵያን ካልማረልኝ ከባህሩ አልወጣም ብለው 100 አመት በባህሩ ውስጥ በጭንቅላታቸው ተዘቅዝቀው ሲጸልዩ ኖረዋል። ከ 100 አመት ቡሐላ ጌታ ተንስእ ወጽእ መሀርኩ ለከ ኩሎ ኢትዮጵያ ... ምሬልሀለው ውጣ ብሏቸው ወጥተዋል።

ከዚህ ቡሐላ ምድረ ከብድ ወርደው ከምድር በላይ ከሰማይ በታች ሆነው 7አመት እንደ ትኩል አምድ ሆነው አይናቸውን ሳይከድኑ 7 አመት ሙሉ አይናቸውን ሳይከድኑ ቆመው ጸልየዋል። ሰይጣን ግን ለምቀኝነት አያርፍምና ቁራ መስሎ መጥቶ አይናቸውን አንቁሮ አሳወራቸው። 2 ሱባኤ ሲፈጽሙ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው እፍፍ ብለው አድነዋቸዋል።

ከዚያ ተነስተው ወደ ዝቁዋላ ሲሄዱ ስላሴን በአምሳሌ አረጋውያን ከጥላው ስር አርፈው አገኙዋቸው። በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጽነንሀል አዝለክ አንድ አንድ ምህራፍ ሸኘን አሉዋቸው። አዝለው ከሸኙዋቸው ቡሐላ በአንድነት በሶስትነት ሆኖ ታያቸው። ድንግጠው ወደቁ : እግዚአብሔር ግን አንስቷቸው ሂድ ዝቁዋላ ሄደህ ጠላቶችህን ተበቀላቸው አላቸው :: በዛበነ መብረቅ ደርሰው 7 ቱን ሊቃነ መላእክት አጋዥ አድርገው እልፍ አእላፍ አጋንንትን አጭደዋል።

ጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍታቸው መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ ስለዚህም ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር የመጋቢት 27 ስቅለት ደግሞ ጥቅምት 27 ቀን እንዲከበር ተደረገ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ይህ ስርዓት ሆነ።

ምንጭ - ገድለ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ተአምር 14 
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

14 Oct, 20:17


ኧረ እንዴት ነው አቡኤ

ኧረ እንዴት ነው አቡዬ ኧረ እንዴት ነው ጻድቁ

>>  ተራራን በግርማ የሚሰነጥቁ

>>  የሌጌዎን ጭፍሮች በስምህ አለቁ

>>  በፆም በጸሎትህ በመብረቅ ወደቁ

>>  ገድሉ አንፀባራቂ ተአምሩ የገነነ

>>  በረከት ያገኛል ኪዳኑን ያመነ

>> እናቱ አቅሌሲያ አባቱ ስምዖን

>>  ምግቡ ምስጋና ነው ተሰጥቶታል ኪዳን

>>  ስእለትን ይሰማል ፀበሉ ፈዋሽ ነው

>>  የሳሪሱ አቦ ቅዱስ ለጠሩት አባት ነው

>>  አቡየን ጥሩልኝ እኚያን ባለጭራ

>>  ያወጡ የለም ወይ ከሲዖል መከራ

>>  ገብረ  መንፈስ ቅዱስ እንደኛ  ሰው ናቸው

>>  መስቀል ከሰማይ ላይ የወረደላቸው

>>  ፀበል ከጪንጫ ላ ይ የፈለቀላቸው

>>  አንበሳና ነብር የሰገደላቸው

>>  ለዝቋላው አቦ እልል በሉላቸው

>>  ለዚጊትው አቦ እልል በሉላቸው

>>  ለፈረንሳይ አቦ እልል በሉላቸው

>>  ለሳሪሱ አቦ እልል በሉላቸው

ለመቀላቀል
👇👇
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127
    
     🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

14 Oct, 04:38


🕊

[  † እንኩዋን ለቅዱሳን ነገሥታት "አብርሃ ወአጽብሃ" እና ለቅዱስ "ሐናንያ ሐዋርያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]


†  🕊 ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ  🕊  †

እነዚህ ነገሥታት ሞገሶቻችን: ብርሃኖቻችን ናቸውና ደስ እያለን እንወዳቸዋለን: እናከብራቸዋለን:: ሥላሴ ቢመርጧቸው ዛሬ ላለንበት ሕይወት መሠረቱን ጥለው አልፈዋልና::

፪ቱ ቅዱሳን ነግሥታት መንትያዎች ሲሆኑ ወላጆቻቸው ንጉሥ ታዜር / አይዛና / ሠይፈ አርዕድ እና ንግሥት አሕየዋ / ሶፍያ ይባላል:: ንጉሡና ባለቤቱ ልጅ ቢያጡ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ:: ፈጣሪም በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ፪ ዕንቁዎችን አስረከባቸው::

ንግስት አሕየዋ [ሶፍያም] መጋቢት ፳፱ ቀን በ፫፻፲፩ ዓ/ም ጸንሳ: ታሕሳስ ፳፱ ቀን በ፫፻፲፪ ዓ/ም ፪ቱን ቅዱሳን ወልዳቸዋለች:: "አምላክ ሽሙጥን አራቀልኝ" ስትልም "አዝጉዋጉ" ብላቸዋለች:: እነዚህ ፪ ፍሬዎች በልጅነታቸው ከወቅቱ ሊቀ ካህናት እንበረም ኦሪቱን ጠንቅቀው ተምረዋል::

ከእግዚአብሔር የተሰጡ ናቸውና በ፲፪ ዓመታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ገብተዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን አባታቸው ታዜር በማረፉ ሕዝቡ ፪ቱን ቅዱሳን "ንገሡልን" አሏቸው:: እነርሱም "እኛ የፈጣሪ አገልጋዮች ነንና አንችልም" በማለታቸው ለተወሰነ ጊዜ እናታቸው አስተዳደረች::

ቆይቶ ግን ቅዱስ ሚካኤል ለሊቀ ካህናቱ እንበረም "የፈጣሪ ፈቃዱ ስለ ሆነ አትዘኑ:: ፪ታችሁም በአንድ ዙፋን ላይ ንገሡ: ታላቅ ጸጋ ለሃገሪቱ ይሆናል በላቸው" አለው::

ሊቀ ካህናቱም የታዘዘውን ተናግሮ: በ፲፱ ዓመታቸው: ፪ቱንም በአንድ ዙፋን ላይ "ነገሥተ ኢትዮዽያ" ሲል አስቀምጦ ቀባቸው:: ስማቸውን "ኢዛና" እና "ሳይዛና" አላቸው:: ቅዱሳኑ እንደ ነገሡ ቀዳሚ ሥራቸው የቀናችውን ሃይማኖት መፈለግ ሆነ::

በወቅቱ ፍሬምናጦስ [የሁዋላው አቡነ ሰላማ] በቤተ መንግስቱ ውስጥ የቅርብ አማካሪ ነበርና ጠርተው ተጨዋወቱት:: "አንተ ወንድማችን! ክርስቶስ ይወርዳል: ይወለዳል ተብሎ የተቆጠረው ሱባኤ እኮ አልፏል:: ምነው ቀረሳ? በርግጥ ምሥጢሩ ንገረን" አሉት::

እርሱም አትቶ: አመሥጥሮ: ከ፫፻ ዓመታት በፊት አምላክ ሰው መሆኑንና ዓለምን ማዳኑን አስተማራቸው:: "አጥምቀን?" ቢሉት "አልችልም" አላቸው:: እነርሱም ከብዙ ስጦታ ጋር ወደ ግብጽ ላኩት::

ቅዱስ አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "አቡነ ሰላማ" ብሎ ከብዙ መጻሕፍት ጋር ላከው:: በመጀመሪያ ኢዛናና ሳይዛና ተጠመቁ:: ስማቸውም "አብርሃ ወአጽብሃ" ተባለ:: ቀጥሎም ሠራዊቱና ሕዝቡ ተጠመቀ::

ሃገራችንም በእነዚህ ቅዱሳን አማካኝነት ከጨለማ ወደ ብርሃን መጣች:: የክርስትና ደሴት ሆነች:: ሃገረ እግዚአብሔርነቷንም አጸናች:: ቅዱሳኑ ከዚህ በሁዋላ በሞገስ ክርስትናን ያስፋፉ ዘንድ ደከሙ:: ከ፻፶፬ በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያንጹ አብዛኞቹ ፍልፍል ነበሩ::

በተለይ ግን በአክሱም ከተማ ላይ ያነጿትና ፲፪ ቤተ መቅደሶች የነበሯት የጽዮን ቤተ ክርስቲያን ልናያት ትናፍቀናለች:: ጌጧ: ብርሃኗ ውል ውል ይልብናል:: ይህቺው ቤተ ክርስቲያን በ፲ ኛው ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት በእሳት አውድማታለችና:: መሠረቱ ግን ዛሬም አለ::

ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ ግን ክርስትናን ለማስፋፋትና መንግስትን ለማጽናት ሲሉ ከአክሱም በተጨማሪ በሽዋም ዙፋንን ዘረጉ:: ለብዙ ዓመታትም አምላክ በፈቀደው መንገድ እስከ የመን ድረስ ገዙ:: ክርስትናንም አስፋፉ::

ቅዱስ አብርሃ በተወለደ በ፶፪ ዓመቱ: በ፫፻፷፬ ዓ/ም ጥቅምት ፬ ቀን ሲያርፍ ወንድሙ ለ፲፭ ዓመታት ብቻውን አስተዳድሯል:: በ፫፻፸፱ ዓ/ም ደግሞ በዚሁ በጥቅምት ፬ ቀን ቅዱስ አጽብሃም በተወለደ በ፷፯ ዓመቱ በክብር ዐርፏል::

ከሁለቱም መቃብር ላይ ለ፴ ቀናት የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታይቷል:: ጌታችንም በማይታበል ቃሉ "ስማችሁን የጠራውን: መታሰቢያችሁን ያደረገውንም እምርላቹሃለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::


†  🕊  ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ  🕊  †

ሐናንያ ቁጥሩ ከ፸፪ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ: በሕገ ኦሪት አድጐ: ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ፸፪ቱ አርድእት ደመረው::

ለ፫ ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ: ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: [ሉቃ.፲፥፲፯] ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ፶ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ፰ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል [የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ] ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::

ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነው የነገረው:: ከ፫ ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል:: ሳውል [ዻውሎስ] ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር::

፪ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው: ፈወሰው: አጠመቀው: በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: [ሐዋ.፱፥፩-፲፱]

ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::

አምላከ አብርሃ ወአጽብሃ "ድሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ" የሚል ዳኛ: ሃይማኖቱ የቀና መሪንም ያምጣልን:: የቅዱሳኑን ክብር በእኛ ላይ ያድርግልን::

🕊

[  † ጥቅምት ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሃ
፪. ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ [ከ፸፪ቱ አርድእት]
፫. ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ባኮስ ሰማዕት
፭. ቅዱሳን ባባ እና ማማ
፮. ቅዱስ ዮሐንስ ሕጽው

[  † ወርኀዊ በዓላት  ]

፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት]

" እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ: ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር: ልመናና ጸሎት: ምልጃም: ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ: ስለ ነገሥታትና መኩዋንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ:: ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው:: " [ጢሞ.፪፥፩-፬]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

11 Oct, 04:44


+ ማርያም +🤗

ብዙ ሰው "ሔዋን ለመውደቃችን ምክንያት ናት" ሲባል ይስማማል:: ድንግል ማርያም ግን ለመዳናችን ምክንያት ሆነች የሚለውን ግን አንዳንዶች ለመቀበል ይቸገራሉ:: ሔዋን ለመውደቃችን ካደረገችው ይልቅ ድንግል ማርያም ለመነሣታችን ያደረገችው ይበልጣል!

የድኅነታችን መጀመሪያ የሆነችውን ይህችን ድንግል ክብርዋን በሕሊናችን እንሳለው:: እሳታዊ መልአክ ቆሞ የዘመረላት ድንግል፤ አባትዋ ዳዊት ከሩቅ ሆኖ እያያት "ልጄ ሆይ ስሚ እዪም ጆሮሽን እዘንብዪ" እያለ የገብርኤልን ቃል እንድትሰማና ከሲኦል እንድታወጣው የሚማጸናትን ድንግል፤ ወንድምዋ ሰሎሞን "እኅቴ ሙሽራ ሆይ ሁለንተናሽ ውብ ነው ነውርም የለብሽም" እያለ የቀረበላትን 'የተባረክሽ ነሽ' የሚል ምስጋና እንድትቀበል የሚዘምርላትን፤ በእጆችዋ ሐርና ወርቅን፤ በማኅጸንዋ ሰውና አምላክን፤ በመውለድዋ ሰውና መላእክትን አስማምታ የፈተለችና ያዋሐደችዋን ይህች ድንግል እስቲ ለአፍታ እናስባት:: የባቢሎንን ሰባት እጥፍ የነደደ እሳት ያቀዘቀዘው ገብርኤል በፊትዋ በትሕትና አደግድጎ የቆመላትና ዘካርያስን ዲዳ ትሆናለህ ባለበት አንደበቱ "አንቺ የተባረክሽ ነሽ" እያለ የሚማጸናትን የዐሥራ አምስት ዓመት ብላቴና እስቲ እናስባት! ዓላማ ይዞ እንደተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ይህች ማናት?

ሽማግሌ አባትዋን ቅጠል ከለበሰበት ዛፍ አውጥታ ልጅዋን ሸማ አድርጋ ያለበሰች፤ እናትዋን ሔዋንንም የሚጎዳ ማሠሪያዋን ፈትታ ቁስልዋን ያከመች የሔዋን መድኃኒት ይህች ድንግል ማን ናት? የእርስዋን ክብር በኃጢአተኛ ብዕር እንደምን እጽፈዋለሁ?
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ያለውን ብዬ ብዘጋው ይሻለኛል"የድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ፀሐይን ከነብርሃንዋና ከነሙቀትዋ መሣል ይቀልላል።"

"ክብር ለ ድንግል ማርያም ይሁን "

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

10 Oct, 15:58


ድንግል ማርያም ሆይ 🕯

👉 ልጅሽን ቅዱሳን መላእክት ሊቀርቡት ይፈሩታል፤ አንቺ ግን ጸንሰሽ ወለድሽው።

👉 ልጅሽን  ፍጥረታት ሁሉ "ፈጣሪያችን" ይሉታል፤ አንቺ ግን ልጄ ትይዋለሽ።

👉 መልክና ባህሪሽ ልጅሽ ፈጣሪን  ይመስላል።

👉 የተባረኩት ሴቶች ቅዱሳንን ይወልዳሉ፤ አንቺ ግን ፈጣሪሽን ወለድሽ።

👉 ምስጢሩ ከሰው አእምሮ በላይ ስለሆነ እጹብ ድንቅ ተብሎ ማለፍ ነው እንጂ።🙏

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሀገራችን ሰላምን ለህዝባችን ፍቅርን ለታመሙት ፈውስን ለተራቡት ምግብን ታድልልን አሜን!🤲😥💚💛❤️🙏✝️

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

09 Oct, 04:03


መስከረም ፳፱

በዚህች ዕለት ቅድስት አርሴማ እና አብረዋት የነበሩ ደናግሎች ሰማዕት ሆኑ።

ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ የቅድስት አርሴማን ሥዕሏንም ሥለው ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ ።

ደናግልሉም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው ወደ አርማንያ በሥውር ሸሹ። ከእርሷ ጋርም ሰባ አምስት ወንዶችና ሠላሳ ዘጠኝ ሴቶች ነበሩ።

ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን ወታደር ወደ እኔ አምጣት ብሎ አዘዘው።እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወሰዷት።

ድርጣድስም እናቷ አጋታን እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት ። ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።

ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት ። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር
በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ። በዚህች ዕለትም ሰማዕትነትን ተቀበሉ።

የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን አሜን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

08 Oct, 06:09


💀 የሰይጣን ለቅሶ 💀

አንድ ለመመንኮስ የፈለገ ወጣኒ ወደ አበመኔቱ ይሄድና እንዲያመነኩሰው ይጠይቀዋል አበመኔቱም እንዳመነኩስህ ከፈለክ ሂድና በእስክንድርያ አደባባዮች እኔ ዘማዊ ነኝ እያልክ ለመንገደኛው ሁሉ ንገር ይለዋል ይህም ወጣት እንደታዘዘው ሲያደርግ ውሎ በነጋታው ጠዋት ቤተክርስቲያን ሲገባ በዚያ የተሰበሰቡት ሁሉ "አንተ ዘማዊ እያሉ አፌዙበት
አበመኔቱም "አዎ አንተ ሀጢያተኛ ነህ" ብሎ አስወጣው ወጣቱም ምንም ሳይናገር ወጣ ይህ ወጣት ከወጣ በኋላ ግን አበመኔቱ ለተሰበሰቡት ምዕመናን እንዲህ አላቸው

👉"በትክክል ለምንኩስና የታጨች ነፍስ ይህቺ ናት እናንተ ስትስቁበት አጋንንት ግን ሲያለቅሱ አያቸው ነበር፣ እኛ ሀጢአቱን ስንዘረዝር መላእክት ግን ስሙን በብርሃን መዝገብ ሲፅፉት ተመለከትኩ አላቸው፣
ያንንም ወጣት ጠርቶ አመነኮሰው

👉ብዙ ሰዎችን ከቤተክርስቲያን ፣ ከመንፈሳዊ አገልግሎት፣ ከበጎ ስራ ከሚያርቁት ነገሮች ዋነኞቹ ትችት እና ሀሜት ነው ብንል ማጋነን አይሆንም በተለይ ደግሞ ለመንፈሳዊ ተግባር አዲስ የሆኑትን እስከመጨረሻው ላያስመልስ የሚችል ተግባር ነው

👉ወዳጄ የቱንም ያህል ብትሰደብ ፤ የቱንም ያህል ብትናቅ፤ የቱንም ያህል ሰዎች ተሰብስበው ስላንተ ቢያወሩ ፤ በተሰደብከው ልክ ክብርህም ይጨምራልና ከደጁ እንዳትርቅ

👉አንቺን ብሎ ጸሎተኛ ፤ አንቺን ብሎ ጾመኛ፤ አንቺን ብሎ ዘማሪ ፤አንቺን ብሎ ቤተክርስቲያን ተሳላሚ ፤ አንቺን ብሎ ቆራቢ ፤ .......ብዙ ብዙ ነገር እያሉ ሊያሸማቅቁሽ ቢሞክሩ ከመንገድሽ እንዳትወጪ ሰዎች በሳቁብሽ ልክ ፈታኝሽ ዲያቢሎስ ያለቅሳልና

👉 እናንተም ፈራጆች ሆይ ሰው ላይ ስትፈርዱ ሰይጣን በናንተ ይስቃል፣ የሰውን ሀጢአት ስትመዘግቡ ሰይጣን በደስታ የናንተን ሀጢአት ይፅፈዋል
ስለዚህ ለወዳጆችህ እየፀለይክ ሰይጣንን አስለቅሰው
በቅዱስ መስቀሉ ጠላታችን ዲያብሎስን ከእግራችን በታች ይጣልልን አሜን 🙏

ለተዋህዶ ልጆች ሼር👉
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127
@Maryam_Maryam2127

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

07 Oct, 06:02



መድሃኒአለም የአለም ሁሉ መድሃኒት
ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ለኛ ሲል ህይወቱን የሰጠ🙏🥹

ብንታመም መድኃኒታችን
ብንደክም ብርታችን
ብንፈተን ጽናታችን
ብንወድቅ ጉልበታችን
ቢጨልምን መብራታችን
ብንሞት ህይወታችን
ብንቸገር እረዳቴታችን

የድንግል ማርያም ልጅ ቸሩ መድኃኔዓለም አንተ ነህ አባቴ!

ቸሩ መድሀኒአለም በያለቹበት ይጠብቃችሁ
ወጥቶ ከመቅረት ከድንገተኛ አደጋ ይጠብቃችሁ አሜን🙏

✞ማርያም አማላጅ ናት✞

06 Oct, 06:02


ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ጽንሰቱ❤️

መስከረም ሃያ ስድስት በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ወደ በራክዩ ልጅ ዘካርያስ ልኮት መጥምቁ ዮሐንስ ከእርሱ ስለ መወለዱ አበሠረው።

ስሙ የተመሰገነ እግዚአብሔር ልጅን ይሰጠው ዘንድ አስቀድሞ ሁል ጊዜ በመጸለይ ወደ እግዚአብሔር ይማልድ ነበር። ልጅ ያልወለደውን እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ ምድርን ምሉዋት ያለውን በረከት ያጣ ነው በማለት እስራኤል ይገዳደሩት ነበርና

ልመናውንም ሰማ በቤተ መቅደስም ቁሞ ዕጣንን ሲያሳርግ መልአኩን ላከለት በከበረ ወንጌልም እንደተባለ መንገዱን ይጠርግ ዘንድ በንጉሥ ክርስቶስ ፊት እንደሚሔድ የተነገረለት ታላቅ ነቢይ ዮሐንስ ከእርሱ መወለዱን አበሠረው።

ዘካርያስም የሰውነቱን መድከም የመውለጃውም ዘመን እንዳለፈና ፈጽሞ እንዳረጅ የሚስቱም እንዲሁ ዘመኗ እንዳለፈና ፈጽማ እንዳረጀች መካንም እንደሆነች ያውቃልና ስለዚህ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል እኔ ያረጀሁ ሽማግሌ ነኝ ሚስቴም እንዲሁ ዘመኗ አልፎ መካን ሁናለች ብሎ የእግዚአብሔርን መልአክ ተከራከረው።

መልአኩም እኔ ይህን ልነግርህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወዳንተ ተልኬ ነበር ልትጠራጠር ባልተገባህም ነበር አሁንም ይህ በጊዜው እስቲፈጸም ዲዳ ሁነህ መናገር ይሳንሃል ብሎ ገሠጸው። ዘካርያስም የወልደ እግዚአብሔርን መንገድ የሚጠርግ ዮሐንስ እስከሚወለድበት ጊዜ ድረስ ዲዳ ሆነ

በሚገረዝበትም ቀን የሕፃኑን አባት ዘካርያስን የሕፃኑን ስም ምን ብለው እንደሚሰይሙት ጠየቁት እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ በዚያም ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው። ስለ ልጁ ዮሐንስም እርሱ የልዑል ነቢይ እንዲባል መንገዱንም ይጠርግ ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።

አምላከ ቅዱሳን ከመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከት ያሳትፈን🙏🏻❤️

9,418

subscribers

442

photos

52

videos