ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

@eslmnan_teqebelu


ቻናሉ የተከፈተበት ዋና አላማ ሚሽነሪዎች እስልምና ላይ ለሚቀጥፏቸው ቅጥፈቶችም ሆነ ሊሚያነሷቸው
ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጥበታል
እዲሁም ክርስትና እና እስልምና ይነፃፀርበታል
ኑ እስልምናን ተቀበሉ in box እጠብቃቹሀለው👇👇

in box👉 @Yarebi_12

ነይ 👆👆👆

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:23


ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው ማንን ነው?

በ  — ዮሐንስ 20፥28 ላይ ባለው ጥቅስ የተሰጠ ማብራሪያ ይነበብ

ለማንበብ👉 [ ጌታዬ እና አምላኬ ]

ሼር ይደረግ ቻናላችን እድገቱ ተቀዛቅዟል😔ምን ታስቦ ነው🧐

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:23


ሙግት ሁለት

እኛ ከፈለግን ጌታና አምላክ የሚለው አብን ብቻ ነው ብለን መሞገት እንችላለን ከላይ ልናገር እደሞከርኩት መታወቅ ያለበት ጥቅሱ ለኢየሱስ ቢሆንም አምላክ ሊያደርገው እንደማይችል ነው ነገር ግን እውነታው ምንድነው የሚለውን እንድትረዱት በሚለው ነው እንጂ ለኢየሱስም ቢሆን የሚያመጣው ለውጥ የለም ሆኖም እስኪ ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው አብን ነው ብለን እንሞግት ከጥቅሱ ጋር ተመሳሳይ ናሙና እንይ
ዘፍጥረት 19፥18 “ሎጥም አላቸው፦ ጌታዬ ሆይ፥ እንዲህስ አይሁን፤”
እንግሊዝ ኛውን KJV ተመልከት
And Lot said unto them, Oh, not so, my Lord

አማርኛው ላይ ጌቶች ብሎ አስቀምጦታል ነገር ግን ኢንግሊዝኛዎችን ብታዩ ጌታዬ ብሎ ነው ያስቀመጠው እንዴ ነጃ ምን ነካህ መልአክቶች እኮ መልእክተኞች ናቸው  ሉጥ እኮ ጌታዬ ሲል በመልአክቶቹ አማካኝነት ጌታዬ እያለ የሚያናግረው እግዚአብሔርን ነው የምትሉን ከሆነ እንግዲያውስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ስለሆነ ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው በኢየሱስ በኩል አብን ነው ኢየሱን የአብ ተላኪ እና መልክት አቀባይ ስለሆነ
ዮሐንስ 17፥3 “እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 2:5 አንድ አምላክ Θεοῦ አለና፥ በአምላክ Θεοῦ እና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም *ሰው* የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ Θεοῦ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤
የሐዋርያት ሥራ 2:22 የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላክ Θεοῦ በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከአምላክ Θεοῦ ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤

እንግዲህ ኢየሱስ ሰው ከሆነ እና አንዱ አምላክ የላከው ከሆነ ሰው የሆነው ኢየሱስ እና አንዱ አምላክ ሁለት የተለያዩ ማንነት እና ምንነት ናቸው ማለት ነው፤ ኢየሱስ የሚያመልከው የራሱ አምላክ እንዳለው አይተናል የዛ የሚያመልከው ተላላኪ እና መልክት የሚያደርስ ከሆነ ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው በኢየሱስ በኩል ለአብ ነው!

መዝጊያ

ክርስቲያኖች ብድግ ይሉና አይ ቀጣይ ላይ እኮ “ኢየሱስም፦ ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው።” ስለዚህ ቶማስ ያለው ኢየሱስን ነው ይሉናል ኢየሱስን ቢሆንም ለኛ የሚያመጣው ለውጥ የለም ለምን እንዲህ እዳልኩኝ ላስረዳቹ እደ ባይብል ጌታ የሚለው ሆነ አምላክ የሚለው ለሁለት ይከፈላሉ
የበሀሪ ጌትነት እና የሹመት ጌትነት
የባህሪ አምላክነት እና የሹመት አምላክነት
በሚል ለሁለት ይከፈላሉ

ነጥብ አንድ
የባህሪ ጌትነት እና አምላክነት

የባህሪ ጌታ እና አምላክ ማነው ከተባለ እደ ባይብል አብ ነው ያ አምላክ በጌትነቱ ላይ ባርነት የሌለበት በጥበቃው ላይ እንቅልፍ የሌለበት በህያውነቱ ላይ ሞት የሌለበት አንዱና ብቸኛው አምላክ አብ ነው የኢየሱስ የሀዋሪያቱ የስጋ ለባሽ ሁሉ አምላክና ጌታ አብ ነው
ኤርምያስ 32፥27 “እነሆ፥ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ በውኑ እኔን የሚያቅተኝ ነገር አለን?”
ዮሐንስ 20፥17 “ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ
#አምላኬና ወደ #አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።”
ሮሜ 1፥7 በአምላክ ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥3 “ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
2ኛ ቆሮ 1፥2 “ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
ሉቃስ 1፥32 እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤”

በሉቃስ 1:32 ጌታ አምላክም የተባለው አብ መሆኑን ክርስቲያኖች ያምናሉ ያ ጌታ አምላክ የኢየሱስ የሀዋሪያት የሁሉም ፍጥረት አባትና አምላክ እንዲሁም ጌታ ስለሆነ ጌትነቱ የእርሱ የግሉ በሀሪው እንጂ ከጊዜ ቡሀላ ስላልተቀበለው የባህሪ ጌታ እና አምላክ የሚወስደው አብ ነው ሲቀጥል

ነጥብ ሁለት
የሹመት ጌትነት እና አምላክነት

የሹመት ጌትነት እና አምላክነት ምንድነው ሲባል እደባይብል ጌታም አምላክም የተባሉ ፍጥረታት አሉ ለምሳሌ ነቢያቶች መልዐክቶች ፃድቃን ሰዎች ጌታም አምላክም ተብለዋል እነዚህ ፍጡራን ጌታ እና አምላክ ሲባሉ የባህሪ ጌትነትን እና አምላክነትን የሚይዘውን ከአብ እኩል ሳይሆን ሹመትን አመልካች ነው እነዚህ ጌታ እና አምላክ የተባሉ ፍጡራን የሚያመልኩት አምላክ አላቸው በጌትነታቸው ላይ ባርነት አለባቸው ጌታ ወይም አምላክ ቢባሉም ባሪያ የሆኑለት አምላክ ስላላቸው ከጊዜ ቡሀላ ያገኙት ስለሆነ የሹመት ጌትነት ውስጥ ይመደባሉ ለናሙና አምላክ የተባሉ
ዘጸአት 7፥1  መዝሙር 82:1-6  ዮሐንስ 10:34-35

"አምላክ" በነጠላ ሲሆን "አማልክት" ደሞ በብዜት ነው ስለዚህ ነቢያቶች መልዐክቶች እንዲሁም ፃድቃን ሰዎች አምላክ ሲባሉ አምላክ የሚለውን ሹመት ከጊዜ ቡሀላ የተሰጣቸው በመሆኑ ከሹመት አምላክነት ውስጥ ይመደባሉ በተመሳሳይም ጌታ የተባሉ ነቢያት መልዐክት እዱሁም ፃድቃን ሰዎች አሉ
ለናሙና ጌታ የተባሉ
ዘፍጥረት 18፥12  ዘፍጥረት 23፥11  ዘካርያስ 6፥4
እነዚህ ነቢያትና መልዐክት ጌትነትንም ሆነ አምላክነትን ያገኙት ከሀያሉ አምላክ ስለሆነ ከጊዜ ቡሀላ ያገኙት እና የተሾሙበት ስለሆነ ጌትነታቸው የሹመት ጌትነት ነው ኢየሱስም ጌትነቱን እደሌሎች ነቢያቶች ከጊዜ ቡሀላ ነው ያገኘው
ሐዋርያት 2፥36 እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።”

እዚኛውም ጥቅስ ላይ አምላክ የተባለው አብ ነው ያ አምላክ ኢየሱስን ጌታ እና ክርስቶስ አድርጎታል ስለዚህ ቶማስ ኢየሱስን ጌታዬ ማለቱ ምንም የሚገርም ነገር አይደለም ምክንያቱም ነቢያቶች መልዐክትም ፃድቃን ሰዎች ጌታዬ ስለተባሉ በተመሳሳይ ዮሴፍ ጌታ ተደርጓል ልክ እደ ኢየሱስ
ዘፍጥረት 45:9
እግዚአብሔር በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ጌታ አደረገኝ፤ ወደ እኔ ና፥ አትዘግይ፤”

ስለዚህ ኢየሱስ የሚመደበው የሹመት አምላክነት እና ጌትነት ውስጥ ነው ምክንያቱም ኢየሱስ እደሌሎች ነቢያቶች ጌትነቱን ከጊዜ ቡሀላ ነው ያገኘው የሚያመልከው አምላክ አለው የአምላክ ባሪያ ነው ስለዚህ ኢየሱስ የሹመት ጌትነት ውስጥ ይመደባል በአጭሩ ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው ኢየሱስን ነው ቢባል እራሱ ሌሎች ነቢያቶችና መልዐክቶች በተባሉበት ልክና መጠን እንጂ የባህሪ አምላክና ጌታ ለማለት አይደለም ምክንያቱም ኢየሱስ ጌታ እንዳለው ሊናገር እንጂ እዲያመልሉት ስላልመጣ የኢየሱስ ጌታውም አምላኩም ደሞ አላህ ነው

5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ 

እንደ ኢየሱስ ለጌታችን ባሪያ መሆን ምንኛ መታደል ነው? ስለዚህ የኢየሱስን ጌታ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ጌታችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።


ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:23


ቶማስ ጌታዬ እና አምላኬ ያለው ማንን ነው?

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَا أَمَرْتَنِي بِهِ أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ


ክርስቲያኖች ከመፅሀፋቸው ላይ ኢየሱስን አምላክ ያደርግልናል ብለው ከሚጠቀሟቸው ዋነኛ እና ዋቢ ጥቅስ መካከል ቶማስ ኢየሱስን ጌታዬ አምላኬ ብሎ ጠራው የሚለውን ሰገደለት በሚል እያጭበረበሩ ሊያወዘጋግቡ ይሞክራሉ ሆኖም ግን ሰገደለት ሆነም መለሰለት አማርኛው በስነስርአት አላስቀመጠውም ወደ እንግሊዝ ኛው እና ወደ ግሪኩ ስንሄድ እየተረዳነው እንሄዳለን ለማንኛውም ጥቅሱ እንዲህ የሚል ነው
“ቶማስም፦ ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።”
  — ዮሐንስ 20፥28
እንግዲህ ይሄን ጥቅስ በሁለት መልኩ መሞገት እንችላለን አንደኛው ሙግታችን ጌታ የተባለው ኢየሱስ ነው አምላክ የተባለው አብ ነው በሚል ሁለተኛው ደሞ ጌታም አምላክም የተባለው ኢየሱስ አይደለም አብ ብቻ ነው በሚል  በአጭሩ ግን መታወቅ ያለበት ጥቅሱ ለኢየሱስ ቢሆንም አምላክ ሊያደርገው እንደማይችል ነው ነገር ግን እውነታው ምንድነው የሚለውን እንድትረዱት በሚለው ነው

ሙግት አንድ

ግራም ፒል ሻም ፕሩል የሚባል ነገር አለ በግራም ፒል ሻም ፕሩል ህግ መሰረት ሁለት የማዕረግ ስሞች "ጌታ" አምላክ"ንጉስ" ወዘተ ከፊታቸው "ሆ"ὁ" ማለትም "ዘ""The" የሚል ጠቃሽ አመልካች መትፀአምር ከተጠቀመ በመቀጠል "ካይ"καὶ" "እና" "And" መትፀአምር ከተለየ ዓረፍተ ነገሩ ተመሳሳይ ሙያ ከሆነ ሁለት የተለያዩ ማንነቶች ናቸው ይለናል በዚህ ህግ መሰረት ቶማስ ሁለት የማዕረግ ስሞችን ተጠቅሞ እናገኘዋለን "ጌታ" እና "አምላክ" የሚለውን ግሪክ ሰብቱጀብትን መመልከት ይቻላል
20:28ἀπεκρίθη Θωμᾶς καὶεἶπεν αὐτῷ ὁ κύριός μου καὶ ὁ θεόςμου
በተመሳሳይ እንግሊዝ ኛውን መመልከት ይቻላል
Thomas said to him, “The Lord me and Teh God me !”

በግሪኩ"ሆ"ὁ" እና "ካይ"καὶ" የሚለውን በእንግሊዝኛው ደሞ "ዘ"The" እና "ኤንድ"and" የምትለዋን አስምሩልኝ ስለዚህ ይሄን ህግ ይዘን ቶማስ "ጌታዬ" እና "አምላኬ" ሲል ማንን እና ማንን ለማለት ነው የሚለን እንመልከት ተመሳሳይ ናሙና ብንመለከት
“በአንተ ያለውን ግብዝነት የሌለበትን እምነትህን አስባለሁ፤ ይህም እምነት ቀድሞ በአያትህ በሎይድ በእናትህም በኤውንቄ ነበረባቸው፥ በአንተም ደግሞ እንዳለ ተረድቼአለሁ።”
  — 2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥5

ይሄን ጥቅስ በግሪክ እና በእንግሊዝኛው ብትመለከቱት በአያትህ በእናትህ በሚለው መካከል "እና" ወይም ካይ "καὶ" ኤንድ "and" የሚል መትፀአምር ይጠቀማል ስለዚህ ጳውሎስ ለጢሞቲዎስ ሲናገር አያትህ እና እናትህ የሚል ሁለት የማዕረግ ስሞችን እናገኛለን ይህም ማለት እናት የተባለችው እና ሀያት የተባለችው ሁለት የተለያዩ ማንነቶች መሆናቸውን ያስረዳናል በተመሳሳይ ቶማስም ጌታዬ እና አምላኬ ሲል ሁለት የተለያዩ ማንነቶችን እየጠቀሰ ነው ሌላ ናሙና ስናይ  
“ስለዚህ ሰው አባቱ እና  እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፥”
  — ማርቆስ 10፥7

በተመሳሳይ አባት እናት በሚለው መካከል "እና" ወይም ካይ "καὶ" ኤንድ "and" የሚል መትፀአምር ተጠቅሞ እናገኛለን ስለዚህ አባት እና እናት የሚለው ሁለት ማንነቶችን አመልካች ነው ስለዚህ እናትና አባት አንድ ማንነት ናቸው እደማንለው ሁሉ በተመሳሳይ ጌታዬ እና አምላኬ ሲል ሁለት የተለያዩ ማንነቶችን እየጠቀሰ ነው የሚል ነው ጌታ የተባለው ኢየሱስ ነው አምላክ የተባለው አብ ነው ቶማስ አምላኬ ያለው ለኢየሱስም ለሀዋሪያቶችም አምላክ ለሆነው አብ ነው
ዮሐንስ 20፥17 “ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ
#አምላኬና ወደ #አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።”

እዳያቹት ለሀዋሪያቶቹም ለኢየሱስም አምላክ ወደሆነው ማለት ነው ስለዚህ የአብ አምላክነት ለቶማስ ብቻ አይደለም ለኢየሱስም ጭምር ስለሆነ ለሀዋሪያቶቹም የአብ አምላክነት የተነገረው ቶማስንም ስለሚጨምር አምላኬ ሲል አብን አመልካች ነው
ሮሜ 1፥7 በአምላክ ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”

"God our Father" ከአምላክ ከአባታችን አለ ስለዚህ የኢየሱስም የሀዋሪያቱም አምላክ እና አባት አብ ከሆነ ቶማስ አምላኬ ያለው አብን እንጂ ኢየሱስን አይደለም
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥3 “ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
2ኛ ቆሮ 1፥2 “ከአምላክ ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።”
 
አምላክ የሚለው አብን ነው ጌታ የሚለው ኢየሱስን ነው ስለዚህ ቶማስም ጌታዬ ሲል ኢየሱስን ነው አምላኬ ሲል ደሞ አብን ነው ሁለቱ ደሞ የተለያዩ ማንነቶች ነው ለዛ ነው
1ኛ ቆሮንቶስ 6፥14 “አምላክም ጌታንም አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።”

ስለዚህ አምላክ የሚባለው አብ ነው ተነሳ የተባለው ጌታ ደሞ ኢየሱስ ነው በተመሳሳይ
ሐዋርያት 2፥36 እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ።”

እዚኛውም ጥቅስ ላይ አምላክ የተባለው አብ ነው ያ አምላክ ኢየሱስን ጌታ እና ክርስቶስ አድርጎታል ስለዚህ ቶማስ ኢየሱስን ጌታዬ ማለቱ ምንም የሚገርም ነገር አይደለም ምክንያቱም ነቢያቶች መልዐክትም ፃድቃን ሰዎች ጌታዬ ስለተባሉ
ዘፍጥረት 18፥12 “ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን?
#ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል።”
ዘፍጥረት 23፥11 “አይደለም፥
#ጌታዬ፥ ስማኝ፤ እርሻውን ሰጥቼሃለሁ በእርሱም ዳር ያለውን ዋሻ ሰጥቼሃለሁ በወገኔ ልጆች ፊት ሰጥቼሃለሁ፤ ሬሳህን ቅበር።”
ዘካርያስ 6፥4 ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረውም መልአክ መልሼ፦ ጌታዬ ሆይ፥ እነዚህ ምንድር ናቸው? አልሁት።”

ስለዚህ ኢየሱስ ጌታዬ ሲባል ጌትነቱን የተቀበለውና ከጊዜ ቡሀላ ያገኘው ስለሆነ የሚመደበው ሳራ አብርሃምን ጌታዬ ባለችው አብረሀምም መልአኩን ጌታዬ ባለው ዘካሪያስም መልአኩን ጌታዬ ባለው መልኩ እንጂ የአምላክነት መገለጫ አይደለም ነው ካላቹ እንግዲያውስ ነቢያቶች እና መልዐክት ሁሉም አምላክ ልታደርጓቸው ነው ስለዚህ ቶማስ ጌታዬ ሲል ከላይ ባየናቸው ጥቅሶች መሰረት ኢየሱስን ነው አምላኬ ሲል ደሞ ከላይ ባየናቸው ጥቅሶች መሰረት አብን ነው የሚል ሙግት እናቀርባለን ተዋጠልህም አልተዋጠልህን እውነቱ ይሄ ነው ግራም ፒል ሻም ፕሩል ህግ በዚህ መልኩ ነው የሚፈታው!

ለሙግት ሁለት ይሄን ንካው👉 ሙግት ሁለት

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:00


የነቢያት ኃጥያት

እውን ነቢያቶች ኃጢያትን ሰርተዋል ወይስ የስም ማጥፋት ዘመቻ ነው የተካሄደባቸው የነቢያት ኃጥያት በሚል ርዕስ ነቢያቶች ላይ የተቀጠፈባቸውን ቅጥፈት አጋልጠናል ይሄ እውነት ሌሎች ጋር እንዲደርስ ሼር ይደረግ

ፅሁፉን ለማንነብ ስሙን ይጫኑ
👇

የነቢያት ሀጥያት👉 [ ክፍል አንድ ]
የነቢያት ሀጥያት👉 [ ክፍል ሁለት ]

ሼር እያደረጋቹ ሌሎችም ጋር አድርሱልኝ

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:00


ነጥብ ሶስት
ነብዩላህ አሮን(ሀሩን)

በኢስላም ሀሩን ከታላላቅ ነቢያቶች መካከል አንዱ ሲሆን ፃዲቅ ሰው ነው ነገር ግን በባይብል ጣዎት አምላኪ ተደርጎ ስሙ ጠፍቷል
ዘጸአት 32
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² አሮንም፦ በሚስቶቻችሁ በወንዶችና በሴቶች ልጆቻችሁም ጆሮ ያሉትን የወርቅ ቀለበቶች ሰብራችሁ አምጡልኝ አላቸው።
³ ሕዝቡም ሁሉ በጆሮቻቸው ያሉትን የወርቅ ቀለበቶች ሰብረው ወደ አሮን አመጡለት።
⁴ ከእጃቸውም ተቀብሎ በመቅረጫ ቀረጸው፥ ቀልጦ የተሠራ ጥጃም አደረገው፤ እርሱም፦ እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር ያወጡህ አማልክትህ ናቸው አላቸው።
⁵ አሮንም ባየው ጊዜ መሠዊያን በፊቱ ሠራ፤ አሮንም፦ ነገ የእግዚአብሔር በዓል ነው ሲል አወጀ።

እዳያቹት እንግዲህ ጥጃን ሰርቶ እሱን እደሚያመልክ ይናገራል ይሄ ደሞ ትልቅ ወንጀል ነው ከአንድ ነቢይ የማይጠበቅ እና ነቢይ ይሄን ያደርጋል ብለን ህሊናችን ሊቀበለው የማይችል ነገር ነው በእርግጥ ባይብል ነው የታላቁን ነቢይ ሀሩን ስም ያጠፋው እንጂ ቁርአን የትክክለኛውን ሀሩን ታሪክ ስለሚተርህልን ፃዲቅ እደነበረ ጣዎትን እዳላመለከ ነው የሚነግረን

21፥48 *ለሙሳ እና ለሃሩንም እውነትንና ውሸትን የሚለይን ብርሃንንም ለጥንቁቆችም መገሰጫን በእርግጥ ሰጠናቸው*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَا مُوسَىٰ وَهَارُونَ الْفُرْقَانَ وَضِيَاءً وَذِكْرًا لِّلْمُتَّقِينَ

ሃሩን በራሱ መልእክተኛ አይደለም፤ ግን ነቢይ ሆኖ ሙሳን በመልእክቱ በማስተላለፍ ይረዳዋል፤ አላህ ወደ ሕዝባቸው በተዓምራታችንና በግልጽ አስረጅ ላካቸው፦
19፥53 *ከችሮታችንም ወንድሙን ሃሩንን ነቢይ አድርገን ሰጠነው*፡፡     
25፥35 *በእርግጥም ለሙሳ መጽሐፍን ሰጠነው፡፡ ከእርሱም ጋር ወንድሙን ሃሩንን ረዳት አደረግንለት*፡፡
23፥45 *ከዚያም ሙሳንና ወንድሙን ሃሩንን በተዓምራታችንና በግልጽ አስረጅ ላክን*፡፡ ثُمَّ أَرْسَلْنَا مُوسَىٰ وَأَخَاهُ هَارُونَ بِآيَاتِنَا وَسُلْطَانٍ مُّبِينٍ

ስለ ነቢዩ ሃሩን በጥቅሉ ይህንን ይመስላል። ከላይ ባለው ጥቅስ መሰረት እውነትንና ውሸትን የሚለይን ብርሃንንም ለጥንቁቆችም መገሰጫን በእርግጥ ሰጠናቸው የሚለውን አስምሩልኝ ነብዩላህ ሀሩን ሰዎችን ከሙሴ ጋር ሆኖ ከጣዎት እንዲርቁ ሲጣራ የነበረ ፃዲቅ ሰው እንጂ እራሱ ጣዎትን የሚያመልክ ሰው አልነበረም ስለዚህ ፍትህ ለሀሩን በተደረገበት የስም ማጥፋት ዘመቻ ብለናል

ነጥብ አራት
ይሁዳ

የልጁን ሚስት ዝሙት የፈፀመ ይሁዳ ይሁዳ እንግዲህ የዘር ግንዱ ተመዞ ተመዞ ኢየሱስን የሚነካ ሰው ነው ይህም ማለት የኢየሱስ የዘር ግንድ ውስጥ ይሁዳ አለ
ማቴዎስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፤
³ ይሁዳም ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ፤

ይሄ የኢየሱስ የዘር ሀረግ ውስጥ ያለ ታላቅ ሰውን ከልጁ ሚስት ጋር ሴተኛ አዳሪ መስላው ዝሙት ሰራ ብሎ ባይብል ይተርክልናል አጂብ ነው
ዘፍጥረት 38
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ለትዕማርም፦ እነሆ፥ አማትሽ ይሁዳ የበጎቹን ጠጕር ይሸልት ዘንድ ወደ ተምና ይወጣል ብለው ነገሩአት።
… 
¹⁵ ይሁዳም ባያት ጊዜ ጋለሞታን መሰለችው፤ ፊትዋን ተሸፍና ነበርና።
¹⁶ ወደ እርስዋም አዘነበለ፦ እባክሽ ወደ አንቺ ልግባ አላት፤ እርስዋ ምራቱ እንደ ሆነች አላወቀም ነበርና። እርስዋም፦ ወደኔ ብትገባ ምን ትሰጠኛለህ? አለችው።

ሙሉውን ታሪክ ስታነቡት አብረው እደተኙ እና ልጅ እደወለደችለት ዝሙት የሰራች ሴት እዳለች ተነግሮት ሊወግራት ሲሄድ የራሱ ጉድ እደያዘች ስታሳየው እደማራት የዘፍጥረት 38 ሙሉ ታሪኩ ያስረዳናል ሆኖም አንድ ፃዲቅ ከሚባል ሰው እና የኢየሱስ የዘር ሀረግ ከዝሙተኛ ሰው ወይም ከዲቃላ መመዘዙ ከባድ ነው ዲቃላ ደሞ መንግስተ ሰማያት አይገባም
“ዲቃላ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ፤ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ።”
  — ዘዳግም 23፥2
ስለዚህ የኢየሱስ የዘር ሀረግ ውስጥ ዲቃላ አለ ይህ ደሞ ዲቃላ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ ስለተባለ ኢየሱስንም ችግር ውስጥ ይከተዋል

ነጥብ አምስት
ነብዩ ዳዊት

ዳዊት ከጎረቤት ሴት ጋር ዝሙት ፈፅሟል ይለናል ባይብል ነገር ግን ዳዊት ከትላልቅ ነቢያቶች መካከል አንዱ እና በቁርአን ስማቸው ከተጠቀሱ 25 ነቢያቶች መካከል አንዱ ነው እደ ቁርአን ትርክት ዳውድ ፃዲቅ ሰው እንጂ ዝሙተኛ አልነበረም እደባይብል ግን ከጎረቤት ጋር ዝሙት የሰራ ተብሎ ስሙ ጠፍቷል
2ኛ ሳሙኤል 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² እንዲህም ሆነ፤ ወደ ማታ ጊዜ ዳዊት ከምንጣፉ ተነሣ፥ በንጉሥም ቤት በሰገነት ላይ ተመላለሰ፤ በሰገነቱ ሳለ አንዲት ሴት ስትታጠብ አየ፤ ሴቲቱም መልከ መልካም ነበረች።
³ ዳዊትም ልኮ ስለ ሴቲቱ ጠየቀ፤ አንድ ሰውም፦ ይህች የኤልያብ ልጅ የኬጢያዊው የኦርዮ ሚስት ቤርሳቤህ አይደለችምን? አለ።
⁴ ዳዊትም መልእክተኞች ልኮ አስመጣት፤ ወደ እርሱም ገባች፥ ከርኵሰትዋም ነጽታ ነበርና ከእርስዋ ጋር ተኛ፤ ወደ ቤትዋም ተመለሰች።
⁵ ሴቲቱም አረገዘች፥ ወደ ዳዊትም፦ አርግዤአለሁ ብላ ላከችበት።

ዘፋኝ ዳዊት
  — 2ኛ ሳሙኤል 6፥14
  — 2ኛ ሳሙኤል 6፥16

በኢስላም ግን ዳዊት(ዳውድ)ከታላላቅ ነቢያቶች መካከል እንጂ ዝሙተኛ አልነበረም ዘፋኝም አልነበረም
17፥55 ጌታህም በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አብልጠናል፡፡ *"ለዳውድም ዘቡርን ሰጥተነዋል"*፡፡ وَرَبُّكَ أَعْلَمُ بِمَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۗ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ ۖ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا

ነጥብ ስድስት
የአባቱን እቁባት የተገናኘው ሮቤል

“እስራኤልም በዚያች አገር በተቀመጠ ጊዜ ሮቤል ሄደ የአባቱንም ቁባት ባላን ተገናኛት፤ እስራኤልም ሰማ። የያዕቆብም ልጆች አሥራ ሁለት ናቸው”
  — ዘፍጥረት 35፥22


እዳያቹት እንግዲህ ባይብል ነቢያቶችን በጣም ያረክሳቸዋል ይሄ በነቢያቶች ላይ የተቀጠፈባቸው ቅጥፈት ነው እንጂ አንድ ፃዲቅ የሚባል ሰው ይሄን ሊያደርግ አይችልም ስለዚህ ነቢያቶች ከተሰነዘረባቸው ውሸት ያጠራቸው ኢስላም ነው
17፥18 በልም፦ *"እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና"*፡፡ وَقُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ ۚ إِنَّ الْبَاطِلَ كَانَ زَهُوقًا
34፥49 *«እውነቱ መጣ፡፡ ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውም ተወገደ»* በላቸው፡፡ قُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ

በእርግጥ ክርስትና ነቢያቶችን ሁሉ አርክሷቸዋል ሀጥያት እደሰሩ አድርጎ ነው የተረከው ኢስላም ግን ነቢያቶች ፃዲቃን እደነበሩ ይናገራል ታዲያ እርሶ የትኛውን ይመርጣሉ የሌሎች ነቢያቶችን ስም እና የነቢዩ ኢየሱስ ስምን ያረከሰው ባይብልን እና ክርስትና ወይስ የነቢያቶችን ክብር የጠበቀውን ኢስላምን እና ቁርአንን ትከተላላቹ መልሱ ለህሊና

አላህ ሂዳያ ይስጣቹ ለእኛም በቅኑ መንገድ ላይ ሆነን ፅናቱን ይስጠን አሚን

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:00


የነቢያት ሀጥያት

ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

4፥48 አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ

በክፍል አንድ ፅሁፌ ኃጢያት ምን ማለት ነው በስንትስ ይከፈላል እኛ ሙስሊሞች ነቢያቶች ኃጢያት አልሰሩም ስንል “ከባኢር” كبائر ማለት “አበይት ኃጢያት”ነው ማለትም ፦ ሺርክ፣ ዝሙት፣ አራጣ፣ ቁማር፣ ሌብነት ወዘተ...ወይስ
“ሰጋኢር” صغائر ማለት “ንዑሳን ኃጢያት” ነው በአለማወቅ አሊያም በአለፍፅምና የሚመጡ ስህተት ናቸው፤ ለምሳሌ መናደድ፣ መቆጣት፣ ማዘን፣ መበሳጨት ወዘተ.... አልሰሩም የምንለው ከሁለቱ የትኛውን ሀጥያት ነው አልሰሩም የምንለው የሚለውን በክፍል አንድ ፅሁፌ ተመልክተን መተናል በዚኛው ክፍል የምንመከከተው በክርስትና ነቢያቶች ሀጥያት እደሰሩ ተደርገው ተተርኮልና ያ በእነሱ ላይ የተዋሸባቸው ውሸት ነው በኢስላም ደሞ ያ የተዋሸባቸው ውሸት ያጋልጣል እሱን አብረን የምናጋልጥ ይሆናል ሁሉንም ነብያቶች ባንመከትም ዋና ዋና የሚባሉት ነጥብ በነጥብ እንመለከታለን

ነጥብ አንድ
ነብዩላህ ኑሕ

ኑህ እንግዲህ በኢስላም ከታላላቅ እና ስማቸው በቁርአን ላይ ከተጠቀሱት 25 ነቢያቶች መካከል አንዱ ነው ሆኖም በባይብል ትልቅ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተካሂዶበታል እሱም ሰክሮ እደ እብድ ሆኖ እደነበረ የዘፍጥረት ፀሀፊ ይነግረናል
ዘፍጥረት 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ።
²¹ ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ።

²⁴ ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ።

እዳያቹት እንግዲህ ሰክሮ እራቆቱን በድንኩአን ውስጥ መቆየት እብደት ነው ነብይን የሚያክል ነገር አስካሪ መጠጥን መጠጣቱ በራሱ ይሄ ህሊና የማይቀበለውና በዛ ታላቅ ነብይ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ማድረጉ ነው በኢስላም ኑህ የተከበረ ነብይ ነው ኑሕ"ዐለይሂ  ሰላም" የአላህ መልእክተኛ ነው፤ አላህ ወደ እርሱ ወሕይ አውርዷል፦
4፥163 እኛ ወደ ኑሕ እና ከእርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ إِنَّا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ كَمَا أَوْحَيْنَا إِلَىٰ نُوحٍ وَالنَّبِيِّينَ مِن بَعْدِهِ
11፥36 *ወደ ኑሕም እነሆ፦ «ከሕዝቦችህ በእርግጥ ካመኑት በስተቀር ወደፊት አያምኑም፡፡ ይሠሩትም በነበሩት ክህደት አትዘን» ማለት ተወረደ፡፡* وَأُوحِيَ إِلَىٰ نُوحٍ أَنَّهُ لَن يُؤْمِنَ مِن قَوْمِكَ إِلَّا مَن قَدْ آمَنَ فَلَا تَبْتَئِسْ بِمَا كَانُوا يَفْعَلُونَ

አምላካችን አላህ ወደ ኑሕ፦ "ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ" በማለት ላከው፤ እርሱም፦ "ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ለእናንተ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ" በማለት አስጠነቀቃቸው፦
71፥1 *እኛ ኑሕን «ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ» በማለት ወደ ሕዝቦቹ ላክነው።* إِنَّا أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ أَنْ أَنذِرْ قَوْمَكَ مِن قَبْلِ أَن يَأْتِيَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ
7፥59 ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ አላቸውም፡- «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ለእናንተ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ፡፡» لَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَقَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيነው

እዳያቹት እንግዲህ ነቢዩላህ ኑሕ አላህ ያዘዘውን ሲያስተምርና ሲሰብክ የነበረ ጻድቅ ሰው እንጂ አላህ የከለከለውን አስካሪ መጠጥ ጠጥቶ እየተንገዳገደ እራቆቱን እደ እብድ አሎነም ስለዚህ በባይብል ላይ ስሙ ለጠፋው ነብዩላህ ኑሕ ፍትህን እንፈልጋለን

ነጥብ ሁለት
ነብዩላህ ሉጥ

ነብዩላህ ሉጥ ታላላቅ ነቢያት ከሚባሉት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን በቁርአን ስማቸው ከተጠቀሱ 25 ነቢያቶች መካከል አንዱ ነው እንግዲህ ነብዩ ሉጥ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከተደረገበት መካከል ከልጆቹ ልጅን እደወለደ ተደርጎ ነው ዘፍጥረት 19
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁰ ሎጥም ከዞዓር ወጣ፤ በዞዓር ይቀመጥ ዘንድ ስለ ፈራም ከሁለቱ ሴቶች ልጆቹ ጋር በተራራ ተቀመጠ፤ በዋሻም ከሁለቱ ሴቶች ልጆቹ ጋር ተቀመጠ።

… 
³³ በዚያችም ሌሊት አባታቸውን የወይን ጠጅ አጠጡት፤ ታላቂቱም ገባች፥ ከአባትዋም ጋር ተኛች፤ እርሱም ስትተኛና ስትነሣ አላወቀም።
³⁴ በነጋውም ታላቂቱ ታናሺቱን አለቻት፦ እነሆ ትናንት ከአባቴ ጋር ተኛሁ፤ ዛሬ ሌሊት ደግሞ የወይን ጠጅ እናጠጣው አንቺም ግቢና ከእርሱ ጋር ተኚ፥ ከአባታችንም ዘር እናስቀር።

አስቡት ከአብራካቹ ክፋይ ልጅን የሚያህል ነገር ከልጆቻቹ ጋር ተራክቦ አድርጋቹ ልጅ ስትወልዱ ከባድ ነው ይሄ ትልቅ የስም ማጥፋት ነው ታላቅ ነቢይ የሚባል እስካሪን መጠጥ አይጠጣም ከልጆቹጋርም አይተኛም ስለዚህ በቁርአን ያለው ሉጥ ስሙ የጠራው ነቢይ ነው ባይብል ያዋረደውን ሉጥ ቁርአን ያከብረዋል አምላካችን አላህ ነብዩ ሉጥን  በሰዶም ድርጊት በተሰማሩ ሕዝቦች መካከል ፍርድንና ዕውቀትን ሰጥቶ ላከው፤ ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ አንዱ ነው፦
37፥133 *ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው*። وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ الْمُرْسَلِينَ
21፥74 *ሉጥንም ፍርድንና ዕውቀትን ሰጠነው፡፡ ከዚያችም መጥፎ ሥራዎችን ትሠራ ከነበረችው ከተማ አዳንነው፡፡ እነርሱ ክፉ ሰዎች አመጸኞች ነበሩና*፡፡ وَلُوطًا آتَيْنَاهُ حُكْمًا وَعِلْمًا وَنَجَّيْنَاهُ مِنَ الْقَرْيَةِ الَّتِي كَانَت تَّعْمَلُ الْخَبَائِثَ ۗ إِنَّهُمْ كَانُوا قَوْمَ سَوْءٍ فَاسِقِينَ

በሉጥ ዘመን በነበረው ለህዝቦቹ የተሰጣቸው ቅጣት ውስጥ በሉጥ ያመኑ ሰዎች ስለነበሩ ሙሉ አለም ላይ የነበሩትን አላህ ቢያጠፋም በሉጥ ነብይነት ያመኑ ነበሩ ስለዚህ እነሱ ተጋብተው እዳዲስ መራባትን ጀመሩ እንጂ እደባይብል ውሸት ከልጆቹ ወለደ ብሎ ያላደረገውን ስሙን አያጠፋም
11፥112 *እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና*፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ وَلَا تَطْغَوْا ۚ إِنَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِي

ያመኑት የሚለው አስምርበት ያመኑ አካላት ነበሩ እንጂ እደ ባይብል ትርክት ሙሉ ህዝቡ ጠፍቶ ሉጥና ልጆቹ ብቻ ቀሩ ብሎ ሉጥን ያላደረገውን ከባድ ወንጀል የሆነውን ዝሙት ከልጆቹ ጋር አድርጓል ብሎ አይተርክም ስለዚህ ባላደረገው ነገር ስሙ የጠፋው ነብዩላህ ሉጥ ፍትህ ይገባዋል

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:00


እዳያቹት እንግዲህ እኛ ሙስሊሞች ክርስትና ነቢያቶችን አርክሷል ኃጢያተኞች አድርጎ ነው የተረከልን ኢስላም ግን ነቢያቶች ኃጢያት እዳልሰሩ ነው የሚተርክልን ስንል “ከባኢር” كبائر ማለትም “አበይት ኃጢያት” አልሰሩም እያልን መሆኑን አይዘንጋ ማለትም  ሺርክ፣ ዝሙት፣ አራጣ፣ ቁማር፣ ሌብነት ወዘተ..ናቸው። በኢስላም አስተምህሮት ሁሉም ነቢያቶች ከእነዚህ ትልልቅ ኃጢያቶች የተጠበቁ ናቸው ነገር ግን ነቢያቶች ከእኛ የሚበልጡት ነቢይ እና ከአምላክ ዘንድ መለኮታዊ ቃልን ስለሚወርድላቸው ነው ነቢይ ደሞ መልአክ አይደለም እደኛው ሰው ነው ስለዚህ ማንኛውም ሰው ትናንሽ ስህተቶችን እደሚሰራው ሁላ ነቢያቶችም ሆነ ነብያችን ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም “ሰጋኢር” صغائر ማለት “ንዑሳን ኃጢያት” የሚባለውን ሐጥያት  በአለማወቅ አሊያም በአለፍፅምና የሚመጡ ስህተት ሊሰሩ ይችላሉ ለምሳሌ መናደድ፣ መቆጣት፣ ማዘን፣ መበሳጨት ወዘተ፦ ስለዚህ እኛ ሙስሊሞች ኢስላም ነቢያቶችን አክብሯል ኃጥያት እዳልሰሩ ነው የሚተርክልን ስንል “አበይት ኃጢያት” እዳልሰሩ እንጂ “ንዑሳን ኃጢያት” አልሰሩም ማለታችን እዳልሆነ ልትረዱን እንሻለን ሲቀጥል ደሞ እደባይብል ትርክት አዎ ነቢያቶች አርክሶ ነው የተረከልን እደግመዋለው ባይብል ነቢያቶችን ለስማቸውና ለባህሪያቸው የማይገባውን ነገርና ተግባር ለጥፎባቸው ሲቀጠፍባቸው የስም ማጥፋት ዘመቻ ሲደረግባቸው አይተናል ሆኖም እኛ ሙስሊሞች ዘንድ የነቢያት ትክክለኛው ትርክት ስላለ በባይብል የጠፋውን ስማቸውን በነጥብ ሁለት ክፍላችን ላይ የምናጠራ ይሆናል ወደዛ ከመሄዴ በፊት ግን ስለ ታሪክ ነገር ትንሽ ልበላቹ ለምሳሌ ነጃ በሳምን ውስጥ ሶስት ቀን እህቶቹን እና ወንድሞቹን ይዞ ወደ መናፈሻ የመሄዴ ልምድ አለኝ ብዬ ብፅፍ ትክክለኛው ትርክት ያለው እኔ በአንደበቴ የተናገርኩት እና በእጄ ፅፌ ያሰፈርኩት ነው  ነገር ግን ሶስት ሰዎች መተው አንዱ ነጃ በሳምን አንድ ቀን አንዱ በሳምን አምስት ቀን አንዱ በወር አንድ ቀን ከወንድሞች እና ከእህቶቹ ጋር መናፈሻ የመሄድ ልምድ አለው ብለው ቢተርኩ ትክክለኛውና ኦርጅናሉ ትርክት እኔ በራሴ አንደበት የተናገርኩት ነው እንጂ እነዚህ ሶስት ሰዎች የተረኩት አይደለም ምን ለማለት ፈልጌ እደሆነ ግልፅ ላድርገው ስለ ነቢያቶች ታሪክ ባይብል ቁርአንም ተርከውልናል ነገር ግን የባይብሉ ትርክት የሰው ቃል እደመቀላቀሉም እደመበረዙም ባይብል እርስ በእርሱ እደመጋጨቱም የባይብል ኦርጅናል ማንስክሪትቶች እደመጥፋታቸው ጭምር ተደማምሮ ባይብል ላይ ያለው ስለ ነቢያቶች የተተረከው ትርክት ነቢያቶች ላይ የተቀጠፈባቸ እና የስም ማጥፋት ዘመቻ እደተደረገባቸው እንረዳለን ነገር ግን የቁርአኑን ትርክት ስንመለከት ቁርአን ላይ የነቢያትን ታሪክ የሚተርክልን ሀያሉን አምላካችን አላህ ሱብሀነ ወተአላ እደመሆኑ የነቢያት ታሪክ የሚያውቅ የተከሰተውን ክስተት የማይረሳ ከተከሰተ ቡሀላ ከመከሰቱም በፊት ያለውን ነገር የሚያውቅና በእውቀቱ ላይ ገደብ የሌለበት አምላክ እደመተረኩ ቅዱስ ቃሉ ቁርአንም በኦርጅናል ማንስክሪፕት ደረጃም ሆነ በሌሌችም መንገድ እስካሁን ተጠብቆ መቆየቱ የነቢያት ትክክለኛው ትርክት የቁርአኑ ትርክት መሆኑ ያስገነዝበናል የሆነው ሆኖ ቁርአን ነቢያቶች ፃድቃን እደነበሩ እንጂ “አበይት ኃጢያት” ሰርተዋል ወይም ረክሰዋል ብሎ አይተርክልንም ምክንያቱም ነቢያቶች እና መልእክተኞች የሚላኩት ከኃጥያት ሊመልሱ እንጂ እነሱ እራሳቸው ሀጥያት ውስጥ እዲቦኩ አይደለም አላህ ሱብሀነ ወተአላ ነቢያትን እና መልእክተንኞችን ሲልክ ከሀጥያት ይጠብቃቸዋል ምክንያቱም ከሚያሳዩት ጥሩ ስነምግባር ነውና ከሰዎች ውስጥ ተመርጠው በጥመት የሚዋልሉትን ሰዎች ከጥመት ውስጥ እዲያወጡ የሚላኩት እውን እደባይብል ትርክት እናዚያ ፃድቃን ናቸው ብሎ ፈጣሪ የመረጣቸው ነቢያቶች እንደዚህ የረከሰ ተግባርን ይፈፅማሉ? አይ ከሆነ መልሳቹ ታዲያ በባይብል ስለ ነቢያቶች የተተረከው ትርክት በነቢያት ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ እደሆነ አንረዳምን? አይደለም ከተባለ እግዚአብሄር እነዚህን ሰዎች  ፃድቃን ብሎ ሲመርጣቸው እሱ በጥብቅ የከለከላቸው ሀጥያቶች ውስጥ እደሚገቡ አያውቅም ነበርን? መልሶቹን ለህሊናቹ ጠይቁት ኢንሻአላህ በክፍል ሁለት ፅሁፌ ነቢያቶች በኢስላም እና በክርስትና ያላቸው ደረጃ እዴት ነው የሚለውን እውነታ አብረን የምናጋልጥ ይሆናል ኢንሻአላህ እስከዛው ለወገናችን ዘአትናቴዎስ(ዳግም) እድታደርሱልኝ ስል እናም ሼር እድታደትጉ ስል በትህትና እጠይቃለው እስከዛው የአላህ ጥበቃ ከእኛ ጋር ይሁን

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

21 Jan, 00:00


የነቢያት ሀጥያት

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

4፥48 አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ


ቢነግሩሽ አትሰሚ ቢጠቅሱሽ አትይ፣ ዝግ ብለሽ ሂጂ ብር ብር አትበይ፡፡ አለ ያገሬ ሰው ወገናችን [ዘአትናቴዎስ] የወይን ጠጅ ጉዳቱ በሚል ርእስ በነጥብ ሁለት ፅሁፌ ላይ ምላሽ እሰጣለው ብሎ የባጡን እና የቆጡን እያደበላለቀ ፅፎ ለቀቀው ወገናችን ዘአትናቴዎስ ከፃፋቸው ነገሮች ውስጥ አንድ አንድ ትኩረቴን የሳቡት ነገሮችን ስለተመለከትኩኝ የነቢያት ሀጢያት በሚል ርእስ ለወገናችን ዘአትናቴዎስ ምላሽም ለሌሎችም እውቀት ይሆን ዘንድ ይዤላቹ መጥቻለው ወገናችን  ዘአትናቴዎስ ነጃ እየቀጠፈ ነው ብሎ በገሀድ የምንመለከተውን የባይብል በነብያት ላይ የተቀጠፈውን ቅጥፈት እና ውሸት ሊያስተባብል ሲሞክር እና ነጃ እውቀት አልባ አቶ ዘአትናቴዎስ(ዳግም) ደሞ የእውቀት ባለቤት አድርጎ በደረሰን ፅሁፍ ላይ መመልከት ችለናል የሆነው ሆኖ እውን ነጃ ዋሽቷል ወይስ አቶ ዘአትናቴዎስ የደበቁት እና ያላወቁት ነገር አለ አብረን እንመልከት ወገናችን ዘአትናቴዎስ እንዲህ በማለት ለማስተባበል ሞክረዋል (ሙስሊም ወገናችን ጽሑፋን ሲጀምር ብቻ አይደለም ፣ መጻፍ የጀመረውን መጣጥፍ ሲያገባድድም ጭምር በቅጥፈት ና በውሸት ነው። ክርስትና ነቢያቶችን የረከሱ አርጎ አያቀርብም ፤ በእርግጥ አንዳድ ነቢያቶች ኃጢአት እንደሰሩ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጽፋል )

ብሎ እራሱ ከመሰከረልን ቡሀላ አንድ አንድ ነገሮችን ጨማምሮ ኢስላምን ለመንካት በዛውም የነጃን እውቀት ወርዶ እንዲታይ ለማድረግ እንዲህ በማለት ተናግሯል (ሌላኛው የሙስሊም ወንድማችን ቅጥፈት ፣ በእስልምና ነቢያት ሀጢአት እንዳልሰሩ እንደሚያስተምር  አድርጎ በሰው አእምሮ ለመሳል ያደረገው ጥረት ነው ፤ ይህም እስልምና ነቢያትን አክብሮአል ለሚለው ተረት መደገፊያ ይሆነው ዘንድ ነው።ሆኖም ነጃ የእውቀት እጥረት ያለበት በክርስትና ላይ ብቻ ሳይሆን ይሆነኛል ፣ ይበጀኛል ብሎ በሚከተለው እምነት በእስልምና ላይም ጭምር ነው ፤ እንደዛማ  ባይሆን ኖሮ ቁርአን ነቢያት ፣ ሙሐመድንም ጨምሮ ኃጢአትን እንደሰሩ እንደሚናገር ባልጠፋው ነበር ። )

ብሎን አረፈው 😁ለማንኛውም ከላይም እዳልኩት ይህ ፅሁፌ ለወገናችን ዘአትናቴዎስ(ዳግም) ምላሽ ብሎ ለለቀው ፅሁፍ ምላሽም በዛውም ለሌሎች ትምህርት እንዲሆን የታሰበ ነው እውን ነጃ ቀጥፏል ወይስ ወገናችን ዘአትናቴዎስ(ዳግም) ምላሽ ብሎ ምእመኑን እያታለለ ይሆን ነጥብ በነጥብ የምናይ ይሆናል


ኃጢያት ምንድነው?

ነቢያቶች ሀጥያት ሰርተዋል አልሰሩም ወደሚለው ከመግባታችን በፊት ኃጥያት እራሱ ምንድነው የሚለውን መረዳት ይኖርብናል ->ኃጢያት ማለት ሰው በተሰጠው ነፃ ፍቃድና ምርጫ መሰረት የአምላክን ፍቃድና ሀሳብ መቃወም ወይም ጥሶ መገኘት ማለት ነው
->አንድን ነገርእንፈፅመው ዘንድ ትእዛዝን ሰቶን እኛም የታዘዝነውን ነገር መፈፀምና መተግባር እየቻልን ሳንፈፅም ስንቀር ኃጥያት ይባላል
->ወይንም አንድን ነገር እዳንቀርበውና እድንርቀው ተነግሮን ያን ነገር አድርገነው ሲገኝ ሀጥያት ይባላል
ኃጢያት በሁለት ይከፈላል፦
“ከባኢር” كبائر ማለት “አበይት ኃጢያት”ሲሆን እነርሱም፦ ሺርክ፣ ዝሙት፣ አራጣ፣ ቁማር፣ ሌብነት ወዘተ..ናቸው።
“ሰጋኢር” صغائر ማለት “ንዑሳን ኃጢያት” ሲሆኑ በአለማወቅ አሊያም በአለፍፅምና የሚመጡ ስህተት ናቸው፤ ለምሳሌ መናደድ፣ መቆጣት፣ ማዘን፣ መበሳጨት ወዘተ፦
53፥32 እነዚያ የኃጢያትን “ታላላቆችና” አስጠያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፤ ግን “ትናንሾቹ” የሚማሩ ናቸው። ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፤ ٱلَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلْإِثْمِ وَٱلْفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلْمَغْفِرَةِ
4፥31 ከእርሱ ከተከለከላችሁት “ታላላቆቹን” ብትርቁ “ትናንሾቹን ኃጢአቶቻችሁን” ከእናንተ እናብሳለን፤ የተከበረንም ስፍራ እናገባችኋለን፡፡ إِن تَجْتَنِبُوا۟ كَبَآئِرَ مَا تُنْهَوْنَ عَنْهُ نُكَفِّرْ عَنكُمْ سَيِّـَٔاتِكُمْ وَنُدْخِلْكُم مُّدْخَلًۭا كَرِيمًۭا
42፥37 ለእነዚያም “የኀጢያትን ታላላቆችና” ጠያፎችን የሚርቁ በተቆጡም ጊዜ እነርሱ የሚምሩ ለሆኑት። وَٱلَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلْإِثْمِ وَٱلْفَوَٰحِشَ وَإِذَا مَا غَضِبُوا۟ هُمْ يَغْفِرُونَ

እንግዲያውስ በኢስላም ነብያት የሚጠበቁት ከአበይት ኃጢያት ነው፤ ከንዑሳን ኃጢያት እንደማንኛውም ሰው አለፍፅምና ስላለባቸው በራሳቸው ሆነ በሰይጣን ሊሳሳቱ ይችላሉ፤ ለምሳሌ አደም ነብይ ነው፤ ግን ሰይጣን ወደ እርሱ ጎትጉቶት የጌታውን ትእዛዝ ጣሰ፤ ተሳሳተም፦
20፥120 ሰይጣንም ወደ እርሱ ጎተጎተ «አደም ሆይ! በመዘውተሪያ ዛፍ በማይጠፋ ንግሥናም ላይ ላመላክትህን አለው፡፡ فَوَسْوَسَ إِلَيْهِ ٱلشَّيْطَٰنُ قَالَ يَٰٓـَٔادَمُ هَلْ أَدُلُّكَ عَلَىٰ شَجَرَةِ ٱلْخُلْدِ وَمُلْكٍۢ لَّا يَبْلَىٰ

በተመሳሳይ ሰይጣን ኢዮብን በጉዳትና በስቃይ ጎድቶታል፤ እንደ ባይብሉም ከእግሩ ጫማ ጀምሮ እስከ አናቱ ድረስ በክፉ ቍስል መቶታል፤ ይህ ሲደረግ ሰይጣንን እግዚአብሔርም ሕይወቱን ተወው እንጂ እርሱ በእጅህ ነው አለው፦
38፥41 ባሪያችንን አዩብንም አውሳላቸው፡፡ *«እኔ ሰይጣን በጉዳትና በስቃይ ነካኝ»* ሲል ጌታውን በተጣራ ጊዜ፡፡ وَٱذْكُرْ عَبْدَنَآ أَيُّوبَ إِذْ نَادَىٰ رَبَّهُۥٓ أَنِّى مَسَّنِىَ ٱلشَّيْطَٰنُ بِنُصْبٍۢ وَعَذَابٍ
ኢዮብ 2፥6-7 እግዚአብሔርም ሰይጣንን ሕይወቱን ተወው እንጂ እነሆ፥ እርሱ በእጅህ ነው አለው። ሰይጣንም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ፥ ኢዮብንም ከእግሩ ጫማ ጀምሮ እስከ አናቱ ድረስ በክፉ ቍስል መታው።

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:58


የቻናል አሪፍ [ ሎጎ ] የምትሰሩ ልጆች የት ናቹ🤔 እስኪ ለቻናሌ አሪፍ ሎጎ ስሩና IN BOX ላኩልኝ
እስኪ ለቻናሌ አሪፍ ፕሮፋይል የሚሰራልኝ ማነው ኤዲስ ማድረግ የምትችሉ ልጆች በግል አናግሩኝ


👉 @Yarebi_12

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:56


◆▮ውይይት▮◆

ነፃ ፍቃድ በክርስትና እና በእስልምና

ተመስገን በኢስላም ነፃ ፍቃድ አለ ብሎ የሚያምን ክርስቲያን ተገኘ ይሄ ትልቅ ለውጥ ነው😘


ወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
         🅥🅢
◍ ከወገናችን Meenaahilikaa Dhugaakoo

-----------------------------------------------
https://t.me/eslmnan_teqebelu

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:56


ነጥብ ሁለት
የወይን ጠጅ ጉዳቱ

እደባይብል ትርክት ከሆነ አብዛኛው ነቢያቶች ሀጥያትን ሰርተዋል ኢየሱስም ጭምር የኢየሱስን ሀጥያት የምንመለከት ይሆናል ነገር ግን በብሉይ ኪዳን ጠጅ ፃዲቃን የሚባሉ ነቢያቶችን ሀጥያት ሲያሰራ እንጂ ጥቅሙን አላየንም ሉጥ ከልጆቹ እዲወል አድርጎታል
ዘፍጥረት 19
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁰ ሎጥም ከዞዓር ወጣ፤ በዞዓር ይቀመጥ ዘንድ ስለ ፈራም ከሁለቱ ሴቶች ልጆቹ ጋር በተራራ ተቀመጠ፤ በዋሻም ከሁለቱ ሴቶች ልጆቹ ጋር ተቀመጠ።

… 
³³ በዚያችም ሌሊት አባታቸውን የወይን ጠጅ አጠጡት፤ ታላቂቱም ገባች፥ ከአባትዋም ጋር ተኛች፤ እርሱም ስትተኛና ስትነሣ አላወቀም።
³⁴ በነጋውም ታላቂቱ ታናሺቱን አለቻት፦ እነሆ ትናንት ከአባቴ ጋር ተኛሁ፤ ዛሬ ሌሊት ደግሞ የወይን ጠጅ እናጠጣው አንቺም ግቢና ከእርሱ ጋር ተኚ፥ ከአባታችንም ዘር እናስቀር።

አስቡት ከአብራካቹ ክፋይ ልጅን የሚያህል ነገር ከልጆቻቹ ጋር ተራክቦ አድርጋቹ ልጅ ስትወልዱ ከባድ ነው የዚህ ሁሉ መዘዝ የወይን ጠጅ ነው  ሲቀጥል የተከበረው ነቢይ ኑህም ሰክሮ እደ እብድ ሲሆን ነበር

ዘፍጥረት 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ።
²¹ ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ።

እዳያቹት እንግዲህ የወይን ጠጅ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል የወይን ጠጅ በእስልምናም ሆነ በክርስትና የተከለከለ ነው ታዲያ ኢየሱስ ምን አስቦ ነው በመጀመሪያ ተአምሩ ውሀን ወደ ወይን ጠጅ ቀይሮ ህዝቡን እዲሰክር ያደረገው ነገሩ እዲህ ነው እረዥም ታሪክ ስለሆነ አጠር አስርጌ ላቅርብላቹ አንድ ሰሞን ላይ ኢየሱስ ሰርግ ሊታደም ይሄዳል በዛ ሰርግ ላይም እንግዳው የወይን ጠጅ በመጠጣት እና በመጨፈር ላይ ነበሩ በዚህ መሀል የወይን ጠጅ ያልቃል የኢየሱስ እናት ማርያምም የወይን ጠጅ ማለቁን ትነግረውና እንስራ ላይ ውሀ እንዲሞሉ አስደርጎ ውሀውን ወደ ወይን ጠጅ ይቀይረዋል ህዝቡም ይጠጣና ይሰክራል ሙሉ ታሪኩን ማንበብ ትችላላችሁ እኔ ፅሁፉ እዳይረዝም ቀንጨብ አድርጌ ላስቀምጥላቹ

ዮሐንስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ።
³ የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው።
… 
⁷ ኢየሱስም፦ ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።
⁸ አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም።
⁹ አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፦
¹⁰ ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው።

ቁጥር አስር ላይ ከሰከሩም በሀላ የምትለዋን አስምሩልኝ እንግዲህ ኢየሱስ ያዘጋጀው የወይን ጠጅ ህዝቡን አስክሮት ነበር  የእኛም ጥያቄ የሚከተለውን ይሆናል ኢየሱስ የወይን ጠጅ መጠጣት ሆነ ማስጠጣት ሀጥያት መሆኑን አያውቅም ነበር? ያውቃል ከተባለ ለምን እያወቀ ሀጥያትን ሰራ? ኢየሱስ መስከርን ሆነ ማሰከር ሀጥያት እደሆነ አያውቅም ነበር? ያውቃል ካላቹ ኢየሱስ እያወቀ ለምን የወይን ጠጅ ጠምቆ እዲሰክሩ ተዋቸው? ይህስ ሀጥያት አይደለምን? ሲቀጥል ደሞ የሰከሩት ሰዎችስ ቢሆን ጥፋትን አጥፍተው ቢሆንስ ምክንያቱም የኢየሱስ ሙሉ ታሪክ በወንጌላት ላይ ስላልተፃፈ

“ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፤ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል።”
  — ዮሐንስ 21፥25

ኢየሱስ ያደረጋቸው ነገሮች ያልተፃፉ ብዙ ካለ ኢየሱስ እዲሰክሩ ያደረጋቸው ሰዎች ሰክረው ሴትን ደፍረው ሰው ገለው ዘረፋ ፈፅመው ቢሆንስ እውን ኢየሱስ በሰዎቹ ላይ ይሄን ማድረጉ ተገቢ ነውን መልሱን ለህሊና ትቻለው

መዝጊያ

በእርግጥ ክርስትና ነቢያቶችን ሁሉ አርክሷቸዋል ሀጥያት እደሰሩ አድርጎ ነው የተረከው ኢስላም ግን ነቢያቶች ፃዲቃን እደነበሩ ይናገራል ታዲያ እርሶ የትኛውን ይመርጣሉ የሌሎች ነቢያቶችን ስም እና የነቢዩ ኢየሱስ ስምን ያረከሰው ባይብልን እና ክርስትና ወይስ የነቢያቶችን ክብር የጠበቀውን ኢስላምን እና ቁርአንን ትከተላላቹ መልሱ ለህሊና

17፥18 በልም፦ *"እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና"*፡፡ وَقُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَزَهَقَ الْبَاطِلُ ۚ إِنَّ الْبَاطِلَ كَانَ زَهُوقًا
34፥49 *«እውነቱ መጣ፡፡ ውሸትም መነሻም መድረሻም የለውም ተወገደ»* በላቸው፡፡ قُلْ جَاءَ الْحَقُّ وَمَا يُبْدِئُ الْبَاطِلُ وَمَا يُعِيدُ
21፥18 *በእርግጥ እውነትን በውሸት ላይ እንጥላለን፡፡ አንጎሉን ያፈርሰዋልም፡፡ ወዲያውም እርሱ ጠፊ ነው*፡፡ ለእናንተም ከዚያ ከምትመጥኑት ነገር ብርቱ ቅጣት አላችሁ፡፡ بَلْ نَقْذِفُ بِالْحَقِّ عَلَى الْبَاطِلِ فَيَدْمَغُهُ فَإِذَا هُوَ زَاهِقٌ ۚ وَلَكُمُ الْوَيْلُ مِمَّا تَصِفُونَ

አላህ ሂዳያ ይስጣቹ ለእኛም በቅኑ መንገድ ላይ ሆነን ፅናቱን ይስጠን አሚን

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:56


አስክሮተ ሀጥያት😜

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

2፥219 አእምሮን ከሚቃወም መጠጥ እና ከቁማር ይጠይቁሃል፡፡ «በሁለቱም ውስጥ ታላቅ ኃጢኣት እና ለሰዎች ጥቅሞች አሉባቸው፡፡ ግን ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ነው» በላቸው፡፡ يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْخَمْرِ وَالْمَيْسِرِ ۖ قُلْ فِيهِمَا إِثْمٌ كَبِيرٌ وَمَنَافِعُ لِلنَّاسِ وَإِثْمُهُمَا أَكْبَرُ مِن نَّفْعِهِمَا ۗ

የጠጅህን ማማር ብርሌህ ነገረኝ፣ ከጠላህ አልደርስም ምንም ቢቸግረኝ፡፡ መጨነቅ መጠበብ ለጠጅ ብቻ ነው፣ ለጠላ መድኀኒት ተወት ማድረግ ነው እነዚህ ሁለት ቅኔዎች አሁን ገና ቦታቸውን አግኝተዋል እነዚህ ሁለቱን ቅኔዎች ለምን እደተቀቀምኳቸው ቡሀላ በደንብ እየተገለጠላቹ ስለሚሄድ አብሽሩ እናተ ብቻ እመኑ እንጂ አሉ እነ እገሌ ለማንኛውም አስካሪ መጠጥ በኢስልምና በክርስትና እዴት ይታያል የሚለውን እንመልከት
2፥219 አእምሮን ከሚቃወም መጠጥ እና ከቁማር ይጠይቁሃል፡፡ «በሁለቱም ውስጥ ታላቅ ኃጢኣት እና ለሰዎች ጥቅሞች አሉባቸው፡፡ ግን ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ነው» በላቸው፡፡ يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْخَمْرِ وَالْمَيْسِرِ ۖ قُلْ فِيهِمَا إِثْمٌ كَبِيرٌ وَمَنَافِعُ لِلنَّاسِ وَإِثْمُهُمَا أَكْبَرُ مِن نَّفْعِهِمَا ۗ

"ኸምር" خَمْرየሚለው ቃል "ኸመረ" خَمَرَ ማለትም "ሸፈነ" "ደበቀ" "ሰወረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ "የሚሸፍን" "የሚደብቅ" "የሚሰውር" ማለት ነው፥
ቁማር መሠረቱ ገንዘብ ስለሆነ ለሰዎች ጥቅም አለው፥ አስካሪ መጠጥ በህክምና አገልግሎት ለሰዎች ጥቅም አለው። ነገር ግን ኸምር ሆነ ቁማር ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ስለሆነ ታላቅ ኃጢኣት አለባቸው፥ አስካሪ መጠጥ ውስጥ የሚካተቱት ጠላ፣ ጠጅ፣ አረቄ፣ ውስኪ፣ ቮድካ ወዘተ ናቸው፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 74, ሐዲስ 14
ኢብኑ ዑመር”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ዑመር በአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” አትሮንስ ላይ ኹጥባህ ሲያደርግ እንዲህ አለ፦ ”ኸምር ሐራም መሆኑ የሚናገረው የወረደው ከአምስት ነገር ማለትም ከወይን፣ ከተምር፣ ከስንዴ፣ ከገብስ እና ከማር ስለሚዘጋጁት ኸምር ናቸው። ዐቅልን የሚሰውር ሁሉ ኸምር ነው”። عَنِ ابْنِ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما ـ قَالَ خَطَبَ عُمَرُ عَلَى مِنْبَرِ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقَالَ إِنَّهُ قَدْ نَزَلَ تَحْرِيمُ الْخَمْرِ، وَهْىَ مِنْ خَمْسَةِ أَشْيَاءَ الْعِنَبِ وَالتَّمْرِ وَالْحِنْطَةِ وَالشَّعِيرِ وَالْعَسَلِ، وَالْخَمْرُ مَا خَامَرَ الْعَقْلَ

እዚህ ሐዲስ ላይ “የሚሰውር” ለሚለው የገባው ቃል “ኻመረ” خَامَرَ መሆኑ ልብ አድርግ! አስካሪ መጠጥ አእምሮን የሚያስት እስከሆነ ድረስ ሙሥኪር ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 36, ሐዲስ 95
ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ”፦ ”ሙሥኪር ሁሉ ኸምር ነው፥ ኸምር ሁሉ ሐራም ነው” ሲሉ እንጂ ሌላ ዐላውቅም”። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، قَالَ وَلاَ أَعْلَمُهُ إِلاَّ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ كُلُّ مُسْكِرٍ خَمْرٌ وَكُلُّ خَمْرٍ حَرَامٌ ‏”‏
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 30, ሐዲስ 3514
ሙዓዊያህ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቼ ነበር፦ ”ሙሥኪር ሁሉ ለሁሉም ምእመናን ሐራም ነው”። سَمِعْتُ مُعَاوِيَةَ، يَقُولُ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ “‏ كُلُّ مُسْكِرٍ حَرَامٌ عَلَى كُلِّ مُؤْمِنٍ ‏”‏

በኢስላም በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ካየን ዘንዳ በክርስትናስ እዴት ይታያል የሚለውን በነጥብ ነጥብ እንመልከት

ነጥብ አንድ
የወንድ ጠጅ መከልከሉ

“አሁንም ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅን የሚያሰክርም ነገር አትጠጪ፥ ርኩስም ነገር አትብዪ።”
  — መሳፍንት 13፥4
“ከወይንም ከሚወጣው ሁሉ አትብላ፥ የወይን ጠጅንም የሚያሰክርንም ነገር አትጠጣ፥ ርኩስም ነገር ሁሉ አትብላ፤ ያዘዝኋትን ሁሉ ትጠብቅ አለው።”
  — መሳፍንት 13፥14
“ከወይን ጠጅና ከሚያሰክር መጠጥ ራሱን የተለየ ያድርግ፤ ከወይን ወይም ከሌላ ነገር የሚገኘውን ሆምጣጤ አይጠጣ፥ የወይንም ጭማቂ አይጠጣ፤ የወይን እሸት ወይም ዘቢብ አይብላ።”
  — ዘኍልቁ 6፥3

በእነዚህ ሶስት ጥቅሶች መሰረት የወይን ጠጅ መጠጣት እና መስከር አጥብቆ የተከለከለ ነው ሲቀጥል ደሞ እንዲው ስንረዳው እራሱ አስካሪ መጠጦች መከልከን እንጂ መፈቀድም የለባቸውም ምክንያቱም በባይብልም ሆነ በዘመናችን በገሀዱ አለም ሰው ሲሰክርና አቅሉን ሲስት ምን እንደሚያደርግ ግልፅ ነው በባይብል እንደውም የአስካሪ መጠጥ ጉዱ ብዙ ነው

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:52


ጡብ የግንብ ወይም ሲራሚክ ስሪት ሲሆን የሚያገለግለውም እንደ ግንብ ያሉ መዋቅሮችን ለመገንባት ነው። ጡብ ከሸክላ አፈር የሚዘጋጅ የብሎኬት አይነት ነው።

ግድግዳ ወይም ግንብ ቋሚ መዋቅር ሲሆን የሚያገለግለውም አንድን የተወሰነ ቦታ ለመከለል እንዲሁም ለመከላከል ነው። ይህ መዋቅር በውስጡ በር እና መስኮቶች ሊኖሩት ይችላል።

ታዲያ እርሶስ በዚህ ጡብ ቤቶን ማስዋብና አጥሮን ማጠናከር ይፈልጋሉ እንግዲያውስ ያናግሩን ያሉበት ቦታ በፈለጉት ቁጥር ይዘን ከች እንላለን የተሻለ ጥራት በጣም በቅናሽ ዋጋ ይደውሉልን


☎️በሳፋሪ:- [ +251707572559 ]

ነጃ የንጽጽር መድረክ | 𝐍𝐞𝐣𝐚 𝐂𝐨𝐦𝐩𝐚𝐫𝐚𝐭𝐢𝐯𝐞

20 Jan, 23:50


ዛሬ እንግዲ ያ ሀያሉ እና ታላቁ አምላክ አይሞትም ማንም አይቀርበዉም ሊቀርበዉ አይችልም የተባለዉ አምላክ በፈጠራቸዉ ፍጡሮች ተመቶ ተገርፎ ተተፍቶበት እርሱ በፈጠረዉ እንጨት ተሰቀለ ሞተ ብለዉ የሚያምኑ የዋህ ህዝቦች የአምላክን ክብር ያዋረዱ አምላካችን ሞተ ብለዉ የሚያከብሯት ቀን ናት እዉን ይሄን የሚያከብሩ ሰዎች ግን ጤነኞች ናቸዉ?

አረ ወገን ጭቅላታቸንን እንጠቀምበት ጭቅላት የተሰጠን እንድናገናዝብበት ነዉ ለዛም ነዉ

ሁሉንም ፈትሹ መልካሙን ያዙ።
[1ኛ ተሰሎንቄ 5:21]

ንቃ

2፥256 በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ ۖ قَد تَّبَيَّنَ الرُّشْدُ مِنَ الْغَيِّ

ከወንድም NEJA 𝑺𝒕𝒖𝒅𝒆𝒏𝒕 🇵🇸
@eslmnan_teqebelu
ወሠላሙ ዐለይኩም

2,300

subscribers

60

photos

29

videos