Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

@eiasc1


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

22 Oct, 19:09


ጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 19፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ ግምገማ ተጀመረ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (ተቅዪም) ቦንጋ ከተማ በሚገኘው የምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ነው።

ዛሬ የተጀመረውና በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ ሑሴን  ሐሰን የተመራው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በ2016 ዓ.ል በምክር ቤቱ በተከናወኑ ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርጓል።

ግምገማው በ2016 ዓ.ል በከፍተኛ ምክር ቤቱ የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል የታዩ ውሱንነቶችን በመለየትና የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ በ2017 ዓ.ል. የክልሉ እስልምና ምክር ቤት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የተሻለ ውጤት ያስመዘግባል ብለው እንደሚጠብቁ ሸይኽ ሑሴን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሴ 18፣ 2016 ዓ.ል በአዲስ አበባ ባደረገው የ2ኛ ዓመት፣ 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል  የሥራ አፈጻጸማቸውን እንዲገመግሙ አቅጣጫ ማመላከቱ ይታወሳል።

ዛሬ በቦንጋ ከተማ በክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተጀመረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ከቦታው የሚገኘው    ቃል አቀባያችን የላከው መረጃ ያመለክታል።


•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

22 Oct, 13:38


ጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 19፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ ክፍሎች የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት የልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች የ2017 ዓ.ል. የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።

በምክር ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተካሄደውን የግምገማ መድረክ የከፈቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሐጂ ከማል ሐሩን፣ የመድረኩ ዓላማ በምክር ቤቱ የሚገኙ የሥራ ክፍሎች በ2017 ዓ.ል የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በሥራ አፈጻጸም ረገድ ያሳዩዋቸውን መልካም ውጤቶች ማስቀጠል እና ክፍተቶችን ማረም ነው ብለዋል።

በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ በምክር ቤቱ ውስጥ የሚገኙ ሀያ የሥራ ክፍሎች የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ያቀረቡ ሲኾን፣ ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎችና ለተሰጡ አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

22 Oct, 08:29


ጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 19፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጠቅላይ ምክር ቤቱ የክልልና የከተማ እስልምና ምክር ቤቶችን የሦራ አፈፃፀም ግምገማ በማድረግ ላይ ይገኛል።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |


በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ የሱማሌ :የሐረ ር : የድሬደዋ እና  የአፋር  ክልል  እስልምና  ጉዳዮች  ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል የሥራ  አፈፃፀም  ግምገማ (ተቅዪም) መጠናቀቁን የግምገማ ቡድኑ አባል ሼይኽ ኢድሪስ ዓሊ ሁሴን (ደጋን)ተናገሩ።

የኢትዮጵያ  እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሴ 18/2016 ዓ.ል በአዲስ አበባ  ባደረገው 2ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባዔ   የክልልና የከተማ አስተዳደሮች እስልምና ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል  የስራ ዕቅድ  አፈፃፀም ክንውናቸውን  እንዲገመግም አቅጣጫ መሠረት ያደረገው የክልልና የከተማ  እስልምና ጉዳዮች የሦራ  አፈፃፀም ግምገማ በሶስት ቡድን ተከፍሎ እየተሰራ መሆኑን ሼይኽ ኢድሪስ ተናግረዋል።

  የእስልምና  ምክር ቤቶቹ ያስመዘገቡት ውጤት   እንደ ክልሎቹ  ነባራዊ  ሁኔታ እንደሚለያይ   ሼይኽ ኢንድሪስ ተናግረዋል።

ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማው  (ተቅዪም) በ2016 ዓ.ል በምክር ቤቱ በተከናወኑ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ትኩረት ማድረጉን  የተናገሩት ሼይኽ  ኢድሪስ ፤ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ  ውጤቶችን  ይበልጥ በማሰቀጠል  የታዩ ክፍተቶችን  በመለየትና  የማስተካከያ  እርምጃ በመውሰድ  በያዝነው 2017 ዓ.ል እስልምና ምክር ቤቶቹ  የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አቅም ይፈጥርላቸዋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤቱ የተጀመረው  የክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል በጀት ዓመት ስራ አፈፃፀም  ግምገማ  (ተቅዪም) ግምገማ ባልተደረገባቸው ክልሎች እንደቀጠለ ሼይኽ ኢድሪስ ተናግረዋል።



•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

21 Oct, 18:53


ጥቅምት 11፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 18፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላይ ምክርቤቱ ፕሬዚደንት ተመርቆ ተከፈተ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ባሌ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኾነውን የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መርቀው ከፈቱ።

በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን እና ከፍተኛ ዓሊሞች ተገኝተዋል።

የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መሥራችና ዋና አስተባባሪ ዶክተር ጀይላን ገለታ በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የዩኒቨርሲቲው መከፈት በአካባቢው ማኅበረሰብ የእስልምና እውቀት ላይ ትልቅ አሴት ይጨምራል ብለዋል።

የዩንቨርሲቲው መሥራች ለባሌ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መከፈት ከአካባቢው ማኅበረሰብና ከበጎ አድራጊዎች ትብብር ባሻገር መንግሥትም ትልቅ ድጋፍ በማደረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዩኒቨርሲቲው ምረቃ ላይ ሲናገሩ፣ ባሌ ሮቤ በኢትዮጵያ የእስልምና ትምህርት ላይ ትልቅ አሻራ ያሳረፈ የዓሊሞች መፍለቅያና ትልቅ ታሪክ ያለው አካባቢ መኾኑን ጠቅሰው፣ ይህን መሰል ዩኒቨርሲቲ መከፈቱ ለእስላማዊው ትምህርት ጥራት ትልቅ የብርሃን ጎዳና እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሁኑ ጊዜ 80 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው ይህ ዩንቨርሲቲ ከሃይማኖታዊ ትምህርት ባሻገር በተለያዩ የአካዳሚ ዘርፎች ትምህርት የሚሰጥበትና ማኅበረሰቡን የሚያገለግል በመኾኑ፣ ሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ዩኒቨርሲቲውን እንደ ሃብታቸው እንዲንከባከቡት ፕሬዚደንቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መከፈት ማኀበራዊ ችግርን በእውቀት ለመፍታት፣ ለመንፈሳዊ ሕይወት ልዕልና፣ እንዲሁም ለትምህርት ጥራት አስተዋጽዖ እንደሚያበረክት ክቡር ሸይኽ ሐጂ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዚሁ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ምሥረታ ሂደት ላይ የተሳተፉትን የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናትን፣ እንዲሁም ዓሊሞችን አመሥግነዋል።

መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከሚያደርገው ጥረት አኳያ የዩኒቨርሲቲው መከፈት ለሀገር ትልቅ ዕድል መኾኑ የተጠቀሰ ሲኾን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሚቻለው ሁሉ ከዩኒቨርሲቲው ጎን ለመቆም ቃል ገብቷል።

በባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲን የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ መርቀው በከፈቱበት ስነ ሥርዓት ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን፣ የመንግሥት ተወካዮች፣ የዑለማ ጉባዔ ተወካዮች እና ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

19 Oct, 20:51


ጥቅምት 9፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 16፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በሀዲያ ዞን በሙስሊሞችና በፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መካከል የተፈጠረ ግጭትና አለመግባባት በእርቀ ሰላም ተፈታ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ወራቤ |

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሀዲያ ዞን፣ አንሌሞ ወረዳ በ2015 ዓ·ል ከገና በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ በጭንጎ ቀበሌ ነዋሪ ሙስሊሞች እና በበንደሊቾ ቀበሌ ነዋሪ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች መካከል ተፈጥሮ የነበረው ግጭትና አለመግባባት በእርቀ ሰላም መፈታቱ ተሰምቷል።

ግጭትና አለመግባባቱ በእርቀ ሰላም መፈታቱን ለማብሰር የሰላም ኮንፈረንስ መርኃግብር ተካሂዷል።

እርቁ የተካሄደው የሁለቱም ሃይማኖት የበላይ መሪዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ባደረጉት ያልተቋረጡ ጥረቶች እና ተከታታይ ውይይቶች መኾኑ ተነግሯል።

በእርቀ ሰላም ኮንፈረንሱ ላይ ለመገኘት ከኢትዮጵያ አስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሰላም ክልልና የዲያስፖራ ጉዳይ ዋና ተጠሪ ሐጂ ሙስጠፋ ናስር፣ የሕዝብ ግንኙነት ተጠሪ ሼይኽ ሑሴን ሐሰን፣ የወጣቶችና የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ ሼይኽ አብዱል ሐሚድ አህመድ ወደ ስፍራው መጓዛቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በኮንፈረንሱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዚደንት ሐጂ ሙሐመድ ኸሊል፣ የክልሉ መጅሊስ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልወሃብ ሸይኽ በድረዲን ሱሩር ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ሸይኽ ዑመር ሙስጠፋ፣ ዋና ፀሐፊው ኡስታዝ ሳዲቅ ወጌቦ፣ የሰላምና እርቅ ተጠሪው ሸይኽ ሙዘይን ሰዒድ፣ የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ተጠሪው ሸይኽ አባስ ያሲን፣ የክልሉ የመንግሥትና የፀጥታ አካላት፣ የሀዲያ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ማትዮስ አኒዮ፣ የዞኑ የመንግሥትና የፀጥታ አካላት፣ የአንሌሞ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አማኑዔል እና የወረዳው የመንግስትና የፀጥታ አካላት ተገኝተዋል።

በመጨረሻም ለእርቀ ሰላሙ አስተዋፅዖ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች የዕውቅናና የሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶ፣ ኮንፈረንሱ በሁለቱም ሃይማኖቶች መሪዎች ዱዓ እና ፀሎት ተጠናቋል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

18 Oct, 13:34


ጥቅምት 8፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 15፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መስማት የተሳናቸው ወገኖች ቁርኣን የሚቀሩባቸው ተቋማት እንዲስፋፉ ተጠየቀ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

መስማት የተሳናቸው ወገኖች ቁርኣን የሚቀሩባቸው ተቋማት ሊስፋፉ እንደሚገባ በኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ማኅበር ፕሬዚደንት አቶ ኑርሰፋ ኸሊል ተናገሩ።

ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት ማኅበሩ ዛሬ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የስብሰባ አዳራሽ፣ "እኛም በቋንቋችን ቁርኣን መቅራት እንችላለን" በሚል መሪ ሐሳብ ለአባላቱ ባካሄደው የዳዕዋ መርኃግብር ላይ ነው።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በተፈጥሮ እና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ሳቢያ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችን የሚደግፍ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት መከፈቱን የጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ኦፊሰር ሲስተር ኢንትሳር አየለ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለ'በኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ማኅበር' የሕጋዊነት ፈቃድ እና ቢሮ ሰጥቶ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ሲ/ር ኢንትሳር ተናግረዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የሳዑዲ አረቢያ ዜግነት ያላቸው ሼይኽ ኢህሳም ሙሐመድ አል-አንሷሪ ኢትዮጵያ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች በማኅበር ተደራጅተው ዲናቸውን እንዲያውቁ የሚሠራ ድርጅት በመኖሩ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሕጋዊ እውቅና የተሰጠው ''በኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ማኅበር'' በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋ ሳቢያ መስማት የተሳናቸው ወንድምና አህቶችን በምልክት ቋንቋ  የቅዱስ ቁርኣንና የዲን ትምህርት ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው  አወሊያ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በአዲስ አበባ አሥራ አምስት መስጂዶችና በአራት ክልሎች ትምህርት እየሰጠ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

ዛሬ በተካሄደው የዳዕዋ መርኃግብር ላይ በተለያዩ ጊዜያት በምልክት ቋንቋ የዲን ትምህርት በመስጠትና በማስተርጎም ማኅበሩን ላገለገሉ በጎ ፈቃደኞች የምሥጋና የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲኾን፣ የተለያዩ አስተማሪ ፕሮግራሞች በማኅበሩ አባላት ለታዳሚው ቀርበዋል።


•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

18 Oct, 07:08


ጥቅምት 8፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 15፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሚሰጠን ድጋፍና የሚያደርገው ክትትል አቅም ሆኖናል" - ሼይኽ ሙሐመድ ኸሊል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
"የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እየሰጠን ያለው ድጋፍና የሚያደርገው ወቅታዊ ክትትል አቅም ሆኖናል" ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሼይኽ ሙሐመድ ኸሊል ተናገሩ።

ፕሬዘደንቱ ይህን የተናገሩት ትላንት ሐሙስ የማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (ተቅዪም)   ወራቤ ከተማ በሚገኘው የምክር ቤቱ ጽ/ቤት በተካሄደበት መድረክ ላይ ነው።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ በ2016 ዓ.ል የበጀት ዓመት ለክልሉ የእስልምና ጉዳይ ከፍተኛ ምክር ቤት የተለያዩ የአቅም ግንባታ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን የተናገሩት ፕሬዚደንቱ፣ በቀጣይም መሰል ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።

ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማው በ2016 ዓ.ል በምክር ቤቱ በተከናወኑ ሥራዎች ላይ ትኩረት ማድረጉን የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ተጠሪ ሼይኽ ሑሴን ሐሰን ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል፣ በታዩ ክፍተቶች ላይ የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ በያዝነው 2017 ዓ.ል የበጀት ዓመት የክልሉ  እስልምና ምክር ቤት ካለፈው ዓመት የተሻለ ውጤት  ያስመዘግባል ብለው እንደሚጠብቁ ሸይኽ ሑሴን  ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሴ 18፣ 2016 ዓ.ል ባደረገው 2ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባዔ  በወሰነው ውሳኔ መሠረት፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል ክንውናቸውን እንዲገመግሙ ባመላከተው አቅጣጫ መሠረት የተጀመረው ዓመታዊ ግምገማ ዉጤታማ መሆኑ ተነግሯል።

ትላንት በወራቤ ከተማ የተጀመረው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ነገ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ በቦታው የሚገኘው ቃል አቀባያችን መረጃ ያመለክታል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

16 Oct, 08:37


ጥቅምት 6፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 13፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የደቡብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ ግምገማ ተጀመረ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (ተቅዪም) ወላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኘው የምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ነው።

ዛሬ የተጀመረውና በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ ሑሴን ሐሰን የተመራው የደቡብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በ2016 ዓ.ል በምክር ቤቱ በተከናወኑ ሥራዎች ላይ ትኩረት አድርጓል።

ግምገማው በ2016 ዓ.ል በከፍተኛ ምክር ቤቱ የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል የታዩ ውሱንነቶችን በመለየትና የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ በ2017 ዓ.ል. የክልሉ እስልምና ምክር ቤት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የተሻለ ውጤት ያስመዘግባል ብለው እንደሚጠብቁ ሸይኽ ሑሴን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሴ 18፣ 2016 ዓ.ል በአዲስ አበባ ባደረገው የ2ኛ ዓመት፣ 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል  የሥራ አፈጻጸማቸውን እንዲገመግሙ አቅጣጫ ማመላከቱ ይታወሳል።

በዚሁ መሠረት የተጀመረው የደቡብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ከኦሮሚያ እና ከሲዳማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች በመቀጠል የተጀመረ ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ መሆኑ ተነግሯል።

በቀጣይ በሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች እንደሚቀጥል ከቦታው የሚገኘው    ቃል አቀባያችን የላከው መረጃ ያመለክታል።

ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የተጀመረው የደቡብ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ነገ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

14 Oct, 11:41


ጥቅምት 4፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 11፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የሲዳማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ ግምገማ ተጀመረ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (ተቅዪም) ሐዋሳ በሚገኘው የምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

ዛሬ የተጀመረውና በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሰላም፣ የክልል እና የዲያስፖራ ዘርፍ ተጠሪ ሐጂ ሙስጠፋ ናስር የተመራው የሲዳማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በ2016 ዓ.ል በምክር ቤቱ በተከናወኑ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ትኩረት አድርጓል።

በ2016 ዓ.ል በከፍተኛ ምክር ቤቱ የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል በታዩ ውስንነቶች ላይ ማስተካከያ እንደሚደረግ ሐጂ ሙስጠፋ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሴ 18፣ 2016 ዓ.ል በአዲስ አበባ ባደረገው የ2ኛ ዓመት፣ 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል የሥራ አፈጻጸማቸውን እንዲገመግሙ አቅጣጫ ማመላከቱ ይታወሳል።

በዚሁ መሠረት የተጀመረው የሲዳማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ባለፈዉ ሳምንት በኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት መካሄዱን መዘገባችን ይታወሳል።

በቀጣይ በሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች እንደሚቀጥል ከቦታው የሚገኘው ቃል አቀባያችን የላከው መረጃ ያመለክታል።

ዛሬ በሐዋሳ ከተማ የተጀመረው የሲዳማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ነገ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

12 Oct, 12:30


ጥቅምት 2፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 9፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"ኢትዮጵያ ለአፍሪካ-አረብ የዲፕሎማሲ ግንኙነት መጀመር  ቀደምት ሀገር ናት።"
- ረ/ፕሮፌሰር አደም ካሚል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
አገራችን ኢትዮጵያ የአፍሪካ እና የአረቡ ዓለም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ፈር ቀዳጅ እንደኾነችረ/ፕሮፌሰር አደም ካሚል ተናገሩ::

ረ/ፕሮፌሰርአደም ካሚል ይህን የተናገሩት "Africa: Challenges of Fragility and Capitalizing of International Competitions በሚል መሪ ሐሳብ   የውጪ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከአል ጀዚራ የጥናትና ምርምር ተቋም ጋር በመተባበር በስካይላይት ሆቴል ባሰናዱት ቀጠናዊ ጉባዔ ላይ ነው።

በኢትዮጵያ እና በአረቡ ዓለም መካከል እስልምና በታላቁ ነቢይ (ሶ.ዐ.ወ.) ከመሰበኩ አስቀድሞም የረዥም ዘመናት የንግድ እና የፖለቲካ ግንኙነት እንደነበረ ያወሱት ዑስታዝ አደም፣ የዛሬ 1 ሺህ 440 ዓመት የነቢዩ ቀደምት ተከታዮች በጃዕፈር ቢን አቡ ጧሊብ መሪነት ወደ ኢትዮጵያ በስደት ሲመጡ ይህ ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ማደጉን ተናግረዋል።

በዚህም መነሻነት "ኢትዮጵያ ለአፍሪካ-አረብ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ፈር ቀዳጅ አገር ናት" ሲሉ ፕሮፌሰር አደም ካሚል ተናግረዋል።

በዚሁ ጊዜም እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ንጉሥ ነጃሺ አገር በሰላም መጣችሁ በማለት ለጉባዔው ታዳሚዎች የመልካም ምኞት መግለጫቸውን አቅርበዋል።

ነብያችን ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) "እርሱ ዘንድ አንድም የማይበደልበት ንጉሥ አለ" በማለት በጃዕፈር ኢብኑ አቡ ጧሊብ መሪነት ሶሐቦቻቸውን "የእውነት አገር" ወዳሏት ሐበሻ፣ በተለይም ፍትኃዊ መሪ መኾኑን ወደመሰከሩለት ንጉሥ አስሐመተል ነጃሺ መላካቸውን ተናግረዋል።

በውጪ ጉዳይ ኢንስቲትዩት እና በአል-ጀዚራ የጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው ቀጠናዊ ጉባዔ በኢትዮጵያ  ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያ መሆኑ ተነግሯል።

በጉባዔው ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት የተወከሉ ከፍተኛ የመንግሥታት ተጠሪዎች፣ የውጭ ግንኙነትና የደኅንነት አሰላሳዮች እና አማካሪዎች መሳተፋቸው ተነግሯል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

11 Oct, 18:03


ጥቅምት 1፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ 8፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መሠረታዊ የኮምፒዩተር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት ዘርፍ በሥራ አመራር ኢንስቲትዩት መሠረታዊ የኮምፒዩተር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱልዓዚዝ አሎ ጠቅላይ ምክር ቤቱ አሥተዳደራዊ አሠራሮቹን ለማዘመን በሚያደርገው ጥረት በተለያዩ ዘርፍ ሠራተኞች ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመፈተሽ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱን የሥራ ክፍሎች በኔትወርክ የማስተሳሰር ሥራዎች መጀመራቸውን ያስታወሱት ምክትል ሥራ አስኪያጁ፣ የትስስር ቅድሚያ ከተሰጣቸው የሥራ ክፍሎች የፋይናንስ፣ የሰው ኃይልና የንብረት ክፍል መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመሰጠት ላይ የሚገኘው የኮምፒዩተር ሥልጠና ከድርጅቱ ፍላጎት ጋር የተናበበ መሆኑንም አቶ አብዱልዓዚዝ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ አቶ ሐሰን ሙሐመድ ሥልጠናው ለተቋሙ አሠራር በሚያመች ሁኔታ የሠራተኛውን አቅምን እንዲገነባ የተመቻቸ መሆኑን ተናግረዋል።

ሥልጠናው ለስድስት ቀናት ይቆያል።

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

10 Oct, 12:43


መስከረም 30፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ ዓ.ሒ. 7፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የትምህርት ሥራ መመሪያ የትውውቅና አተገባበር ውይይት መድረክ ተጀመረ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክተር በሥራ ላይ የሚያውለውን የትምህርት ሥራ መመሪያ የትውውቅ እና አተገባበር ውይይት በጠቅላይ ምክር ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ማካሄድ ጀመረ።

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሼይኽ ሐሚድ ሙሳ በንግግራቸው እስልምና ለትምህርት ከፍተኛ ቦታ መስጠቱን አስታውሰው፣ የትምህርት ሥራ በመመሪያ መደገፉ ሥራውን ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

ለአዲስ አበባ ከተማና ለክፍለ ከተማ የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የሥራ ኃላፊዎች እየተሰጠ ያለውና በቀጣይ ጊዜያት በሥራ ላይ የሚውለው የትምህርት ሥራ መመሪያ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ከፍተኛ ኤክስፐርት በሆኑት ሐጂ ሙሐመድ  ይመር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተዘጋጅቶ የካቲት 11፣ 2016 ዓ.ል. በአዲስ አበባ ስተይ ኢዚ ሆቴል ለውይይት ቀርቦ የነበረው ረቂቅ መመሪያ ከትግራይ ክልል በስተቀር የሌሎች የክልልና የከተማ እስልምና ጉዳይ ከፍተኛ ምክር ቤቶች  ተወካዮች ተሳትፈውበት መሻሻል ይኖርበታል የተባሉ ሐሳቦች በውይይቱ ተሳታፊዎች መቅረባቸውን በጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርት ና ማሕበራዊ  አገልግሎት  ዳይሮክቶሬት ተጠሪ ኢንጂነር አንዋር ሙስጠፋ አስታውሰዋል።

ዛሬ በጠቅላይ ምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ በትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዘርፍ የቀረበው የትምህርት ሥራ  መመሪያ ላለፉት ስድስት ወራት በተሳታፊዎች የተሰጡ የማዳበሪያ ሐሳቦችን በማካተት መቅረቡን በጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርት ና ማሕበራዊ  አገልግሎት  ዳይሮክቶሬት ተጠሪ ኢንጂነር አንዋር ሙስጠፋ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከተቋቋመ ካለፉት አምስት አሠርት ዓመታት ጀምሮ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ለመስጠት መሞከሩን የጠቀሱት ኢ/ር አንዋር እንዲህ ዓይነት መመሪያ አውጥቶ ሥራ ላይ ማዋል ባለመቻሉ በሚፈለገው መልኩ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ አለመቻሉን ተናግረዋል ።

በጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት  ዳይሬክተር የተዘጋጀውና ይፀድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ የትምህርት ሥራ መመሪያ፣ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን የአካል ጉዳተኞች ሁኔታ ያማከለ፣ እስላማዊ እሴቶችን ያከበረና መማር ማስተማሩ ጤናማ እንዲሆን አዎንታዊ አስተዋፅኦ  የሚያደርግ፣ በዋነኛነትም የሕዝበ መስሊሙን የትምህርት ተሳትፎ የሚያሳድግ በመሆኑ ታሪካዊ እንደሚያደርገው ኢ/ር አንዋር ተናግረዋል።

የሥራ መመሪያው በጠቅላይ ምክር ቤቱ ሲፀድቅ በቀጣይ ቀሪ ክልሎች እንደየአካባቢያቸው ተጨባጭ ሁኔታ  ተግባራዊ በማድረግና የጋራ ትስስር ለመፍጠር ጠቀሜታው ከፍ ያለ መሆኑም ከመድረኩ ተነግሯል።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

10 Oct, 11:03


መስከረም 30፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ ዓ. 7፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ በባህል እና በሃይማኖት ያላቸውን መመሳሰል የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከር መጠቀም ይገባል - የሠላም ሚኒስቴር

*

ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ በባህል እና በሃ
ይማኖት ያላቸውን መመሳሰል የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከር መጠቀም እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ ተናግረዋል፡፡

በሰላም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በሞሮኮ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልዑክ ከሞሮኮ የኢንዶውመንት እና የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር አሕመድ ተውፊቅ ጋር ተወያይቷል።

ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ በባህል እና በሃይማኖት ተመሳስሎሽ እንዳላቸው የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው፤ “እነዚህ ዕሴቶች በሀገራቱ መካከል እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር መጠቀም ይገባል” ብለዋል፡፡

የሞሮኮ የኢንዶውመንትና የሃይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር አሕመድ ተውፊቅ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ሃይማኖቶችን በመገናዘብ እንዲኖሩ ማድረጓ እና ለእንግድነት አቀባበል ያላት ታሪካዊ ቅርስ የሁሉም ኩራት መሆኑን አንስተዋል፡፡

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ቤተሰቦችን እና ባልደረቦችን በዚያ ፈታኝ ወቅት በማስተናገድ የዋለችው ውለታም በሙስሊሙ ዓለም ታሪክ ውስጥ በደማቁ የተጻፈ መሆኑን አበክረዋል፡፡

በሁለቱ ሀገራት ሕዝቦች መካከል ያለውን የባህል፣ የታሪክና የሃይማኖት ግንኙነት ለማጠናከር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እንደሚሠራ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን የሁለቱ ሀገራትን የሁለትዮሽ ግንኙነት የሚያጠናክሩ የልምድ ልውውጥ መረድኮችን ለማከናወን በሞሮኮ ይፋዊ ጉብኝት እያደረገ እንደሚገኝ ከሠላም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡



•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

09 Oct, 18:58


መስከረም 29፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ ዓ. 6፣ 1446 ዓ.ሒ.
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አዲስ አበባ ስታዲየም አካባቢ በሚገኘው የምክር ቤቱ ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ (ተቅዪም) እያካሄደ ነው።

ማክሰኞ ዕለት የተጀመረው የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የ2016 ዓ.ል የሥራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሼይኽ ሐሚድ ሙሳ ባደረጉት ንግግር፣ መድረኩ በዓመቱ በምክር ቤቱ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችን ለማስቀጠልና የታዩ ውሱንነቶች ላይ የእርምት አቅጣጫ ለማስቀመጥ ጠቃሚ መኾኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ነሐሤ 18፣ 2016 ዓ.ል ባደረገው 2ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ባሳለፈው ውሳኔ የክልልና የከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤቶች የ2016 ዓ.ል የሥራ እቅድ ክንውናቸውን እንዲገመግሙ አቅጣጫ መስጠቱ ይታወሳል።

በዚሁ መሠረት የተጀመረው የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳይ ከፍተኛ ምክር ቤቶች እንደሚቀጥል ሼይኽ ሐሚድ ሙሳ ተናግረዋል።

ትላንት የተጀመረው የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ነገ (መስከረም 30) ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።



•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

09 Oct, 16:51


መስከረም 29፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ሳኒ ዓ. 6፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን በሞሮኮ የልምድ ልውውጥ እያደረገ ነው
.............................................

ከተለያዩ ተ
ቋማት የተውጣጣ የኢትዮጵያ መንግሥት የልዑካን ቡድን በሞሮኮ የልምድ ልውውጥ እያደረገ ይገኛል።

ቡድኑ የመንግሥት የሰላምና ፀጥታ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ ኃላፊዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች የተካተቱበት ነው።

ጉብኝቱ በሁለቱ ሀገራት ያለውን ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር የገለጹት የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር)፤ ሞሮኮ የተለያዩ ሃይማኖቶችና ሕዝቦችን ተከባብረው እንዲኖሩ በማድረግ በአፍሪካ ጠንካራ ኢኮኖሚ የገነባችበት መንገድ ለሀገራችን ጥሩ ልምድ ይሆናል።

የልዑካን ቡድኑ የሞሮኮ ዋና ከተማ ራባት እና ዋና የንግድ ከተማ ካዛብላንካን ጨምሮ በአራት ትላልቅ ከተሞች የሚገኙ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ተቋማትን እንደሚጎበኝ እና ከከተሞቹ የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚወያይ ተገልጿል።

ጉብኝቱን ያስተባበረው የሰላም ሚኒስቴር መሆኑ ገልፆ ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግቦታል።



•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

01 Oct, 17:35


መስከረም 21፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ዓ. 28፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የትምህርት ተቋማት አመራሮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት "የአካዳሚያዊ አመራር ክህሎት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት" በሚል መሪ ሐሳብ ለእስላማዊ የትምህርት ተቋማት መሪዎች ያዘጋጀው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ምክትል ዋና ጸሐፊና ቋሚ የፈትዋ አባል ዶክተር አብደላ ኸድር ሥልጠናው የእስላማዊ የትምህርት ተቋማትን የአመራር ብቃት ለማሻሻል ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

በምክር ቤቱ የሥርዓተ-ትምህርት ክፍል ግምገማ መሠረት ብዙዎቹ የከፍተኛ ደረጃ የእስላማዊ የትምህርት ተቋማት መስፈርቱን ያሟሉ ባለመሆኑ፣ ይህን ሥልጠና ማዘጋጀት አስፈልጓል ብለዋል።

ለእስላማዊ የትምህርት ተቋማት አመራሮች በተዘጋጀው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ላይ የ16 የትምህርት ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል።

ሥልጠናውን የተካፈሉት የከፍተኛ እስላማዊ ትምህርት ተቋማት አመራሮች ከሥልጠናው ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ተሳታፊዎቹ፣ "ሥልጠናው ራሳችንን የመዘንንበት፣ ምን ደረጃ ላይ እንደምንገኝ ያወቅንበትና ክፍተታችንን ያየንበት ለሥራ ያነሳሳን ነው" ሲሉ በመግለጽ፣ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ትውልዳዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ በመሆኑ አመስግነዋል።

የአቅም ግንባታ ሥልጠናውን ላጠናቀቁ የእስላማዊ ትምህርት ተቋማት አመራሮች የምስክር ወረቀት የሰጡት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ሱሩር፣ ሥልጠናው ለሙስሊሙ ማኅበረሰብ መንፈሳዊ ከፍታ፣ አብሮ ለመሥራት፣ የጋራ ርዕይ ለመሰነቅ ትልቅ መሳሪያ በመሆኑ ተቋማትን ማጠናከር ያስፈልጋል" ብለዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ በየዘርፉ የተቋማትን አቅም በማሳደግ ለሰላምና ለአብሮነት የቻለውን ያህል ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የዓሊሞች ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢና የፈትዋ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ጄይላን ኸድር፣ በጠቅላይ ምክር ቤቱ የዓሊሞች ጉባዔ ዋና ፀሐፊ ሼይክ ሙሐመድ ሐሚዲን (ዶ/ር)፣ በአፍሪካ እና በዓለምአቀፍ እስላማዊ ዩንቨርሲቲ ከ30 ዓመት በላይ የማስተማር ልምድ ያላቸው ሸይኽ ሲዲቅ በረካት (ዶ/ር) ተገኝተዋል።


•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

30 Sep, 09:01


መስከረም 20፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ዓ. 27፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለእስላማዊ የትምህርት ተቋማት አመራሮች የአቅም ግንባታ  ሥልጠና መስጠት ተጀመረ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽሕፈት ቤት በአገራችን በሥራ ላይ ለሚገኙና አዲስ ለሚመሠረቱ ከፍተኛ እስላማዊ የትምህርት ተቋማት አመራሮች የሁለት ቀናት የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት  ጀመረ።

"የአካዳሚያዊ አመራር ክህሎት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በጠቅላይ ምክር ቤቱ  የስብሰባ አዳራሽ የተጀመረው ይህ ሥልጠና በጠቅላይ ምክር ቤቱ የዓሊሞች ጉባዔ ዋና ፀሐፊ በሼይክ ሙሐመድ ሐሚዲን (ዶ/ር) ንግግር ተከፍቷል።

ሼይኽ ሙሐመድ ሐሚዲን በንግግራቸው እስልምና ትልቅ ቦታ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ ትምህርት መኾኑን ጠቅሰው፣ የትምህርት ተቋማትን ለሚመሩ ኃላፊዎች የሚሰጡ እኒህን መሰል ተከታታይ ሥልጠናዎች ሥራቸው ውጤታማ እንዲሆን ይረዳቸዋል ብለዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ክቡር ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ለሁለት ቀናት በሸይኽ ሲዲቅ በረካት (ዶ/ር) የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ሥልጠና የተሳካ እንዲሆን ላደረጉት ጥረት ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

ዛሬ በተጀመረው የአቅም ግንባታ ሥልጠና መክፈቻ ላይ በጠቅላይ ምክር ቤቱ የዓሊሞች ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢና የፈትዋ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር  ጄይላን ኸድር እና ሌሎችም ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

28 Sep, 15:54


መስከረም 18፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ዓ. 25፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የጠቅላይ ምክር ቤቱ የልማት ኤጀንሲ የአመራር ለውጥ አደረገ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የልማት ክንፍ የኾነው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ (ኢሙልኤ) አዲስ ለተሾሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጁደዲን ሰይድ የኃላፊነት ርክክብ አካሄደ።

በልማት ኤጀንሲው ቅጥረ ግቢ ዛሬ በተካሄደው መርኃ ግብር ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሐጂ ከማል ሐሩን ጠቅላይ ምክር ቤቱ በለውጥ ሂደት ላይ መኾኑን ጠቅሰው፣ ከለውጦቹ አንዱ የልማት ኤጀንሲውን በቀጣይ ለሕዝብ ተደራሽ ማድረግ መኾኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ላለፉት ዘጠኝ ወራት የተቋሙን የወደፊት አቅጣጫ ለመቅረጽ በባለሙያ ጥናት ሲያስደርግ መቆየቱን ሐጂ ከማል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ ቀደም ሲል በነበረበት የአቅም ውሱንነት ሳቢያ ሰፊውን ሙስሊም ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ አለመቻሉን ተናግረዋል።

የኢሙልኤ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አሕመድ ሑሴን ኤጀንሲው የሚሰጠውን አገልግሎት ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግና አቅሙን ለማሳደግ የተለያዩ ጥናቶች ሲያስጠና መቆየቱን ጠቅሰው፣ ጥናቱን ወደተግባር ለመለወጥ የተቋሙን ሥራ ወደ ከፍታ ሊያደርሱ የሚችሉ የሙያ ዘርፎች ላይ ቦርዱ ቅጥር መፈፀሙን ተናግረዋል።

ኢሙልኤ ከተቋቋመበት ዓላማ አኳያ ሰፊ ሥራ መሥራት ይጠበቅበታል ያሉት የቦርድ ሰብሳቢው በቀጣይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተባብሮ በመሥራት አዲሱ አመራር ለውጥ ማምጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።

አዲሱ የኢሙልኤ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጁደዲን ሰዒድ ኤጀንሲው የሚሰጠውን ሰብኣዊ አገልግሎት በማሳደግ እንደ አገር የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት አዲሱ አመራር ከመቼውም በላይ ዝግጁ መኾኑን ተናግረዋል።

ኤጀንሲው የተለያዩ የሰብኣዊ አገልግሎቶች ላይ የሚሠራውን ሥራ እንደሚያሰፋ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣ ዘር፣ ቀለም እና ሃይማኖት ሳይለይ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሰብዓዊ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

በቀጣይም ሰዎች ከተረጂነት ወጥተው ወደ ረጂነት እንዲቀየሩ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች እና የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ እንደሚሰማራና፣ "ከከጃይ እጅ የላይ እጅ ይበልጣል" የሚለውን የነቢያችን ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ሐዲስ አስታውሰዋል።

አገራችን ኢትዮጵያ የመልማት ተፈጥሯዊ ፀጋ የታደለች አገር መሆኗን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣ በቀጣይ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የድህነት ቅነሳ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት አድርገው እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሥራ አስፈፃሚ አባልና የትምህርትና ማኅበራዊ ዘርፍ ተጠሪ ኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ በአንዳንድ የአገራችን ክፍሎች በደረሱት የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግሮች ሳቢያ የእርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ በመምጣቱ የዕለት ደራሽ ሥራዎች ላይ ኤጀንሲው ጥናት በማድረግ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

26 Sep, 22:55


መስከረም 16፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ዓ. 23፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በ1445 ዓ.ሒ. የሐጅ ጉዞ በግል ቲኬት ቆርጣችሁ ለተጓዛችሁ ሐጃጆች፣ እንዲሁም ክፍያ ፈጽማችሁ ጉዞውን ማድረግ ላልቻላችሁ በሙሉ!
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በ1445 ዓ.ሒ. (2016 ዓ.ል.) የሐጅ ጉዞ በጠቅላይ ምክር ቤቱ የባንክ ሒሳብ ቁጥር ሙሉ ክፍያ አስገብታችሁ፣ ነገር ግን በግላችሁ የአውሮፕላን የደርሶ መልስ ቲኬት ቆርጣችሁ በመጓዛችሁ ምክንያት የቲኬት ክፍያ ተመላሽ ገንዘብ ለጠየቃችሁ፣ እንዲሁም በ1445 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ ለማድረግ ተመዝግባችሁ፣ ገር ግን በተለያየ ምክንያት መጓዝ ላልቻላችሁ፤ ጠቅላይ ምክር ቤቱ አስፈላጊውን ማጣሪያ ካደረገ በኋላ ተመላሽ ገንዘብ በሐጃጅ ስም በተከፈተው የባንክ ሒሳብ ቁጥር ገቢ ማድረጉ ይታወቃል።

ሆኖም አንዳንድ ሐጃጆችና ምዝገባውን አከናውነው ነገር ግን ጉዞ ማድረግ ያልቻሉ ተመዝጋቢዎች፣ ተመላሹ ብር በባንክ ሒሳብ ቁጥራቸው እንዳልገባላቸው ለተቋማችን ተናግረዋል።

ስለሆነም፣ በባንክ ሒሳብ ቁጥራችሁ ገቢ ያልተደረገላችሁ የአውሮፕላን ቲኬት ክፍያ ተመላሽና ለሐጅ ጉዞ ተመዝግባችሁ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ጉዞውን ማድረግ ያልቻላችሁ ተመላሽ ገንዘብ ጠያቂዎች፣ ለጠቅላይ ምክር ቤቱ ገቢ ያደረጋችሁበትን ሰነድ ቅጂ በቴሌግራም ቁጥር +251-920400400 እንድታያይዙልን በአክብሮት  እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት።
•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

26 Sep, 13:50


መስከረም 16፣ 2017 ዓ.ል | ረቢዑል ዓ. 23፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከክልልና የከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች ጋር በመተባበር ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ።

ዛሬ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ቅጥረ ግቢ በተካሄደው የርክክብ ስነ ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ጸሐፊ ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እንደ ሀገር ተከስቶ በነበረው ጦርነት ለከፍተኛ ችግር ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር መዋቅራዊ ግንኝነቱ ተቋርጦ እንደነበር አስታውሰዋል።

በተፈጠረው የሰላም አጋጣሚ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለአቃፊነትና ለሰላም ባደረገው ጥረት ከትግራይ መጅሊስ ጋር ተቋርጦ የነበረው ትስስር እየተጠናከረ መምጣቱን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስተባባሪነት በጉዳት ላይ የነበረውን የትግራይ መጅሊስ ለማገዝ በተደረገው ንቅናቄና የክልል መጅሊሶች ባደረጉት ትብብር የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ለማጠናከር ለትግራይ መጅሊስ ተሽከርካሪ መገዛቱን ተናግረዋል።

በርክክብ ስነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን ሱሩር መረዳዳት የሃይማኖቱ ትልቁ ባህርይ መኾኑን አውስተው፣ የትግራይ መጅሊስ በጦርነቱ ብዙ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ጉዳቶችን እንዳስተናገደ አስታውሰዋል።

ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለተበረከተው ተሽከርካሪ ፌደራል መጅሊስን ጨምሮ 14 የክልል መጅሊሶች የመዋጮ ትብብር ማድረጋቸው ተነግሯል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ አቅሙ በፈቀደ መጠን ተሽከርካሪ ለሌላቸው የክልል መጅሊሶች ተመሳሳይ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እንደሚያደርግ የተናገሩት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንቱ የተሽከርካሪውን ቁልፍ ለትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልቃድር አደም አስረክበዋል።

የትግራይ መጅሊስ ፕሬዚደንት ሸይኽ አደም አብዱልቃድር
በጠቅላይ ምክር ቤቱ አስተባባሪነት የክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤቶች በጦርነት ያሳለፍነውን ችግር ከግምት በማስገባት ለትግራይ መጅሊስ ላበረከቱት ሥጦታ በራሳቸውና በክልሉ መጅሊስ ስም አመስግነዋል።

በመጨረሻም ሸይኽ አደም አብዱልቃድር ሀገራችን የሰላም፣ የመተሳሰብ የፍቅር ሆና ለሁላችንም አላህ የደስታ ብርሃን ያግናጽፈን በማለት ዱዓ አድርገዋል።

በርክክብ ስነ ሥርዓቱ ላይ የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዚደንት፣ የአዲስ አበባ መጅሊስ ተወካይ፣ የዑለማ ጉባዔ ተወካይ፣ እንዲሁም የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሥራ አስፈጻሚዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ቀደም ሲል የክልል መጅሊስ አመራሮች በተገኙበት መድረክ ለትግራይ መጅሊስ የሰባት ሚሊዮን ብር ድጋፍ መደረጉ ይታወሳል።

••••••••••
የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | twitter.com/eiasc1

8,567

subscribers

117

photos

1

videos