Falcon Academy school

@falconacademyschool


Falcon Academy (KG-Grade 12) Official Channel

Falcon Academy school

16 Aug, 09:26


ለፋልከን አካዳሚ ወላጆች
ከዚህ ቀደም ባሳወቅነው መሰረት የተማሪዎች የመማርያ መጽሀፍ ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች ክዚ ቀደም በወጣው ማሰታወቂያ እሰከ 06/12/2016ዓ.ም እንድትከፍሉና መጽሃፉ በመጣ ጊዜ እድትወስዱ ማሳሰባችን ይታወሳል ሆኖም አሁንም ይህን ያላደረጋችሁ ወላጆች ስላላችሁ እስከ ሰኞ 13/12/2016 ክፍያችሁን እንድትፈጽሙ ት/ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል

Falcon Academy school

09 Aug, 09:25


አስቸካይ መልዕክት ለወላጆች
ለ2017ዓ.ም የትም/ት ዘመን የተማሪ መፅሐፍት እንዲገዙ ዋጋዉን ማሳወቀችን ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ከሐምሌ 1/2016ዓ.ም ጀምሮ ክፍያ ስንቀበል የቆየን ሲሆን እስከአሁን ድረስ በተለያ ምክንያት ያልከፈላችሁ ለመጨረሻ ጊዜ አስከ ሰኞ 06/12/16 ድረስ ያራዘምን መሆኑን እያሳወቅን፡፡ እስከተባለዉ ቀን ድረስ ክፍያዉን የትም/ቤቱ ሒሳብ ክፍል (ቢሮ ቁጥር 10) በአካል በመገኘት እንድትከፍሉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-የመፅሐፍ ዕጥረት ስላለ በመዘግየትዎ መክንያት ለሚፈጠረዉ መስተጓጎል ትም/ቤቱ ሐላፊነት አይወስድም

ትም/ቤቱ

Falcon Academy school

02 Aug, 16:32


አስቸኳይ
ውጤታችሁ ዝቅተኛ በመሆኑ ምክንያት ክረምት ተምራችሁ ምዝገባ እንድትፈፅሙ የተነገራችሁ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ አርብ በ26/11/16 እና ቅዳሜ በ27/11/16  ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ እያሳወቅን ከሰኞ ጀምሮ ግን በእናንተ ቦታ አዲስ ተማሪ እንደምንቀበል እያሳወቅን እና ለሚፈጠረው ችግር ሐላፊነት የማንወሰድ መሆኑን እንገልፃለን።
                                       ትም/ቤቱ

Falcon Academy school

06 Jul, 19:25


ለፋልከን አካዳሚ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች
የ 2016ዓም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች የሰርተፍኬት መስጫ ቀን የፊታችን ሰኞ ሐምሌ01/11/2016 ስለሆነ ሁሉም ተማሪበዕለቱ  ከ2:30 ጀምሮ -6:00 በትመህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ከስም ጠሪ መምህራኖቻችሁ አንድትቀበሉ እናሳስባለን ።
ማሳሰቢያ ፦ ከላይ ከተጠቀሰው ቀን ዉጪ ማንኛዉንም ተማሪ የማናስተናግድ ስለሆነ በተባለው ቀንና ሰዓት ሁሉም ተማሪ መገኘት ይኖርበታል።
                                    ትምህርት ቤቱ ።

Falcon Academy school

06 Jun, 13:19


ለወላጆች
ነገ ዓርብ በ30/09/16ዓ.ም ከ9ኛ-12ኛ ክፍል የስፖርት ቀን የሚከበር ሲሆን ከ9ኛ-11ኛ ክፍል 6:30 ላይ ፕሮግራማቸውን የሚያጠናቅቁ እና በተገለፀው ሰዓት ወደቤት የሚሸኙ ይሆናል። የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፕሮግራም 9:00 ሰዓት የሚጠናቀቅ ይሆናል።
                                           ትም/ቤቱ

Falcon Academy school

08 May, 17:08


ለትም/ቤታችን ተማሪዎች እና ወላጆች
ነገ  ሀሙስ በ01/09/16 በአጠቃላይ የመምህራን ስብሰባ ምክንያት ትም/ት የማይኖር ሲሆን አርብ በ02/09/16 መደበኛ ትም/ት የሚኖር መሆኑን እንገልፃለን።
                                        ትም/ቤቱ

Falcon Academy school

12 Mar, 12:58


ፋልከን  አካዳሚ
ለ9ኛ - 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች
በቅድሚያ የማክበር ስላምታዬን እያቀረብኩኝ የሁለተኛው መንፈቀ ዓመት ቴስት ከ15% የሚያዝ ከቀን 4 - 6/7/2016 ዓም የሚሰጥ ሲሆን በፈተና ወቅት ከተፈታኝ ተማሪዎች የሚጠበቁ ተግባራት በሚከተለው መልኩ ቀርበዋል
1ኛ - ዩኒፎምርም አሟልቶ መምጣት
2ኛ - የተማሪነት መለያ የሆነውን የተማሪ መታወቂያ ይዞ መገኘት
3ኛ - አስፈላጊ የሆኑ የት/ርት ቁሳቁስ ይዞ መገኘት (እርሳስ፣ እስክርቢቶ ፣ ላጲስ ፣ ካልኩሌተር የመሳስሉትን ...... )
4ኛ - የፈተና ሰዓትን በማክበር ት/ቤት መገኘት ይኸውም የጠዋት ተፈታኝ 2:ዐዐ ሲሆን ከሰዓት ተፈታኝ 6፡30 መገኘት አለባቸው ::
5ኛ - ከ20 ደቂቃ በኋላ የሚመጣን ተማሪ ፈተና ላይ አይቀመጥም።
6ኛ - የጠዋት ተፈታኝ ሆነው የተመደቡት 10ኛ እና 12ኛ ሲሆኑ 9ኛ እና 11ኛ የከሰዓት ተፈታኝ ናቸው ::
7ኛ - የጠዋት ተፈታኞች ከሰዓት በኋላ በቤታቸው ሆነው የማንበቢያ ጊዜ ሲሆን የከሰዓት ተፈታኞች ጠዋት በቤታቸው ሆነው የማንበቢያ ጊዜያቸው ይሆናል፡፡
ማሳስቢያ
ወላጆች ልጆቻችሁን በልዩ ትኩረት ማየት አለባችሁ በተለይ ቤት የሚገቡበትን ጊዜ መቆጣጠርና እንዲያነቡ ክትትል ማድረግ አለብን።

ኪዳኔ ብርሀኔ ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል የስራ ሒደት መሪ