ነገረ መለኮት (Theology)

@bibiliotheology


Bibliology

ነገረ መለኮት (Theology)

07 Oct, 04:58


👉የፈረንሳይ ሂውማኒዝም👈
በመጀመሪያው ባለው የ16ኛው ክፍለ ዘመን የሕግ ጥናት በመሰረታዊ የለውጥ ሂደት ውስጥ ነበር። ፍጹማዊ የፈረንሳይ ንጉሳዊ አገዛዝ በፍራንሲስ አንደኛው ስር እያለ አስተዳደራዊ ማዕከሉ እየጨመረ ሲሄድ ለዘመናዊቷ ፈረንሳይ ሕጋዊ የሆነ አመሰራረት እጅግ ጠቃሚ ነበር። የምስረታውን ሂደት ከማፋጠን አንጻር፣ ግቡ ሕጋዊ የሆነ ስርዓት ለመመስረት ሙሉ በሙሉ በፈረንሳይ ለማጽደቅ፣ ይህ የምሁራን ቡድኖችን እርዳታን ፈለገ፣ ማዕከሉም በቦርጀስ እና ኦርላይንስ ዮኒቨርስቲዎች ያደረገ፣ በተግባር ባልታየ ጥናታዊ በሆነ ሁኔታ ላይ በተጠመዱ ምሁራን አማካኝነት አጠቃላይ የሕግ ደንብ በዓለማቀፋዊ መርህ መሰረት ተመሰረተ። ከነዚህም ውስጥ ፈርቀዳጅ ከነበሩት ጉይላውሜ ቡዴ ሁለተኛው ሲሆን፣  ለፈረንሳይ የሚያስፈልገውን የተሳካ እና አትራፊ አዲስ ሕግ ለማግኘት ወደ ሮም ሕግ በቀጥታ መመለስ ያስፈልጋል በማለት ይሞግታል። ከጣሊያን ልማድ ከሆነው የግሪኮ ሮማ የሕግ ጽሑፎችን ማንበብ በመካከለኛው ዘመን ባሉ የሕግ አዋቂዎች የሕግ ማብራሪያ እና የጽሑፍ ስራዎች ብርሀን ውስጥ ስናነጻጽረው፣ ፈረንሳይ የመጀመሪያውን የግሪኮ ሮማ ሕጋዊ ምንጮችን በራሳቸው ቋንቋ በቅደም ተከተል አስፋፍታዋለች።
አንዱ ቀጥተኛው ውጤት የፈረንሳይ ሂውማኒስት ፕሮግራም የውይይት ዘገባዎች በቀጥታ ግልጽ የሆነ ትዕግስት በማጣት በማብራሪያ ጽሑፎች ውስጥ የተካተቱትን ነበር።እንደ አስፈላጊ ጥናታዊ መሳሪያ ሳይታይ፣ ይህም ቀዳሚውን የጽሑፍ ስራ ለማግኘት ትልቅ መሰናክልን ጨመረ። በባርቶለስ እና በአኩርሲየስ የተባሉ ጸሀፊያን በግሪኮ ሮማ የነበሩትን የሕግ ጽሑፎች የተረጎሙበት መንገድ አላስፈላጊ እና የማይገናኝ ነበር። በአንባቢውና በጽሑፉ መካከል የጠሩ ነገሮችን እንደማዛባት አስቀመጡት። እንደ ሂውማኒስት ምሁርነት ማረጋገጫዎች የበለጠ በራስ መተማመን ሲጨምር፣ የአከርሲየስ እና ሌሎችም በጥያቄ ውስጥ ገቡ። ታዋቂው ስፔናዊ ምሁር አንቶኒዮ ኔቢርጃ  በአኩርሲየስ የጽሑፍ ማብራሪያዎች ውስጥ ስላያቸው ዝርዝር ዘገባዎች አሳትሟል።

👉የፈረንሳይ ሂውማኒዝም...የቀጠለ👈
ሬቤላይስ የተባለ ጸሐፊም በንቀት የአኩርሲየስ ምልከታ ያልተገባ እንደሆነ ጽፏል።
የዚህ ዕድገት አስፈላጊነት ለተሀድሶ ያደረገው አስተዋጽዖ የግድ ሊታወቅ ያስፈልጋል። በቦርጀስ እና በኦርላይንስ በፈረንሳይ ሕጋዊ የሂውማኒዝም እንቅስቃሴ ጅማሬ ላይ ተማሪ የነበረው የወደፊቱ የቤተክርስቲያን የተሀድሶ መስራች ጆን ካልቪን፣ ምናልባትም  በ1528 ዓ.ም. በኦርላይንስ እንደነበር ይገመታል። ካልቪን በኦርላይንስ እና በቦርጀስ የማህበረሰብ ሕግን በማጥናቱ ቀዳሚ የሆነን ግንኙነት ከዋናው የሂውማኒዝም እንቅስቃሴ ባህሪይ ጋር ማድረግ አስችሎታል። ይህ ግንኙነት ቢያንስ ካልቪንን ብቁ ችሎታ ያለው የሕግ አዋቂ እንዲሆን አስችሎታል። ይህም በተለይም የጄኔቫ ሕግ እና አዋጅን በማርቀቅ ሂደት ላይ ረዳት ሆኖ እንዲሰራ ጥሪ ሲደረግለት አስገራሚ የሆኑ ሕጎችን ከራሱ እውቀት በማፍለቅ አርቅቋል። ካልቪን ከዚህ በላይ ብዙ ከፈረንሳይ ሂውማኒዝም የተማራቸው ነገሮች አሉ።
የካልቪን ዋና ዘዴዎች ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ በእድሜው ታላቁ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኝ እና ሰባኪ መባሉ ምናልባት በኦርላይንስ እና ቦርጀስ የሕግ ትምህርትን በከፍተኛ ደረጃ ማጥናቱ ውሸትና አከራካሪ ጉዳይ ነው። ብዙ ነገሮች ካልቪን ከቡዴ ብቁ የሆነ የቋንቋ ምርምር እንደተማረ  የሚያመለክት ሲሆን፤ ይህም ከመሰረቱ መልዕክቶችን በቀጥታ ለመረዳት፣ ከስነ ቋንቋ እና ከታሪካዊ ባህሪይ አንጻር አውዳዊ በሆነ መልኩ ለመተርጎምና በነበረበት ዘመን አስፈላጊ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ ነው።  ትክክለኛ በሆነ ትጋት ካልቪን መጽሐፍ ቅዱስን ሲገልጥ በተለይም በስብከቱ ዋና ዓላማው የመጽሐፍ ቅዱስን የእውቀት አድማስ ከአድማጮቹ አውድ ጋር ማገናኘት ነበር። የፈረንሳይ ሂውማኒዝም ለካልቪን ብርታትንና ያለፈውን ነገር በመተው የወደፊት በሆነው በ1550ዎቹ በነበረው የጄኔቫ ከተማ ሁኔታ ላይ ጽሑፎችን ለማዘጋጀት የሚጠቅሙ መሳሪያዎችን በመስጠት አስተዋጽኦ እንዲያደርግ አስችሎታል።

👉የእንግሊዝ ሂውማኒዝም👈
በመጀመሪያዎቹ የ16ኛው ከፍለ ዘመን  የሂውማኒዝም ዋነኛውና አስፈላጊው ማዕከል የነበረው በእንግሊዝ በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ነው፣ በተጨማሪም በኦክስፎርድና በለንደንም አስፈላጊ የነበረ የማይናቅ አስተዋጽዖ ነበራቸው። ካምብሪጅ የቀድሞ የእንግሊዝ ተሀድሶ ቤት ነበር፣ ማዕከሉም "የነጭ ፈረስ ክበብ" የተባለ ሲሆን(በኋላም ይህ ስሙ ተወግዶ የመሸታ ቡና ቤቱ ተዘግቶ የንግስቶች ኮሌጅ ተባለ)፣ ይህም እንደ ሮበርት ባርነስ ያሉ የማርቲን ሉተር በ1520ዎቹ መጀመሪያ የተጻፉ ጽሑፎችን በማግኘት በጉጉት ያነበቡበት እና ውይይት ያካሄዱበት ነው። ይህ የመሸታ ቡና ቤት በቅርብ ጊዜ የቅጽል ስሙ ትንሿ ጀርመን የሚል ስያሜ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቅ የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በካምብሪጅ አካባቢ የንጉሱ ዋና መንገድ እና የካምብሪጅ ኮሚኒስት ፓርቲ አንደኛው ቤት ሲሆን "ትንሿ ሞስኮው" በሚል ስያሜ በ1930ዎቹ አካባቢ ይጠራ ነበር።

ነገረ መለኮት (Theology)

13 Aug, 07:34


👉የስዊዘርላንድ ሂውማኒዝም👈
ከመልክአ ምድራዊ አቀማመጧ የተነሳ  ስዊዘርላንድ በልዩ ሁኔታ የጣሊያን የዳግም ልደት(Renaissance) እሳቤን ተቀብላለች። በዚህ አካባቢ የሚኖሩ ብዙ ተማሪዎች በቬይና ዩኒቨርስቲ እጅግ ተማርከው ነበር። በስነ ጥበብ ትምህርት ውስጥ በቬይና የነበረው ትልቅ ቤተመንግስት የመሰለ አብዮት፣ በኮናርድ ሴልቲስ አማካኝነት በሰፊው ተጽዕኖ ስር የነበረው  ምህንድስና፣ በ15ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ቬይና የሂውማኒስት ትምህርት ማዕከል በመሆን ብዙዎችን የሚስብ ዩኒቨርስቲ አደረገው፤  ታላላቅ የሂውማኒስት ጸሐፊያኖችም እንደ ጆአኪም ቮን ዋት ወይም ተለዋጭ ስሙ "ቫዲያን" የተባለው በቬይና ዩኒቨርሲቲ ሁሉንም የቀለም ትምህርት ክብር ተቀብሏል። በመቀጠልም በ1529 ዓ.ም. ወደ ትውልድ ከተማው "ቅዱስ ጋለን" በመመለስ የከተማው ዜጋ መሪ ሆነ። የባሰል ዩኒቨርስቲም እንዲሁ በ1510 ዓ.ም.  ስመ ጥር እና ውጤታማ የሆነ ዩኒቨርስቲ ሲሆን፣ የሂውማኒስት ቡድኖች ማዕከል ሆነ፣ ከእነዚህም ውስጥ ቶማስ ዊይተንባክ ተጠቃሽ ነው።
የስዊስ ሂውማኒዝም በጥንቃቄ ይጠና የነበረ ትምህርት ሲሆን፣ መሰረታዊው እምነቱና ባህሉን በትክክል መረዳት የሚቻል ነው። ክርስትናን የሚያይበት መንገድ እንደ የሕይወት መንገድ እንጂ እንደ የአስተምህሮ ስብስብ አይደለም። ተሀድሶ በእርግጥ ያስፈልግ ነበር ግን ተሀድሶው የሚገናኘው በቅድሚያ ከቤተክርስቲያን ግብረገብ ጋር ሲሆን እና እያንዳንዱን አማኝ ለማደስ ግለሰባዊ ስነ ምግባር አስፈላጊ ነው ። በስዊዝ ሂውማኒስት እንቅስቃሴ ውስጥ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ለማደስ ምንም የተደረገ ግፊት የለም።
የስዊስ ሂውማኒዝም እምነት በዋነኝነት ግብረገብ ላይ ያተኮረ ነበር፤ መጽሐፍ ቅዱስን ለክርስቲያን እንደ ግብረገባዊ ባህሪይን ማረሚያ እንጂ የእግዚአብሔርን ቃልኪዳን ከመተረክ አንጻር አያዩትም። ይህ እምነትና አመለካከት የጽድቅ አስተምህሮን በተመለከተ ጠቃሚ የሆኑ ነገሮች አሉት። በመጀመሪያ ደረጃ ጥያቄዎች ሉተርን ያነሳሳው  እና ትኩረቱን በአስተምህሮ ላይ እንዲሆን ያደረገው ነገር በስዊዝ አካባቢ ግን ይህ አይነት ጥያቄ ፍጹም አልነበረም።
ጽድቅ(Justification) የሚባለው ነገር አከራካሪ አልነበረም። በእርግጥ የስዊስ ሂውማኒስቶች በሉተር ስለ ጽድቅ ባለው እይታ ግር ተሰኝተው ነበር፣ ስለ ግብረገብ አክራሪ በሆነ እና በሚያስፈራ መልኩ ያመለከተ ይመስላል። ይህም እነርሱ እያደረጉት ካለው የእምነት እንቅስቃሴ ፍጹም የተለየ የማይገናኝ ነው።
የዚህ ምልከታ አስፈላጊነት በቬይና ዩኒቨርስቲ (1498-1502 ዓ.ም.) እና በባዜል(1502-1506 ዓ.ም.) ከተማረው ከሁልድሪክ ዝዊንግሊ ጋር ይገናኛል። በ1519 ዓ.ም. በዙሪክ ዝዊንግሊ ለተሀድሶ ያደረገው ፕሮግራም የስዊስ ሂውማኒስት ግብረገብ መለያን አስገኘ። እስከ 1520ዎቹ በዝዊንግሊ  አስተሳሰብ የጸጋ ዶክተር የሚባለው የአውግስቲን ምልከታዎች አልታዩም ነበር(ከዚያም በኋላ የእርሱ ተጽዕኖ የሚገናኘው በቅድሚያ በቤተክርስቲያን ስርዓት ዙሪያ ባለው የዝዊንግሊ አስተሳሰብ ነው)። በመጨረሻም ዝዊንግሊ የስዊስ ሂውማኒዝም የግብረገብ እምነትን ሰበረው(ከ1523-1525 ዓ.ም. ባለው)። ግን እስከዚህ ጊዜ ድረስ የእርሱ የተሀድሶ ፕሮግራም የነበረው የስዊዝ ሂውማኒስት የግብረገብ አስተምህሮ አመለካከትና ባህሪይን መሰረት አድርጎ ነበር።

ነገረ መለኮት (Theology)

12 Aug, 06:03


👉የሰሜናዊ አውሮፓውያን ሂውማኒዝም👈
በነገረ መለኮታዊ ልዩ የሆነው እና አስፈላጊነቱ የተረጋገጠው የሂውማኒዝም መሰረት ከጣሊያን ሂውማኒዝም ይልቅ የመጀመሪያው የሰሜናዊ አውሮፓውያን ሂውማኒዝም ነው።
የሰሜን አውሮፓውያን ሂውማኒዝም እንቅስቃሴ በእያንዳንዱ የዕድገት ደረጃ ውስጥ የጣሊያን ሂውማኒዝም ወሳኝ የሆነ ተጽዕኖን አድርጓል። በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች ላይ የጣሊያን የዳግም ልደት(Renaissance) እሳቤዎችና ዘዴዎች በሰሜን አውሮፓ ላይ መሰራጨታቸው ተለይቷል።
1. በሰሜን አውሮፓውያን ምሁራን አማካኝነት ወደ ደቡብ ጣሊያን የተዛወረ ሲሆን፤ ይህም በጣሊያን ዩኒቨርሲቲዎች ለማጥናት ወይም እንደ ተልዕኳዊ ዘዴ በማከናወን ነው። ወደ ትውልድ ሀገራቸው ሲመለሱ የዳግም ልደት(Renaissance) መንፈስን ይዘው ተመልሰዋል።
2.በጣሊያን ሀገር ተወላጅ በሆኑ ጣሊያናዊ ሂውማኒስት ጽሑፎች አማካኝነት ሲሆን፤ ሂውማኒዝም ልብን የሚማርኩ ጽሑፎችን በማስተዋወቅ ላይ ትኩረት ያደርጉ ነበር። በዚህም ምክንያት ይጻፉ የነበሩት ደብዳቤዎች የዳግም ልደት(Renaissance) አስተሳሰቦች እንዲስፋፉ እና አርአያ እንዲሆኑ ምክንያቶች ነበሩ። የጣሊያን ሀገር ተወላጅ የሆኑት ጣሊያናዊ ሂውማኒስቶች የጻፉት ጽሑፎች በአብዛኛው በሰሜን አውሮፓ ክፍል እንዲስፋፋ እንዳደረገ ይታሰባል።
3.በሚታተሙ መጽሐፍቶች አማካኝነት፣ ይህም እንደ አልዲን በተባለ በቬኒስ ካለ አሳታሚ በሚገኝ ምንጭ ነው። እነዚህ የጽሑፍ ስራዎች እንደ አዲስ በሰሜን አውሮፓ ባሉ አሳታሚዎች በድጋሜ ይታተሙ ነበር፣ ይህም በስዊዘርላንድ ውስጥ ባለ በባዜል ይደረግ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ ጣሊያናዊ ሂውማኒስቶች ስራዎቻቸውን ለሰሜን አውሮፓ ክፍል በስጦታ ያበረክቱ ነበር፤ ይህም ከእነርሱ ብዙ ነገሮችን እንደወሰዱ ያረጋግጥልናል።
እንዲሁም በሰሜናዊው የአውሮፓ ሂውማኒዝም ሁለት ዋና ልዩነቶች ነበሩ፤ ሁለቱም አስተሳሰቦች በተሳካ መልኩ በስፋት በሁሉም ዘንድ በእንቅስቃሴ ውስጥ ተቀባይነት ያገኘ ነበር።የመጀመሪያው ከዘመናዊው የግሪኮ ሮማ ጊዜ በኋላ በጣሊያን የነበረው ተሀድሶ ልብ በሚነካ ጽሑፍና ንግግር ላይ ተመሳሳይ የሆነ ሀሳብ መኖሩ ነው። ሁለተኛው ኃይማኖታዊ የሆነ ፕሮግራም በቀጥታ ወደ ክርስቲያን ቤተክርስቲያን እንደ አዲስ መነሳሳት እና መነቃቃት እንደሆነ እናገኛለን። የላቲን መፈክር የሆነው "ክርስቲያኒስመስ ሬናሴንስ" "የክርስትና እንደገና መወለድ" የዚህን ፕሮግራም ዓላማ ያጠቃልላል እንዲሁም በዳግም ልደት ጊዜ እንደ አዲስ ከተወለዱ ስነ ጽሑፎች ጋር ያለውን ግንኙነት ያመለክታል።

ነገረ መለኮት (Theology)

11 Aug, 09:12


👉ሂውማኒዝም(Humanism) የቀጠለ...👈
በእነዚህ አጓጊ የሂውማኒዝም አተረጓጎሞች ሁለት ዋነኛ ችግሮች ይገጥማሉ። የመጀመሪያው ቀደም ብለን እንዳየነው ሂውማኒስቶች በቅድሚያ ትኩረት የሚሰጡት ልብ የሚነኩ ሀሳቦችን በማስተዋወቅ እንደ ተገለጡ ነው። ነገር ግን ሂውማኒስቶች ለፍልስፍና አስፈላጊ አስተዋጽዖ አላደረጉም ማለት ግን ትክክል አይደለም። እውነታው ግን ስለ ዓለማዊ ጽሑፎች በጥልቀት የመረዳት ፍላጎት ነበራቸው። በዚህም ምክንያት ስናነጻጽር እነዚያ ታማኝ "ልብ የሚነኩ ሀሳቦችን የሚከታተሉት" ልናስተውላቸው የሚገባ ጥቂት ሂውማኒስቶች በጽሑፎቻቸውም ለፍልስፍና ታማኞች እና ትጉሀን እንደ ነበሩ ነው።
ሁለተኛው ስለ ሂውማኒስት ጽሑፎች በጥንቃቄ ጥናት ሲደረግ ሂውማኒስቶች እንደ የተደበላለቁ አይነት(heterogeneous)ሀሳብ ያላቸው ተደርጎ የሚታሰበውን ነገር አስቀርቷል። ለምሳሌ ብዙ ሂውማኒስት ጸሀፊዎች በእርግጥ የፕሌቶኒዝምን አስተሳሰብ በመደገፍ የሚከራከሩ ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ የአርስቶትሊያኒዝምን ይከተላሉ። ጥቂት ጣሊያናዊ ሂውማኒስቶች ስለ ኃይማኖታዊ ነገሮች የጠለቀ እውቀት ነበራቸው። ጥቂት ሂውማኒስቶች በህዝብ ምርጫ የሚያምኑ ሲሆኑ፣ ሌሎቹ ደግሞ የተለያ ፓለቲካዊ ጸባይን ወስደዋል። በአሁን ጊዜ ያሉ ጥናቶች ስለ ሂውማኒዝም ብዙ በማይማርከው በኩል ባለው ጎን ይሳባሉ፣ ጥቂት ሂውማኒስቶች አስማታዊ በሆኑ እና ጥቅም በሌላቸው ከንቱ በሆኑ ነገሮች ላይ ትኩረት ያደርጋሉ፣ ይህም የእንቅስቃሴውን የተለመደ ምልከታ በአብርሆት ዘመን ጋር ካለው የምክንያታዊነት አስተሳሰብ ጋር ለማስማማት አስቸጋሪ ነው። በአጭሩ አሁን ላሉ ምሁራን ሂውማኒዝም ጥርት ያለ ፍልስፍናዊ የሆነ ሀሳብ የሌለው አይነት እንደሆነ በግልጥ እየታየ ያለው ነገር እየጨመረ ነው። አንድም ፍልስፍናዊ ወይም ፖለቲካዊ ሀሳብ የእንቅስቃሴውን ባህሪ እና ተጽዕኖ የሚገልጥ ነገር የለም። በታሪክ ምሁራን ዘንድ ይህ ሂውማኒዝም የሚለው ስያሜ የተተወ ይመስላል፣ ምክንያቱም ምንም አይነት ወጥ የሆነ ትርጉም የለውም። አንድን ጸሀፊ ሂውማኒስት ነው ማለት የጸሀፊውን ፍልስፍናዊ፣ፖለቲካዊ እና ኃይማኖታዊ ምልከታ ጥቂት ጠንካራ የሆነ መረጃ ያለው እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
  አብዛኛው ተግባራዊ የሆነው አቀራረብ በብዙ ምሁራን ዘንድ በስፋት ተቀባይነት ያገኘው ስለ ሂውማኒስት ያለው ምልከታ እንደ ባህላዊና ትምህርታዊ እንቅስቃሴ ሲሆን፣ በቅድሚያም በተለያዩ መንገዶች ልብን በሚነኩ ሀሳቦች ማስተዋወቅ ላይ ትኩረት ያደረ እንደሆነ ነው። ሂውማኒዝም ስለ ግብረገብ፣ ፍልስፍና እና ፖለቲካዊ ጉዳይ ግን በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚያስቀምጠው ጉዳይ ነው።
ሂውማኒዝም አስፈላጊ በሆነ ባህላዊ ጉዳይ ላይ የጥንት ግሪኮ ሮማ ስራዎችን እንደ ምሳሌ አድርጎ የሚወስድ እንቅስቃሴ ነው። ዋነኛውና አስፈላጊ የነበረው ነገር ወደ ምንጭ መመለስ የሚል ነው። ይህ ላቲናዊ የሆነው የመፈክር ራዕይ የዘመናዊ ምዕራባዊ ባህልን ምንጩ ወደ ሆነው ጥንታዊው ዓለም መመለስ ነው፣ ይህም ባህሉን እንደ አዲስ ለማደስ የጥንት ሀሳቦችን እና እሴቶችን ፍቃድ መስጠትን የሚያመለክት ነው። የግሪኮ ሮማ(classical) ዘመን ለአብርሆት ዘመን ልማድና ምንጭ ነው። በስነ ጥበብ እና በአርክቴክት እንደ ጽሁፍና የንግግር ቃል ያሉ የጥንት መሳሪያዎች እንደ ምንጭ ይታዩ ነበር፣ ይህም በአብርሆት ዘመን የተወሰደ ነገር ነበር። ሂውማኒዝም " የሀሳቦቹ ምንነት ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ሀሳቦች እንዴት ይመሰረታሉ እና ይገለጻሉ" የሚለው ላይ ትኩረት ያደርግ ነበር። ሂውማኒስት የሆነ ሰው ፕሌቶናዊ ወይም አርስቶትላዊ ሊሆን ይችላል ግን በሁለቱም ጉዳዮች ውስጥ በጥንት ጊዜ የተገኙ አስተሳሰቦች ይካተቱበታል። ሂውማኒስት ተጠራጣሪ ወይም አማኝ ሊሆን ይችላል፣ ግን በሁለቱም ሁኔታዎች በጥንት ግኝቶች ሊከራከሩ ይችላሉ።

ነገረ መለኮት (Theology)

09 Aug, 07:42


👉ሂውማኒዝም(Humanism)(ሰውን ማዕከል ያደረገ አስተሳሰብ)👈
ሂውማኒዝም የሚለው ቃል በአሁኑ ጊዚ የእግዚአብሔርን መኖር እና አስፈላጊነት የሚቃወም ወይም ደግሞ ማንኛውንም ፍጹም ዓለማዊ በሆነ ሁኔታ ነገሮችን የሚያይ አስተሳሰብን የሚያመለክት ነው። በዳግም ልደት(Renaissance) ጊዜ ግን ይህ ቃል ትርጉሙ እንደዚህ አልነበረም። አብዛኛዎቹ ሂውማኒስቶች ኃይማኖተኞች የነበሩ እና ትኩረታቸው የክርስትናን እምነት ለማንጻትና አዲስ ለማድረግ የሚጥሩ እንጂ ለማጥፋት የሚጥሩ አልነበሩም። ሂውማኒስት የሚለውን ቃል ለመተርጎም እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው። በቅርብ ጊዜያቶች ውስጥ ሁለት ዋና የአተረጓጎም መስመሮች እንቅስቃሴው ተጽእኖ በፈጠረባቸው መልኩ ትንታኔ ተሰጥቶታል። የመጀመሪያው ሂውማኒዝም የሚለው ቃል የሚያመለክተው የግሪኮ ሮማን(classical) ቋንቋ እና ስነ ጽሑፍ ለማጥናት በትጋት ይደረግ የነበረን እንቅስቃሴ ሲሆን፤ ሁለተኛው የሂውማኒዝም ትንታኔ ደግሞ በዳግም ልደት(Renaissance) ጊዜ የነበረውን አዲስ የፍልስፍና ግኝት እና የሀሳብ ስብስብን የሚያመለክት ነው። እነዚህ ሁለቱም አተረጓጎሞች ጥያቄ የሚነሳባቸው ሲሆን፤ ለምሳሌ:-የዳግም ልደት(Renaissance) ዘመን የግሪኮ ሮማ ቋንቋና ስነጽሑፍ በጥልቀት መጠናት መነሳትን የሚመሰክር ነው ከሚለው ጥያቄ ያልፋል። የግሪክ እና የላቲን ስነ ጽሐፍ እና ቋንቋዎች ይጠኑ የነበሩት በራሳቸው የመጀመሪያ ቋንቋ ነበር። ስለዚህ የሂውማኒዝም አንደኛው ትርጉም ሊሆን የሚችለው በግሪኮ ሮማ ዘመን የነበረውን ነገር በትኩረት ለማጥናት ይደረግ የነበረን እንቅስቃሴን ለማመልከት ይመስላል። ይህ ተመሳሳይ የሆነ ነው፣ ቢሆንም ለምን ሂውማኒስቶች በመጀመሪያ ደረጃ የግሪኮ ሮማን ነገር ለማጥናት ፈለጉ የሚለው ጥያቄ ሊነሳ ይገባል።ያለው መረጃ በማያጠያይቅ መልኩ የሚያመለክተው ለመጨረሻው ምላሽ የሆነ ምክንያትን እንጂ በራሱ መጨረሻ አይደለም። ያ መጨረሻ  የአሁን ዘመን ጽሑፎችን እና ልብ የሚነካ ንግግርን የሚያስተዋውቅ ነው። በሌላ ቃል፣ ሂውማኒስቶች የግሪኮ ሮማን ጥናት ያካሄዱ የነበሩት ልብን የሚነኩ ጽሑፎቻቸውን በመከተል(model) ሊነቃቁበትና ትምህርትን ሊቀስሙበት በመፈለግ ነው። በግሪኮ ሮማ ጥናት እና በቋንቋና የታሪክ እድገት ጥናት ብቁ ችሎታ ያለው መሆን በቀላሉ የጥንት ሀብቶችን ለመበዝበዝ የሚጠቅም መሳሪያ ነው።አብዛኛው ጊዜ  የሂውማኒስት ጽሑፎች ልብ የሚነኩ ነገሮች በትኩረት ያስተዋውቁ ነበር፣ ይህም በንግግር ወይም በጽሑፎቻቸው ውስጥ በጣም በስፋት የግሪኮ ሮማ ጥናቶችን እና የቋንቋና የታሪክ ዕድገቶች ላይ ትኩረት የሚያደርጉ እንደነበር ይጠቁማል።
በሀያኛው ክፍለ ዘመን ያሉ አንዳንድ የሂውማኒስት ተርጓሚዎች እንደሚሉት ይህ እንቅስቃሴ በዳግም ልደት(Renaissance) ጊዜ የተነሳውን የሊቃውንት አስተሳሰብን በመቃወም ሌላ የዕድገት ለውጥ ይዞ የመጣውን አዲስ ፍልስፍና የሚገልጽ ነው ይላሉ። በዚህም ምክንያት የዳግም ልደት(Renaissance) ዘመን የፕሌቶኒዝም ዘመን ሲሆን፣ የዘመነ ሊቃውንት(Scholasticism) ዘመን ደግሞ የአርስቶትሊያን ዘመን ነው የሚል ሙግት አለ። ሌሎች ደግሞ የዳግም ልደት ዘመን በዋነኝነት ጸረ ኃይማኖት የሆነ ድርጊት የተከወነበት እና ለአስራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ለተከሰተው የአብርሆት ዘመን የዓለማዊነት አስተሳሰብ ለመነሳት መሰረት የጣለ ነው በማለት ይከራከራሉ።

ነገረ መለኮት (Theology)

08 Aug, 09:06


👉የቀጠለ..
1.2 የዘመናዊው የአውግስቲኒያን ትምህርት ቤት👈
"የዘመናዊነት መንገድ" እንቅስቃሴ በመጀመሪያው የአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን መሽጎበት የነበረው አንዱ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ነበር። እንዲሁም የዚህ እንቅስቃሴ ዋነኛውም ተቃውሞም የተናሳው በዚሁ ዩኒቨርስቲ ነበር። ለዚህ ተቃውሞ የመጀመሪያው ዋነኛ የነበረው ሰው ቶማስ ብራድዋርዲን ሲሆን፣ በኋላም የካንተርበሪይ ቢሾፕ ነበር። ብራድዋርዲን በኃይለኛ ንዴት በኦክስፎርድ የነበረውን የዘመናዊነት መንገድ አስተሳሰብ በመቃወም "ፔላጊየስን ለመቃወም የእግዚአብሔር ክርክር" በሚል ርዕስ ጽፏል። በዚህ መጽሐፉ የጽድቅ አስተምህሮን በማጉላት የአውግስቲን እይታን መልሶ አመልክቷል። እነዚህም ሀሳቦች የፔላግየስን አስተምህሮ በመቃወም በጻፋቸው ጽሑፎች ውስጥ ተገኝተዋል።
የብራድዋርዲን ሀሳብ በእንግሊዝ ሀገር በጆን ዊክሊፍም ተነስቶ ነበር። ቢሆንም በመቶ አመት ውጊያ ከ1337-1453 ዓ.ም. ምክንያት እንግሊዝ ከሌሎች የአውሮፓ ሀገራቶች ተነጠለች። መሰረታዊው የአውግቲኒያኖች ሀሳብ ከብራድዋርዲን ሀሳብ ጋር ግንኙነት ያለው ሲሆን፣ በሪሚኒው ግሪጎሪ አማካኝነት ይህ ሀሳብ ተወስዶ በአውሮፓ ዋና ክፍል በሆነው በፓሪስ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተተዋወቀ። ግሪጎር ከብራድዋንዲን ይልቅ ብልጫ ያገኘበት ምክንያት፣ እርሱ የኃይማኖታዊ የሕግ ስርዓት ሰጪ የአመራር ቡድን ውስጥ አባል ነበር(የአውግስቲኒያን አመራር) ።  ልክ ዶሚኒሺያኖች የቶማስ አኳይነስን ሀሳብ እንዳስፋፉትና እንዳስተዋወቁት፣ ፍራንሲስኪያኖች የደንስ ስኮተስን ሀሳብ እንዳስተዋወቁት፣ አውግስቲያኖችም የሪሚኒውን ግሪጎሪ ሀሳብ አስተዋወቁ። ይህም የዘመናዊው አውግስቲኒያን ትምህርት ቤት እንቅስቃሴን ጀመረ።
ግሪጎሪ በመጀመሪያ ያደረገው ስለ ዓለም አቀፍ ጥያቄ የኖሚናሊዝሞችን እይታ የወሰደ ሲሆን፤ በእርሱ ዘመን የነበሩ ብዙ አሳባውያኖች እንደሚያደርጉት ጥቂት የእውነታዊነትን ሀሳብ ከቶማስ አኳይነስ እና ከደንስ ስኮተስ በመውሰድ ተጠቅሟል። በዚህም ምክንያት ከዘመናዊነት መንገድ እንቅስቃሴ አቀንቃኝ ከነበሩት ከ ሮበርት ሆልኮት እና ከገብሬይል ቤይል ጋር የጋራ የሆነ ብዙ ሀሳቦች ነበሩት። በሁለተኛ ደረጃ ግሪጎሪ የድነትን ወይም የደኅንነት አስተምህሮን ያበለጸገ ሲሆን፣ አውግስቲኒያዊ ከሆኑ ሀሳቦች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሀሳቦች አንጸባርቋል። ለምሳሌ:- ለወደቀና ኃጢአተኛ ለሆነ ሰው የጸጋ አስፈላጊነትን፣  ጽድቅ በመለኮት ተነሳሽነት እና  መለኮታዊ ቅድመ ውሳኔ ላይ አጽንዖት ሰጥቷል። ደኅንነት ሙሉ በሙሉ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የእግዚአብሔር ስራ እንደሆነ መረዳት ነው።  "የዘመናዊነት መንገድ" እንቅስቃሴ ሰው ለመጽደቅ የተቻለውን ያህል ጥሩ ስራ መስራት አለበት ሲሉ፣ ግሪጎሪ ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው ሊያጸድቅ የሚችለው በሚል ሀሳብ ላይ አጽንዖት ይሰጣል።
"የዘመናዊነት መንገድ" አብዛኛው(ሁሉም አይደለም) አስፈላጊ የደኅንነት ምንጮች መገኛ ያሉት በሰው ተፈጥሮ ውስጥ ነው ይላሉ። እንደ ቤይል ጽሑፍ በጣም አስፈላጊ የሆኑ የደኅንነት ምንጮች የሚገኙት በሰብአዊነት ውስጥ ነው የሚል ነው። የሪሚኒው ግሪግሪ እንደሚሞግተው የደኅንነት ምንጮች የሚገኙት ከአጠቃላይ የሰው ተፈጥሮ ውጪ ነው ይላል። ኃጢአትን በመተው እና ወደ ጽድቅ ለመዞር  የሚቻለው እግዚአብሔር በሰራው በኩል እንጂ በሰው ስራ በኩል አይደለም ይላል።
እነዚህ ሁለት አቀራረቦች ፍጹም የተለያዩ መረዳቶች ያላቸው ሲሆን ጽድቅን ለማግኘት የሰውን ሚና እና የመለኮት ሚና ላይ ያላቸው ትንታኔ የተለያየ ነው። የግሪጎሪ ኦግስቲኒያኒያዊ አስተምህሮ የተገናኘው ከአውግስቲኒያዊው አመራር(Augistinian order) ጋር ሲሆን፣ ከአውግስቲኒያዊ ገዳም ወይም የእርሱን ሀሳብ ከወሰዱት ከዩኒቨርቲዎችና ከትምህርት ቤቶች አይደለም። ይሁን እንጂ የአውግስቲኒያዊ አመለካከቶችን በመጨረሻዎቹ የመካከለኛው ዘመን እና በተሀድሶ ዋዜማ ላይ አስተካክሎ ቀርጾ ያስቀመጣቸው ይመስላል። በተለያዩ መንገዶች  የዊተንበርግ ተሀድሷውያኖች እያንዳንዳቸው አጽንዖት በመስጠት የተጠቀሙት አውግስቲን ፔላጊያውያኖችን ለመቃወም በጻፋቸው ጽሑፎች ነው። ይህም እንደ አዲስ ማግኘት እንደ አዲስ መንቃት ሊባል ይችላል።

ነገረ መለኮት (Theology)

08 Aug, 09:06


👉እውነታዊነት(Realism) እና በአእምሮ መተማመን(Nominalism)...የቀጠለ👈
"ዓለም አቀፍ" የሚለው ሀሳብ ጥቅም ላይ እዚህ ጋር የዋለው ትርጉሙ ግልጽ ስላልሆን በደንብ መብራራትን ይፈልጋል። "እሱ" ሰው ነው እና የሰውነት ምሳሌ ነው። አሁን ፕሌቶን እና አርስቶትልን(አርስጣጣሊስ) እናስብ። እነሱ ሰዎች ናቸው፣ የሰውነትም ምሳሌ ናቸው። እንደዚህ እያልን ልንቀጥል እንችላለን፣ ግለሰቦችን እንደ ብዙሀን ልንሰይም እንችላለን፣ ግን ይህንኑ ንድፍ በተመሳሳይ ግለሰቦችን እንደ የሰዎች ምሳሌ ልናስብ እንችላለን። እውነታዊነት የሰውነት(humanity) ረቂቅ ሀሳብ እወነተኛ የሆነ ህልውና በራሱ አለው ብሎ ይሞግታል። ይህ ዓለም አቀፍ ነው፣ እያንዳንዱ ሰው ለምሳሌ እንደ ሶቅራጥስ፣ ፕሌቶ እና አርስቶትል ግላሰብ የሆኑ ዓለም አቀፋዊ ምሳሌዎች ናቸው። አንድ የሚያደርጋቸው ሰብአዊነት ሶስቱም እያንዳንዳቸው በየራሳቸው ሕልውና ስላላቸው ነው።
በመጀመሪያው የመካከለኛው ዘመን በእውነታዊነት ተጽዕኖ ስር የነበሩ ሁለት ዋና የዘመነ ሊቃውንት ትምህርት ቤቶች ነበሩ። እነሱም የቶሚስም(የቶማስ አኳይነስ አስተሳሰብ) እና ስኮቲስም(የደንስ ስኮተስ አስተሳሰብ) ሲሆኑ የተገኙትም ከቶማስ አኳይነስ እና ከደንስ ስኮተስ ግላዊ ጽሑፎቻቸው ነው። በቀጣይ ባለው በሊቃውንት ዘመን መገባደጃ ላይ ሌሎች ሁለት ትምህርት ቤቶች በኖሚናሊዝም አስተሳሰብ ተጽዕኖ ቁጥጥር ስር ሆኑ። እነዚህም በአጠቃላይ "የዘመናዊነት መንገድ" እና የዘመናዊው የአውግስቲኒያን ትምህርት ቤት በመባል ይታወቃሉ።
1.1. የዘመናዊነት መንገድ
በአሁኑ ጊዜ "የዘመናዊነት መንገድ" የሚለው ስያሜ በአጠቃላይ የኖሚናሊዝምን እንቅስቃሴ ለማመልከት ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን፣ ይህም በአስራ አራተኛው እና በአስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን ላይ የነበሩትን እነ ዊሊያም የኦክሀሙ፣ ፔይሬ ዲ ኤይሊይ፣ ሮበርት ሆልኮን እና ጋብሬይል ቤይል የሚባሉ አሳባውያንን ያጠቃልላል። በአስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን የዘመናዊነት መንገድ በብዙ የሰሜን አውሮፓ ዩኒቨርስቲዎች ጥሶ መግባት ጀመረ። ለምሳሌ በፓሪስ፣ በሄድልበርግ፣ እና በኤርፈርት። በተጨማሪም ፍልስፍናዊ በሆነው የኖሚናሊዝም እንቅስቃሴ የጽድቅ አስተምህሮን ከፔላጊዮሳውያን በመውሰድ የመከራከሪያ መታወቂያቸው ነበር። የሉትራን ነገረ መለኮት የመሰረተው እና የተዋቀረው የዚህን መነሻና ልምምድ ለመቃወም በሚል ነው።

ነገረ መለኮት (Theology)

05 Aug, 15:47


👉በዘመነ ሊቃውንት የነበሩ አስተሳሰቦች👈
⭐️1.እውነታዊነት(Realism) እና በአእምሮ መተማመን(Nominalism)

በእውነታዊነት እና በአእምሮ መተማመን መካከል ያለው ግንኙነት መረዳት በመካከለኛው ዘመን የነበረውን የነገረ መለኮት ትንታኔ እንደ መገንዘብ ነው። ይህም በጥልቀት በመረዳት ለማብራራት ያስችላል። በመጀመሪያው የሊቃውንት ዘመን(ከ1200-1350 ዓ.ም.) ተጽዕኖ አድርጎ የነበረው የእውነታዊነት አስተሳሰብ ሲሆን፤ በቀጣይ ባለው የሊቃውንት ዘመን(ከ1300-1500ዓ.ም.) ተጽዕኖ አድርጎ የነበረው በአእምሮ የመተማመን(nominalism) አስተሳሰብ ነበር። የሁለቱን የተለያዩ ስርዓቶች ለመመልከት ሁለት ነጫጭ ድንጋዮችን እናስብ። እውነታዊነት ዓለም አቀፍ የሆነ ግንዛቤ አለ "ንጣት" ሁለቱንም ድንጋዮች አካቶ የያዘ በማለት ሲያስረግጥ። እያንዳንዱ ሁለቱም ድንጋዮች ዓለም አቀፍ የሆነ የንጣት(whiteness) ባህሪይ አላቸው። ነጫጭ ድንጋዮቹ በጊዜና በቦታ ውስጥ ሲኖሩ፣ ዓለም አቀፉ ንጣት(whiteness) የሚገኘው በተለየ ዲበ አካላዊ(metaphysical) ስፍራ ነው። በአእምሮ የመተማመን(nominalism) አስተሳሰብ ግን ይህ ዓለም አቀፉ "የንጣት(whiteness)" እሳቤ አላስፈላጊ ነው ይላል፣ በምትኩ ትኩረት ሊደረግ እና ሊወራ የሚገባው ባሉት ሁለቱ ድንጋዮች ላይ እንጂ ስለ ዓለም አቀፍ የንጣት ሀሳብ ላይ ልንነጋገር አይገባም በማለት ይከራከራሉ።

ነገረ መለኮት (Theology)

03 Aug, 09:22


👉ዘመነ ሊቃውንት የቀጠለ...👈
እንደ ሌሎቹ አስፈላጊ ባህላዊ ስያሜዎች  "ሂውማኒዝም" እና "ዘመነ አብርሆት(Enlightenment)" ዘመነ ሊቃውንትም ወጥ የሆነ ትርጓሜን ለመስጠት አስቸጋሪ ነው። ይህ አተረጓጎም ሊረዳ ይችላል "የዘመነ ሊቃውንት ዘመን በመካከለኛው ዘመን የነበረ እንቅስቃሴ ሲሆን፤ የተስፋፋውም ከ1200-1500 ዓ.ም. ነው። ለኃይማኖታዊ እምነቶች እና ለእምነቶቹ ስልታዊ የሆኑ አቀራረቦችን ምክንያታዊ በሆነ መንገድ አጽንዖት በመስጠት ይቀመጥ የነበረበት ዘመን ነበር። "የዘመን ሊቃውንት(Scholasticism) ግልጽ የሆነ የእምነት ስርዓትን የሚያመለክት አይደለም፣ ነገር ግን በተለየ መንገድ እና በተቀናጀ መልኩ የነገረ መለኮት ትንታኔን የተሰጠበትን ጊዜ የሚያመለክት ነው። ይህም ቁሳዊ በሆኑ ስራዎች ግልጽ አድርጎ የነገረ መለኮት አጠቃላይ ስራዎችን በማቅረብ በከፍተኛ ደረጃ ያደገ ዘዴን ለመጠቀም ሙከራ አድርጓል። ይህም ምናልባት  ለምን ሂውማኒስቶች እንደሚተቹት በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፤ የሊቃውንት ዘመን ምክንያታዊ ተራ ትችት ለማድረግ እየጣረ ያሽቆለቆለ ዘመን ይመስላል።
ምንም ይሁን ግን የሊቃውንት ዘመን በክርስቲያናዊ ነገረ መለኮት ውስጥ ሊቆጠሩ የሚችሉ ቁልፍ ነገሮች ላይ ዋና የሆነ አስተዋጽዖ እንዳደረገ ሙግቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ በተለይም የምክንያት እና የሎጂክ ሚና በነገረ መለኮት ውስጥ ያለውን ግንኙነት በተመለከተ የተደረጉ ውይይቶችን ማንሳት ይቻላል። የቶማስ አኳይነስ፣ የደንስ ስኮተስ እና የኦክልሀሙ ዊሊያም ጽሑፎች በአብዛኛው በዘመነ ሊቃውንት ዘመን ከነበሩ ጸሀፊያኖች ሶስቱ በነገረ መለኮት ጉዳዮች ላይ ትልቅ የሆነ አስተውጽኦን ያበረከቱ እና በየትኛውም ዘመን የሚያገለግሉ ጎልተው የሚታዩ ተጽዕኖ  ፈጣሪ ጸሀፊዎች ናቸው።

ነገረ መለኮት (Theology)

03 Aug, 08:10


👉ዘመነ ሊቃውንት(Scholasticism)👈
የዘመነ ሊቃውንት ዘመን ምናልባት በሰው ልጅ ታሪክ ከተናቁ የአእምሯዊ እውቀት(የምሁራን) እንቅስቃሴዎች ውስጥ አንዱ ነው። ቃሉ የተገኘው ከታላቁ የመካከለኛው ዘመን ስኮሌ(scholae) (school ወይም ትምህርት ቤት) ከሚል ቃል ነው፣ የነገረ መለኮት እና የፍልስፍና ጥያቄዎች ሙግት የሚደረግበት፣ በአብዛኛው ውስብስብ የሆነና በኋላ የመጡ የታሪክ ሙሁራንን የሚያስደንቅ እና አስደሳች የሆነ ጊዜ ነው። የእንግሊዝኛው ቃል "dunce"(fool(ሞኝ፣ቂል) የሚለው ቃል የመጣው በዘመነ ሊቃውንት ዘመን አንዱ ታላቅ ጸሐፊ ተብሎ ከሚጠራው ደንስ ስኮተስ ነው። የዘመነ ሊቃውን ሀሳባውያን "የትምህርት ሰው" የሚባሉት በቅንነት የሚሞግቱ ናቸው። ዓላማ የሌለውና ትርጉም አልባ የሆነ ክርክር ያደርጉ የነበረ ሲሆን፤ ለምሳሌ "በአንድ የመርፌ አናት ላይ ምን ያህል መላዕክቶች ይደንሳሉ?" የሚል ነበር። ቢሆንም ይህ ልዩ የሆነ ሙግት በእውነቱ ስፍራውን አልወሰደውም ነበር፤ የዚህ ማራኪ ሀሳብ ውጤት የማያጠያይቅ ነበር፣ ሀሳቡ ትክክለኛ እንደሆነ ይጠቃለል የነበረው በዘመነ ሊቃውን አብላጫ ድምጽ በነበረው ሕዝብ ነው። በተለይ ሂውማኒስቶች ስለዚህ ዘመን እንደሚሉት በ16ኛው ክፍለ ዘመን ጅማሬ ላይ እየበዙ የሄዱት ደረቅ የሆነ የአእምሯዊ እውቀት ትንበያዎች ላይ አላስፈላጊ ትንታኔዎች ይሰጡ ነበር።
የሮተርዳሙ ኢራስመስ በ15ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ጥቂት የትምህርት መንፈቅ ጊዜያቶችን(semesters) በፓሪስ ዩኒቨርስቲ ዘመነ ሊቃውንት ተጽዕኖ በፈጠረበት ጊዜ በዚያ አሳልፏል። በጽሁፎቹ ውስጥም ረዘም ባለ እና ብዙ በፓሪስ የጠላቸውን ነገሮች አስፍሯል፣ስለ ምግቡ አለመመቸት፣ ስለሚሸት ሽንት ቤት፣ እና ፍጹም አሰልቺ ስለሆነው ሙግት በተማሪዎቹ(schoolmen) መበሳጨቱን ተናግሯል። "እግዚአብሔር ሰው በመሆን ፈንታ ዱባ መሆን ይችላል? እግዚአብሔር ሴተኛ አዳሪዎችን እንደገና ደናግል እንዲሆኑ ማድረግ ይችላል? የሚሉ ጥያቄያዊ ሙግቶች ነበሩ። ቢሆንም ጠንካራ ጥያቄዎችን ከበስተጀርባው የያዙ ሙግቶች ነበሩ፣ ኢራስመስ ግልፍተኛ የሆነ ወግ ወይም ቀልድን በመጠቀም እነዚህን ጥያቄዎች በራሳቸው ከንቱ እና የሚያጃጅል በሆነ መንገድ ይከራከሩ የነበሩትን ትኩረት ለወጠው።
ይህ ዘመነ ሊቃውንት(Scholasticism) የሚለው ቃል በሂውማኒስት ጸሀፊዎች የተገኘ እንደሆነ ክርክር ይደረግበታል፣ ይህም ቃሉ የሚያመለክተውን እንቅስቃሴ ቦታ ካለመስጠት ያለ ጭንቀት ነው። ስኮላስቲክ የሚለውን ቃል ሂውማኒስቶች የሚጠቀሙት ልክ የመካከለኛውን ዘመን በማኮሰስ እንደሚመለከቱት ነው። የእነርሱ ዓላማየመካከለኛውን ዘመን ዋጋ ከማሳጣትና በግሪኮ ሮማ ዘመን ትኩረታቸውን ለመጨመር ነው። ሂውማኒስቶች በጥቂት የዘመነ ሊቃውንት ዘመን በነበሩ አስተሳሰቦች ፍላጎት አላቸው፣ በቶሚስቶች(በቶማስ አኳይነስ አስተሳሰብ) እና ስኮቲስቶች(በደንስ ስኮተስ አመለካከት)። የዘመነ ሊቃውንት ዘመን(Scholasticism) የሚለው ቃል ትችት ያለበት እና በትክክል ያልተነገረ እና ያልተጻፈ ነገር ግን የታሪክ ምሁራን ቃሉን መጠቀም ማስወገድ የማይችሉት ቃል ነው።

ነገረ መለኮት (Theology)

02 Aug, 17:37


👉የዳግም ልደት ዘመን የቀጠለ...👈
የጣልያን የዳግም ልደት ዘመን(Renaissance) የጥንት ቅርሶችንና ባህላዊ ሀብቶችን የመመለስ እንቅስቃሴ ማዕከላዊ አካል እንደነበር ግልጽ ነው፤ እንዲሁም በመካከለኛው ዘመን የነበረውን የአእምሯዊ እውቀት የስራ ክንውን ውጤቶችን አጠቃሎ መያዝ ነበር። በዳግም ልደት ዘመን የነበሩ ጸሐፊያኖች ከቀድሞ ጸሀፊያኖች ጋር ሲነጻጸሩ የበለጠ አስፈላጊ እና ጠቃሚ እንዲሁም ትልቅ ውጤታማን ስራን በመስራት ያነሱ ነበሩ። በአጠቃላይ እውነተኛ ባህል ምን ነበረ ሲባል እውነተኛ ነገረ መለኮት ነበር የሚል ትርጓሜ ነበራቸው፤ የመጨረሻው የግሪኮ ሮማ ዘመን የነበሩ ጽሑፎች የመካከለኛው ዘመን የነገረ መለኮት ጽሁፎችን አደብዝዟል ይላሉ፤ ይህም በፍሬ ሀሳቡና(substance) በዘዴ(style) ነው። በእርግጥ የአብርሆት ዘመን የሰሜናዊው የአውሮፓውያን ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የነበሩት የስነ ጥበብና የነገረ መለኮት ትምህርት ዘርፎች የአቀራረብ አይነቶች መጨመርን የሚቃወም አይነት ተደርጎ ይታይ ነበር። በሊቃውንት ሙያዊ ተፈጥሯዊ ቋንቋዎች እና ውይይቶች በመናደድ የዳግም ልደት ዘመን ጸሀፊያን በሁሉም ነገር አልፈዋቸዋል ወይም እንደማጣቀሻ አልተጠቀሟቸውም። በክርስቲያናዊ ነገረ መለኮት ጉዳይ ላይ ቁልፉ በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ መልዕክት ጋር በመገናኘት እና የቤተክርስቲያን አባቶች ዘመን የተጻፉ ጽሑፎች ላይ ትኩረት ማድረግ ነበር።

ነገረ መለኮት (Theology)

01 Aug, 12:53


👉የዳግም ልደት ዘመን👈
የፈረንሳይ ቃል የሆነው "Renaissance"(የዳግም ልደት ዘመን) በዓለም አቀፍ ደረጃ በአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመንና በአስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረውን የስነ ጽሁፍና የስነ ጥበብ(art) ማንሰራራትን ለማመልከት ጥቅም ላይ የዋለ ቃል ነው። በ1546 ዓ.ም. ፓኦሎ ጊዮቪዮ ስለ አስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን እንደሚናገረው "ይህ አስደሳች ክፍለ ዘመን የላቲን ፊደላቶች እንደ አዲስ የተወለዱበት ነው" ብሎ በማሰብ ይህን ሙያዊ ቃል ሰይሞታል። አንዳንድ የታሪክ ምሁራን፣ እንደ ጃኮብ ቡርካርድት በአብዛኛው እንደሚከራከሩት የአብርሆት ዘመን የዘመናዊነትን ዘመን ወልዷል ይላሉ። ቡርካርድት እንደሚለው በዚህ ዘመን ነው ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ግለኛ የሆነ አስተሳሰብን ማሰብ የጀመሩት ይላል። በተለያየ መንገድ የቡርካርድት ስለ ዳግም ልደት ዘመን ያለው አተረጓጎምና ፍቺ እና ስለ ግለኝነት ስያሜዎች የተናገረው በከፍተኛ ደረጃ አጠያያቂ ነው። ነገር ግን በሌላ አቅጣጫ ደግሞ የሰጠው ትርጓሜ በማያጠያይቅ መልኩ ትክክል ነው፣ አዳዲስ ነገሮችና አስደሳች ነገሮች በዳግም ልደት ዘመን በጣሊያን መበልጸግ የጀመሩበት ጊዜ ነው፣ ይህም ብዙ አሳቢ ትውልዶችን የሚማርኩ ነገሮች መስራት እንደተቻለ የተረጋገጠበት ነው።
1. የነገረ መለኮት ሊቃውንት(Scholastic theology):- በመካከለኛው ዘመን የነበረው ዋና የአእምሯዊ እውቀት ተጽዕኖ በጣልያን ብቻ አልነበረም። ጣሊያናዊ የሆኑ የነገረ መለኮት ሊቃውንትም ታዋቂነትን ያገኙ ነበሩ(ቶማስ አኳይነስ እና የሪሚኒው ጎርጎሪዮስ)፣ የኖሩትና የሰሩትም በሰሜናዊው የአውሮፓ ክፍል ነበር። በአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን በጣሊያን ትልቅ የእውቀት ጉድለት የነበረበት ጊዜ ነበር። ጉድለቱ የሞላበት እና የዳግም ልደት ዘመን የሂውማኒዝም እንቅስቃሴ ስፍራውን ሲይዝ የነበረውን ክፍተት ተቆጣጠረው።
2.ጣሊያን ታላላቅ በሆኑ በጥንት ቅርሶችና መሳሪያዎች በግልጽ እና ሊዳሰስ በሚችል መልኩ ተሞልታ ነበር። የጥንት የሮም ህንጻዎችና ሀውልቶች ቅሪት በምድሪቱ ላይ ተበታትኖ ነበር። በዳግም ልደት ዘመን የጥንት የሮም ስልጣኔን የመፈለግ አዝማሚያ መታየት ጀመረ። በዚህ ባህላዊ ድርቀት እና ባህላዊ ባዶነት በሆነበት ዘመን የግሪኮ ሮማን ባህል እንደ አዲስ ሕያው ለማድረግ የሚገፋፋ የአስተሳሰብ ድርጊቶች መከወን ጀመሩ።

3.የቤዛንታይን እንቅስቃሴ እየወደቀ ሲመጣ፣ በ1453 ዓ.ም. ቁስጥንጥንያ ወደቀች፤ በዚህ ጊዜ  ለግሪክ ተናጋሪ ሊቃውንቶች በምዕራብ ዘጸዓት ወይም መውጣት ሆኖላቸው ነበር። ጣሊያን ለቁስጥንጥንያ ምቹ ባልሆነ መንገድ ዝግ ሆና የነበረ ሲሆን፣ ከስደቱ በኋላ ግን ብዙ ስደተኞች ተረጋግተው በጣሊያን ከተሞች መቀመጥ ቻሉ። የግሪክ ቋንቋ በማይቀር መልኩ እንደ አዲስ እንደገና ማንሰራራት ጀመረ፣ ይህ እንደገና የጀመረው ማንሰራራት ትኩረቱና ፍላጎቱ የጥንት የግሪክ ስነጽሁፍን መሰረት ያደረገ ነበር።

ነገረ መለኮት (Theology)

30 Jul, 17:12


👉የመካከለኛው ዘመን...የቀጠለ👈
የጨለማው ዘመን የሚለው መጠሪያ  "የመካከለኛው ዘመን" በሚለው መጠሪያ ከምዕራብ አውሮፓ ተወገደ፣ የመካከለኛው ዘመን ውልደት እንደ አዲስ በተለያዩ ዘርፎች በትምህርታዊ ስራዎች መነቃቃቶች የነበሩበት ነበር። በ11ኛው ክፍለ ዘመን በፈረንሳይ የነበረው የፓለቲካዊ ተሀድሶ መረጋጋት የፓሪስ ዩኒቨርሲቲ  በአውሮፓውያን ዘንድ የእውቀት ማዕከል በመሆን እንዲታወቅ ሆነ። ብዙ የነገረ መለኮት ትምህርት ቤቶች በሴይኔ በሚገኘው በሌፍት ባንክ ተመሰረቱ፣ እንዲሁም በ ኢሌ ዴ ላ ሳይት ተመሰረተ።
ከነዚህ ውስጥ አንዱ የሆነው የሶርቦኔ ኮሌጅ ሲሆን፤ ከፓሪስ ዩኒቨርስቲ ጋር ተዛማች የሆነ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ውጤታማ እና ታዋቂነትን ያተረፈ ነው። በ16ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ሳይቀር የፓሪስ ዩኒቨርስቲ ትልቅ ተቀባይነትን ያገኘ የነገረ መለኮት ጥናት እና የፍልስፍና ጥናቶች ማዕከል ነበር። በዚህ ከተማሩ ታዋቂ ሊቃውንት መካከል የሮተርዳሙ ኢራሲመስ እና ጆን ካልቪን ናቸው። ሌሎች የጥናት ማዕከላቶች በጥቂት ጊዜያቶች ውስጥ  በአውሮፓ ውስጥ መቋቋም ጀመሩ። አዲስ የሆነ የነገረ መለኮት እድገት ጥናት  ጀመረ፣ ይህም የክርስቲያን ሕይወትን በቤተክርስቲያን በተመለከተ አእምሯዊ እውቀትን፣ ህጋዊነትን እና መንፈሳዊነትን ለማዳበርና ለማጠናከር የሚደረግ ጥናት ነበር።
የቅድመ መካከለኛው ዘመን በፈረንሳይ በነበረው ዕድገት ተጽዕኖ ስር የነበረ ሲሆን፤ ብዙ ገዳማቶች እና ትልልቅ ተጽዕኖ ፈጣሪ የክርስቲያን ጸሐፊያኖች እና አሳቢዎች የፈሩበት ዘመን ነው። ለምሳሌ ላንፍራንክ(1010-1089 ዓ.ም.) እና አንሰልም(1033-1109 ዓ.ም.) ሁለቱም  በኖርማንዲይ ቤክ ገዳም ነበሩ። የፓሪስ ዩኒቨርሲቲ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ የነገረ መለኮታዊ መላምት ማዕከል ተደርጎ ተቋቋመ፣ ሊቃውንት ከነበሩት ውስጥ እነ ፒተር አበላርድ(1079-1142 ዓ.ም.)፣ ታላቁ አልበርት(1200-1280 ዓ.ም.)፣ ቶማስ አኳይነስ(1225-1274 ዓ.ም.) እና ቦናቬንቹራ(1217-1274 ዓ.ም.) ናቸው። በአስራ አራተኛው እና አስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን ብዙ ዩኒቨርስቲዎች በምዕራብ አውሮፓ እየተስፋፉ ሲሄዱ፣ በተጨማሪም በጀርመን ከተማ አዳዲስ ዋና ዩኒቨርሲቲዎች ተቋቋሙ።
በመካከለኛው ዘመን የነበረው የነገረ መለኮት የሀብት ማዕከል ፍላጎት ከ ፓሪስ ጋር የተያያዘ ነበረ። በጥቂት ጊዜ ውስጥ ከ1140 ዓ.ም. በፊት ፒተር ሎምባርድ በዩኒቨርስቲው ለማስተማር ተቀላቀለ። የእርሱ ዋነኛ ፍላጎት የነበረውም ተማሪዎቹ  አሻሚና አከራካሪ የሆኑ የነገረ መለኮት ጥናቶችን እንዲታገሉ ነበር። አንዱ እርሱ አስተዋጽዖ ያደረገው መጽሐፍ ሲሆን፣ እስከዛሬ ከተጻፉ መጽሐፍቶች ሁሉ አሰልቺ  የሆነ መጽሐፍ ነው። "የአረፍተ ነገሮቹ አራት መጽሐፍት" በአንድ ላይ የመጽሐፍ ቅዱስ እና የቤተክርስቲያን አባቶች የጽሑፍ ማጣቀሻዎች ያሉት ርዕሳዊ በሆነ መልኩ የተደራጀ መጽሐፍ ነው። ፒተር ለማያስተምራቸው ተማሪዎች የሚሰጣቸው ስራ ቀለል ያለና ማጣቀሻዎቹ ተገቢ የሆኑ ነበሩ። መጽሐፉ የአውግስጢኒያዊ አስተምህሮን  መስፋፋት ያለውን አስፈላጊነት በዋነኝነት የሚያረጋግጥ ሲሆን፤ ተማሪዎች የግድ የአውግስቲን ትምህርቶችን ቅርስነት በመቀበል   እና በግልጽ የሚቃረኑ ጽሑፎችን እንዲሁም ተለዋዋጭ የነገረ መለኮታዊ ትንታኔዎችን ፈጠራ በታከለበት መልኩ በማስታረቅ ተስማሚ የሆነ ትንታኔዎችን እንዲሰጡና እንዲታገሉ ያስገድዳቸው ነበር።
ጥቂት ጸሀፊያኖች መጽሐፉን ዋና መመሪያቸው ለማድረግ ሞክረዋል። አልፍ አልፎ ጥንቃቄ ባልተደረገበት በችኮላ በተጻፈ ዓረፍተ ነገሮች ተጠቅመዋል።( ለምሳሌ እንደ ክርስቶስ አካላዊ አካላዊ ሆኖ አልኖረም የሚል ሲሆን፣ ይህ ምልከታ ከጥቂት ጊዜ በኋላ "Christological nihilism" (ነገረ ክርስቶስ ምንም ጥሩ ነገር የለውም የሚል እምነት) በመባል ታወቀ)። ቢሆንም በ1215 ዓ.ም. እጅግ በጣም አስፈላጊ የዘመኑ ድንቅ መጽሐፍ ተብሎ ነበር። ይህም መጽሐፍ የነገረ መለኮት ተማሪዎች የሎምባርድን ነገረ መለኮታዊ ጥናት እና ሀተታዎች ለማጥናት የግድ የሚጠቀሙት መጽሐፍ ነበር። የጽሑፎቹም ውጤት "የዓረፍተ ነገሮቹ ማብራሪያዎች" በመባል የታወቀ ሲሆን፣ በመካከለኛው ዘመን ከነበሩ የነገረ መለኮት ጽሑፎች ጋር የሚመደብ ነው። በዚህ ዘመን በጣም አስደናቂ ጽሑፎች  ከጻፉት ውስጥ ለምሳሌነት የሚካተቱት ቶማስ አኳይነስ፣ ቦናቬንቹራ እና ደንስ ስኮተስ ናቸው።

ነገረ መለኮት (Theology)

30 Jul, 10:00


👉የስያሜዎች ማብራሪያ👈
ዘመናቶችን በታሪክ ውስጥ ለማስረዳት በከባድ ሁኔታ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ነገር ነው። የችግሮቹ አካል የሆነው  አንዱ የየዘመናቶቹ መለያ ባህሪያቶች ዓለም አቀፍ የሆነ ስምምነት አለመኖሩ ነው። ይህ በተለይ የመካከለኛው ዘመን፣ የአብርሆት ዘመን እና የዘመናዊነት ዘመን ነው።በተጨማሪም ዋና እና ለማስረዳት አስቸጋሪ ከሆነ ዘመን ውስጥ የአእምሯዊ እውቀት እንቅስቃሴ ሲሆን፣ በተለይም ሰውን ማዕከል ያደረገ(humanism) እንቅስቃሴ ነው።
ከ1300-1500 ዓ.ም. የዘመነ ሊቃውንት(Scholasticism) እና የሂውማኒዝም እንቅስቃሴ የእውቀት ዓለምንና የነገረ መለኮት ዓለምን ተጽዕኖ አድርገውበት ነበር። ቢሆንም የዘመነ ሊቃውንት ዘመን በ1500 ዓ.ም. ላይ እየተዳከመ መሄዱ ላይ ክርክሮች አሉ። አሁንም ድረስ በብዙ የአውሮፓውያን ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ትልቅ ተጽዕኖ አለው፣ለምሳሌ እንደ ፓሪስ ዩኒቨርስቲ..። የእነዚህን ሁለት እንቅስቃሴዎች ተፈጥሮን ወይም ምንነትን በዚህ ዘመን ውስጥ መረዳት የክርስትና የነገረ መለኮት እድገት ላይ በጣም አስፈላጊ የሆነ ሙከራን አድርጓል። ኃይማኖታዊውን እና የአእምሯዊ እውቀት ግፊት መጨመር በስተመጨረሻ የተሀድሶ መነሳት ምክንያት እንዲሆን አድርጓል። ለባህላዊ ድህነት  ምላሽ ለመስጠት እና በቀድሞ የነገረ መለኮት ትክክለኛነት ላይ ምላሽ በመስጠት ሁለቱ እንቅስቃሴዎች ተጎዳኝተው እንደነበር በኋላ ላይ ይታሰቡ ነበር።
⭐️1.የመካከለኛው ዘመን:-
"የመካከለኛው ዘመን" የሚለው ስያሜ የተሰጠው በዘመነ አብርሆት በነበሩ ጸሀፊያኖች ሲሆን፣ በ16ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ስያሜው በአጠቃላይ ጥቅም ላይ ውሎ ነበር። በአብርሆት ዘመን የነበሩ ጸሀፊያኖች በግሪኮ ሮማ ዘመን የነበረውን ክብርና በእነርሱ በነበሩበት ዘመን መካከል ላይ ጣልቃ ገብቶ የነበረውን ዘመን ዋጋ ላለመስጠት እጅግ ተጨንቀው ነበር። በዚህም ምክንያት "የመካከለኛው ዘመን" የሚለውን ስያሜ በሁለቱ አስፈላጊ እና በብዙ ፈጠራ የተሞላውን ዘመን የለያየ ደስ የማያሰኝና በነገሮች ሁሉ የተገደበውን ዘመን ለመጥራት ተጠቀሙበት። "የመካከለኛው የነገረ መለኮት ዘመን" የሚለው ስያሜ እንደ አጠቃላይ ጥቅም ላይ ይውል የነበረው በጨለማው ዘመን መገባደጃ እና በ16ኛው ክፍለ ዘመን መካከል የነበረውን የምዕራብ አውሮፓውያንን ነገረ መለኮት ለማመልከት ነው። ቢሆንም ይህ ስያሜ ጎልቶ ጥቅም ላይ ቢውልም እንከን ያለበት፣ አከራካሪ እና ለተለያዩ አተረጓጎሞች ክፍት የሆነ ነው።

ነገረ መለኮት (Theology)

30 Jul, 06:49


👉የመካከለኛው ዘመን እና የዳግም ልደት(Renaissance) ዘመን(1050-1500 ዓ.ም. 👈የቀጠለ...
በቤተክርስቲያን ታሪከሰ መሰረታዊና አስፈላጊ የሆነው ክስተት የተከናወነው በዚህ ዘመን ነበር። በተለያዩ ምክንያቶች በዘጠነኛው እና በአስረኛው ክፍለ ዘመን በቁስጥንጥንያ መሰረት አድርጎ የነበረው የምስራቅ ቤተክርስቲያን እና በሮም መሰረት አድርጎ የነበረው የምዕራብ ቤተክርስቲያን ግንኙነት ውጥረት እየጨመረ ሄደ። በተለይም በኒቂያ በተደረገ የመንፈስ ቅዱስን ከአብና ከወለድ የመስረጽ(የመላክ(filioque))አንቀጽ ምክንያት አለመስማማት በመከናወኑ ክፍፍሉ እያደገ እንዲሄድና እርስ በእርስ መቀባበል እንዳይኖር ምክንያት ሆነ። ሌሎች ምክንያቶችም ለመከፋፈሉ አስተዋጽዖ ያደረጉ ሲሆን፣ ፓለቲካዊ ፉክክሮች የላቲን ቋንቋ ተናጋሪ በሆኑ በሮም በሚገኙ እና የግሪክ ቋንቋ በሚናገሩ የቁስጥንጥንያ ቤተክርስቲያናት ዘንድ በተለይም የሮም ቤተክርስቲያን የጵጵስና ስልጣን ይበልጣል የሚለው የይገባኛል እወጃ ለመከፋፈሉ ምክንያት ከነበረው ውስጥ አንዱ ነበር። የመጨረሻው ግልጽ የሆነ መከፋፈል በምዕራብ ካቶሊክ ቤተክርስቲያንና በምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተከናወነው በ1054 ዓ.ም. ነው።
አንዱና ዋነኛው በምስራቅ እና በምዕራብ ውጥረት እንዲከሰት ያደረገው ጥቂት የነገረ መለኮት ክርክር ነበር። የምዕራብ የነገረ መለኮት ተንታኞች የሆኑት እንደነ ቶማስ አኳይነስ አይነቶቹ ነጻ በሆነ ስሜት እና ሁኔታ የግሪክ አባቶች ጽሑፎችን የመጠቀም አዝማሚያ አሳይተው ነበር። እንዲሁ በኋላ የመጡት የኦርቶዶክስ የነገረ መለኮት ተንታኞች እንደነ ጎርጎርዮስ ፓላማስ በምዕራባውያን ጽሑፎች በመሳብ ጥቂት ሀሳቦችን ጠቅሰዋል። በሀያኛው ክፍለ ዘመን ብቻ ነው የምዕራብ የነገረ መለኮት ተንታኞች እንደ አዲስ የኦርቶዶክስ ባህል ውስጥ ያሉ ሀብቶችን በማጥናትና የተለያዩ ሀሳቦችን ማጣቀስ የጀመሩት።
"የመካከለኛው ነገረ መለኮት" የሚለው ስያሜ በአብዛኛው የሚያመለክተው በዚህ ዘመን የነበረውን የምዕራባውያን የነገረ መለኮት ትንታኔ ሲሆን፣ "የቤዛንታይን ነገረ መለኮት" የሚለው ስያሜ በዚያው ዘመን የነበረውን የምስራቅ አብያተክርስቲያናት የነገረ መለኮት አስተሳሰብነው። በዚህ ጊዜ የምዕራብ አውሮፓውያን ታሪክ የክርስቲያን ነገረ መለኮት ወደ ሰሜን የተዘዋወረበትና በፈንሳይና በጀርመን ውስጥ ማዕከል ያደረገበት ጊዜ ነበር። በተጨማሪም የሮም ከተማ የክርስቲያን የኃይል ማዕከል እንደሆነች ቀጥሎ ነበር። አእምሯዊ የሆኑ ስራዎች ግን ይከናወኑ የነበሩት በፈንሳይ ገዳማት ውስጥ ነበር፤ ለምሳሌ እንደነ ቻርትረስ፣ ሬይምስ እና ቤክ። በመካከለኛው ዘመን በተመሰረቱ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የነገረ መለኮት ጥናቶች በስፋት በመጠናት ከፍተኛ የቀለም ትምህርት ማዕከሎች ሆኑ። በመካከለኛው ዘመን የነበሩ ዩኒቨርስቲዎች በዋነኝነት አራት የትምህርት ጥናቶች ይከናወንባቸው የነበረ ሲሆን፤ ስነ ጥበብ(art) የዝቅተኛው የትምህርት ጥናት ክፍል ሲሆን፣ የከፍተኛው የትምህርት ጥናት ክፍል የነበሩት ነገረ መለኮት፣ የሕክምና(medicine) እና የሕግ ትምህርቶች ነበሩ።

ነገረ መለኮት (Theology)

29 Jul, 06:06


👉የመካከለኛው ዘመን እና የዳግም ልደት(Renaissance) ዘመን(1050-1500 ዓ.ም.)👈
የቤተክርስቲያን አባቶች ዘመን ማዕከል ያደረገው በሜዲትራኒያን አካባቢ ሲሆን፣ የወንበር ስልጣኑ ደግሞ በሮም እና ቁስጥንጥንያ ከተማ ነበር። የሮም ውድቀት  በኃያል ወራሪዎች ከሰሜን ወደ ምዕራብ የሜዲትራኒያን አካባቢ መደናገርን እና ውዝግብን አመጣ። ይህ አለመረጋጋት በአካባቢው ላይ ተዛመተ። የታሪክ ተመራማሪዎች የጨለማው ዘመንን ከሮም ውድቀት ጀምሮ እስከ 1000 ዓመት ድረስ ነው ብለው ይጠቅሳሉ። ይህም በነዚህ ክፍለ ዘመናት ውስጥ ባህል እና ትምህርት በአንጻራዊነት ያልተረጋጋበት እና የማያስተማምንበት እንደነበረ ለማመልከት ነው። በዚህ ዘመን ውስጥ በተጨማሪ በምዕራብ አብያተክርስቲያናት ዘንድ የነገረ መለኮታዊ ሀሳቦች ወይይት ቀጥሎ ነበር፣ ይህም በስህተት አስተምህሮቶች ዙሪያ የነበሩ ርዝራዥ አመለካከቶችን በመቃወም አውድ የተደረገ ነበር። በአንጻራዊነት ጥቂት የሕብረተሰብን ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ ነገረ መለኮታዊ ሙግቶች ነበሩ። በምስራቅ ሜዲትራኒያን የነበረው አለመረጋጋት የእስልምና እምነት መጀመርና በአካባቢው ሁሉ እምነቱ እየተስፋፋ ሄደ። በአካባቢው ክርስትና ሙሉ በሙሉ በእስልምና ያልተተካ ቢሆንም  ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ግን በቁጥር አናሳ የሆነ ኃይማኖት ሆነ።
በአውሮፓውያን ታሪክ ውስጥ በዚህ ዘመን የክርስትና ነገረ መለኮት ማዕከል ከሜዲትራኒያን አካባቢ ወደ ምዕራብ አውሮፓ ተለወጠ። በ410 ዓ.ም. የሮም ግዛት በአላሪክ ተያዘ፤ ይህም ዘመን በአብዛኛው በምዕራብ አውሮፓ የጨለማው ዘመን የጀመረበት ጊዜ እንደሆነ የሚቆጠርበት ነው። በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በሜዲትራኒያን አካባቢ የእስልምና  መስፋፋት ፓለቲካዊ የሆኑ ለውጦች እና መዋቅራዊ ለውጦች መሆን ጀመሩ። በ11ኛው ክፍለ ዘመን እስልምና በአካባቢው በተመቻቸ ሁኔታ በመጽናት ስፍራውን ተቆጣጠረ። ሶስት ዋና ዋና ኃያል ቡድኖች የጥንቱን የሮም አገዛዝን ለመያዝና ለመቆጣጠር ብቅ አሉ።
1.ቤዛንታይን:- ማዕከል ያደረጉት በቁስጥንጥኒያ ከተማ ሲሆን( በቱርክ ከተማ የሚገኘው የአሁኑ ኢሳታንቡል)። የክርስትና እምነት አመሰራረትና በአካባቢው ተጽዕኖ አሳድሮ የነበረው በግሪክኛ ቋንቋ እና በጥልቀት ስር የሰደደው በምስራቅ ሜዲትራኒያን የቤተክርስቲያን አባቶች እና ምሁራን በተጻፉ ጽሁፎች ነው። ለምሳሌ እንደ አትናቴዎስ የቀጰዶቅያው፣ የደማስቆው ዮሐንስ.. ናቸው።

2.ምዕራብ አውሮፓ:- ዋና ከተሞች የሆኑት የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ ዝቅተኛ ከተማዎችና የሰሜን ጣሊያን ናቸው። የክርስትና እምነት አመሰራረት እና ተጽዕኖ የፈጠረው የሮምን ከተማ ማዕከል በማድረግ ነበር። በዚያ የነበሩ የቤተክርስቲያን መሪዎች ጳጳስ(Pope) ይባሉ ነበር።(ቢሆንም ይህ ዘመን "ታላቁ መከፋፈል" በመባል የሚታወቅበት ዘመንና ጥቂት አወዛጋቢ የሆኑ ነገሮች የተገለጡበት ነው፤ ዋና ጳጳስ ለመሆን ይደረግ የነበረ የይገባኛል ፉክክር ሲሆን አንደኛው መሰረት ያደረገው በሮም ሲሆን ሌላኛው በደቡብ የፈረንሳይ ከተማ አቪኞን ነው)። የነገረ መለኮት ስራዎች በታላላቅ ካቴድራሎች እና በዩኒቨርስቲ እና በፈረንሳይ ትምህርት ቤቶች  መከማቸት ጀመሩ፤ በአብዛኛው የጽሑፍ ስብስቦች መሰረት ያደረጉት በላቲን ቋንቋ በተጻፉ ጽሑፎች ሲሆን የአውግስቲን፣ የአምብሮስ እና የጦርነት ጽሑፎች ናቸው።
3. የካሊፍ እንቅስቃሴ:- በምስራቅና በምዕራብ የሜዲትራኒያንን አካባቢ በቁጥጥር ስር በማዋል እስላማዊ የሆነ አገዛዝ መያዝ ጀመረ። እስከ 1453 ዓ.ም. የቁስጥንጥንያ ከተማ መውደቅ ድረስ እስልምና በኃይል እየተስፋፋ የቀጠለ ሲሆን፣ ይህም ትልቅ የሆነ ነውጥን በአውሮፓ አስከትሏል። በ15ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ እስልምና በአውሮፓ አህጉር ውስጥ በሁለት ስፍራዎች ላይ አስፈላጊ የሆነ ምስረታዎችን አደረገ፤ ይህም በስፔይን እና በተከፋፈሉ ትናንሽ መንግስታት ነበር። ይሄ የእስልምና በስፔይን ውስጥ መስፋፋት በመጨረሻም ሙርስ በተባሉ የስፔይን ጎሳዎች ድል አድራጊነት በ15ኛው ክፍለ ዘመን መጠናቀቂያ በሆነው በአስር አመት ውስጥ ተገታ። የሙስሊም ተዋጊዎችም ድል እየተደረጉ በ1523 ዓ.ም. ከቬይና ከተማ ውጭ ሆኑ።

ነገረ መለኮት (Theology)

27 Jul, 18:07


https://youtu.be/Q3dl479Lw9w?si=Hxk9Jj6tdRAB9KsG

ነገረ መለኮት (Theology)

27 Jul, 11:24


👉የጸጋ አስተምህሮ የቀጠለ...👈
አውግስቲን "ጸጋ" ሽልማት መቀበል ለማያስፈልገውና ለማይገባው ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ ውድ ስጦታ ነው ይላል። ይህም እግዚአብሔር በፈቃደኝነት በሰዎች ላይ የሰለጠነውን የኃጢአት ጉልበት የሰበረበት ነው። መዋጀት መለኮታዊ የሆነ ስጦታ ብቻ ነው። እንጂ በራሳችን ለራሳችን ልናከናውነው እና ልንፈጽመው የምንችለው ነገር አይደለም።ነገር ግን ለእኛ እግዚአብሔር ሰርቶ የፈጸመልን ነገር ነው። አውግስቲን የደኅንነት ምንጩ እና መገኛው ከሰው ማንነት ውጪ የሆነና ራሱ እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ በአጽንዖት ይናገራል።  ለሰው የደኅንነት ሂደት ሀሳቡን ያፈለቀው ራሱ እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም።
ለፔላጊየስ ግን ይህ ሁኔታ በተቃራኒው ነው። እንደ ፔላጊየስ አስተሳሰብ የደኅንነት ምንጩ እና መገኛው ሰው ጋር ነው የሚል ነው። እያንዳንዱ ሰው ራሱን የማዳን አቅም አለው ይላል። በኃጣአት አልተጠመዱም ነገር ግን ለመዳን ማድረግ የሚገባቸውን ሁሉ የማድረግ ችሎታ አላቸው ይላል። ድነት መልካምን ስራ በመስራት የሚገኝ ሲሆን፣ እግዚአብሔር የግድ ሰው በሚያደርገው ግብረገባዊ ስራ እንደ ምላሽ የሚሰጠው ነው ይላል። ፔላጊየስ ስለ ጸጋ ሀሳብ እንደጻፈው፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሰው የግድ ያደርገው ዘንድ የተሰጠውን ነገር በመፈጸም ድነትን ማግኘት እንደሚቻል ይናገራል። ይህም ለምሳሌ የአስርቱ ትዕዛዛትንና እና ግብረገባዊ የክርስቶስ ኢየሱስን ምሳሌነት መፈጸም ነው ይላል። በዚህም ምክንያት ለፔላጊያኒዝም ቡድኖች ድነት የስራ ሽልማት ሲሆን በአውግስቲን አስተሳሰብ ግን ድነት በጸጋ ነው።
እነዛህ ሁለት የነገረ መለኮት ምልከታዎች ስለ ሰው ተፈጥሮ የተለያየ አይነት ምልከታ አላቸው። ለአውግስቲን የሰው ተፈጥሮ ደካማ፣ የወደቀ እና ኃይል የሌለው ሲሆን፤ ለፔላጊየስ ግን ሰው ራስ ገዝና ለራሱ በቂ የሆነ ነው። ለአውግስቲን ሰው ለመዳን የእግዚአብሔር ማንነት ላይ የግድ መደገፍ ይገባዋል ሲል፣ ለፔላጊየስ ግን እግዚአብሔር ዝም ብሎ ሰው ድነትን ለማግኘት ማድረግ የሚገባውን የሚያመለክት እና ሰዎች ድነታቸውን ራሳቸው በማከናወን ያገኙት ዘንድ የማይረዳቸው እና የተዋቸው እንደሆነ ይናገራል። ለአውግስቲን ድነት የማይገባን ስጦታ ነው ሲል፤ ፔላጊየስ ግን ድነት ለሰራነው ስራ ምላሽ ነው ይላል።
አንዱ የአውግስቲን ስለጸጋ ያለው ግንዛቤ ትንታኔን ይፈልጋል። ሰዎች ሁሉ ራሳቸውን ለማዳን የሚችሉበት አቅም ስለሌላቸው እግዚአብሔር የጸጋ ስጦታን ለጥቂቶች ሰጠ(ለሁሉም አይደለም)። ይህም እግዚአብሔር የሚድኑትን ሰዎች አስቀድሞ መምረጡን ያመለክታል ይላል። እንዲህ አይነት ሀሳቦች በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ ዳብረው እናገኛለን በማለት አውግስቲን የቀድሞ መወሰን(መመረጥ) (predestination) አስተምህሮን አስፋፋ። የቀድሞ መወሰን(predestination) የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር ጥቂት ሰዎችን(ሁሉንም ሰው አይደለም) ለማዳን የመጀመሪያው ወይም ዘላለማዊው ውሳኔውን የሚያመለክት ነው። ይህ የአውግስቲን አመለካከት በዘመናዊዎቹ ተከታዮቹ ብዙ እንዳይጠቀስና ተቀባይነትን እንዳያገኝ ያስደረገው። ነገር ግን ይህ አመለካከት ግን በምንም አይነት መንገድ ከፔላጊየስ አስተሳሰብ ጋር እኩል ተደርጎ ሊታይ አይገባም።
በ418 ዓ.ም. የካርቴጅ ጉባኤ ጸጋን እና ኃጢአትን በተመለከተ የአውግስቲንን ትንታኔ ሲቀበሉ፣ ያለማወላወል የፔላጊያኒዝም አስተምህሮን አውግዘዋል። ይሁን እንጂ የፔላጊያኖች አስተምህሮ በተለያየ መንገድ እና ሁኔታ በቤተክርስቲያን ውስጥ ክርክርንና ጠብን በማንሳት ለጥቂት ጊዜ ቀጥለዋል። ልክ የቤተክርስቲያን አባቶች መገባደጃ ላይ፣ በምዕራብ አውሮፓውያን የጨለማው ዘመን በሆነበት ጊዜ ብዙ ክርክሮች መፍትሔ ሳይበጅላቸው ቀረ። በዚህም ምክንያት በተለያዩ የቤተክርስቲያን መካከለኛው ዘመንና በተሀድሶ ዘመን ገናና የሆኑ አከራካሪ ጉዳዮች በመሆን ቀጥለዋል።

ነገረ መለኮት (Theology)

27 Jul, 11:21


👉የጸጋ አስተምህሮ👈
ግሪክ ተናጋሪ በሆኑት የምስራቅ አብያተክርስቲያናት ዘንድ እያደገ በሄደው የነገረ መለኮት ትምህርት የጸጋ አስተምህሮ እንደ አስፈላጊ አከራካሪ ሀሳብ አልነበረም። ይሁን እንጂ በአምስተኛው ክፍለዘመን በሁለተኛው አስርት አመታት ውስጥ ጠንካራ የሆኑ አወዛጋቢ ጥያቄዎች መነሳት ጀመሩ። የእንግሊዝ መናኝ የሆነው መነኩሴ ፔላጊየስ የተባለ በሮም መሰረት ያደረገ ሰው ሲሆን፤ ጠንካራ ሙግቱ የነበረውም የሰው ግብረገብ ኃላፊነት እጅግ የሚያስፈልግ ጉዳይ እንደሆነ ነው። በተለይ በሮም ቤተክርስቲያን ቸል የተባለውን ጉዳይ እንደ ማንቂያ ደውል ሲናገር ነበር። ሰው ሕይወቱን ቋሚ በሆነ መልኩ የብሉይ ኪዳን ህግ እና የክርስቶስ ኢየሱስን ምሳሌነት ብርሀን አርጎ በመጠቀም ራሱን ሊያሳድግ ይገባል ይላል። ይህን ማድረግ ከራስ ጋር መጣላት አይነት አድርጎ የሚመለከተው የቤተክርስቲያን መሪ የነበረው አውግስቲን እንደሚለው በክርስትና ሕይወት ጅማሬና ቀጣይነት ላይ ለመለኮታዊ ጸጋ ቦታን ላለመስጠት የሚደረግ መቃወም ነው ይላል። የፔላጊያኖች አመለካከት የሰው ራስ ገዝ ነጻነት ኃይማኖት እንደሆነ ተደረጎ መታየት ጀመረ፤ ይህም ሰዎች በራሳቸው ለደኅንነታቸው የሚሆንን ነገር  ማድረግ ይችላሉ የሚል ምልከታ ነበር።
አውግስቲን የፔላጊያኖችን አስተምህሮ አጥብቆ በመቃወም ምላሽን ሰጥቷል። እርሱም በእያንዳንዱ የክርስቲያን የሕይወት ደረጃ ውስጥ የእግዚአብሔር ጸጋ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው አስፈላጊ እንደሆነ ተናግሯል። ለአውግስቲን ሰዎች ለደኅንነታቸው መነሻ የሚሆንን ነገር በነጻነት መቆጣጠር አይችሉም የሚል ነው። ሰው ነጻ የሆነ ፈቃድ አለው እንኳን ብንል የሰው ፈቃድ የተበላሸና የተበከለ ፈቃድ ነው፣ ይህም ክፋትን ለማድረግ የሚገፋፋቸው እና ከእግዚአብሔር እንዲርቁ የሚያደርግ ነው። የእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው ኃጢአትን ከማድረግ ፍላጎት ሊከላከል የሚችለው። አውግስቲን ስለ ጸጋ አጥበቆ በተሟገተበት ሀሳብ ምክንያት ከጥቂት ጊዜ በኃላ "የጸጋ ዶክተር" በሚል እንዲታወቅ አድርጎታል።
ማዕከላዊ የሆነው የአውግስቲን ሀሳብ መሰረት ያደረገው በወደቀው የሰው ተፈጥሮ ላይ ነው። የሰውን ውድቀት ከዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ላይ ካለው ሀሳብ በመውሰድ አሁን ያለው የሰው ተፈጥሮ ቀድሞ እግዚአብሔር ሲፈጥረው ሳይወድቅ በፊት እንደነበረው አይነት እንዳልሆነ ያብራራል። አሁን ያለው የሰው ተፈጥሮ(ማንነት) እግዚአብሔር አስቦ እንደፈጠረው አይነት አይደለም። በቅደም ተከተል የተፈጠሩ ፍጥረታት በሙሉ መልካምነታቸውን ይዘው ቀድሞ እንደነበረው ማንነታቸው ሊሆኑ አልቻሉም። ሁሉም ነገር ተዛብቷል። ሁሉም ነገር ተበላሽቷል ወይም ተበክሏል ነገር ግን የማይስተካከል አይነት አልሆነም፤ ይህንን የደኅንነት አስተምህሮ እና የጽድቅ አስተምህሮ ያረጋግጥልናል። መውደቅ የሚለው ቃል የተፈጠሩ ነገሮች ሁሉ እግዚአብሔር አስቦ በፈጠራቸው ልክ ሳይሆን ዝቅ ባለ ደረጃ  እየኖሩ እንዳለ የሚገልጽ ነው።
በአውግስቲን አገላለጽ  ሁሉም ሰው በተወለደ ጊዜ በኃጢአት ተበክሏል የሚል ነው። በሀያኛው ክፍለ ዘመን ከተነሱት መውደቅ የእኛ ምርጫ ነው(ለእኛ የሚመረጥ ነገር የለም) በማለት ከሚያምኑት ከኤግዚስቴንሻል ፍልስፍና ጋር ስናነጻጽረው፣ አውግስቲን ግን ኃጢአት በውርስ የሚተላለፍ የሰው ተፈጥሮ ነው ይላል። ይህ ከእኛ ማንነት ጋር የተዋሀደ ተፈጥሯዊ ማንነታችን እንጂ አማራጭ የሆነ(በምርጫ የምንኖረው) ሕይወት አይደለም። ይህ አመለካከት ለአውግስቲን ስለ ውርስ ኃጢአት በሰፊው እና በቀጥታ ማብራራት ስለ ኃጢአት አስተምህሮ እና ስለ ደኅንነት ማዕከላዊ አስፈላጊነት ለመረዳት ይጠቀምበታል። ሁሉም ኃጣአተኞች ስለሆኑ ሁሉም ሊታደሱ ወይም ሊዋጁ ይገባል። ሁሉም የእግዚአብሔር ክብር ስለጎደላቸው ሁሉም መዋጀትና መታደስ ይኖርባቸዋል።
ለአውግስቲን ሰው የራሴ የሚለውን ነገር ሁሉ ካልጣለ ከእግዚአብሔር ጋር በምንም ሁኔታ ሕብረት ሊኖረው አይችልም የሚል ነው። ማንኛውም ወንድ ሆነ ሴት የኃጢአትን አቅም በበቂ ሁኔታ ለመስበር ምንም ማድረግ አይችልም።ይህን አውግስቲን መልካም በሆነ ምንም መጋጠም በማይችል ነገር ያብራራዋል። ይህም ናርኮቲክ በተባለ አደንዛዥ ዕጽ ሱስ የተያዘ ሰው  ከኮኬይን ወይም ከሄሮይን ከተባለ አደንዛዥ ዕጽ ነጻ ለመውጣት እንደመጣጣር አይነት ነው። ይህ አይነት ለውጥ ከውስጥ አይደለም፣ መለወጥ የሚፈልግ ሰው ከውጫዊው ሰዋዊ ሁኔታ ሊሆን ይገባዋል። እንደ አውግስቲን አባባል እግዚአብሔር ጣልቃ የገባው ሰው በተቸገረበት አጣብቂኝ ሁኔታ ነው። የእግዚአብሔር ፍላጎት ይህን ማድረግ ሳይሆን ነገር ግን ከፍቅር በመነጨ ለሰው ውድቀት እግዚአብሔር በሰው ሁኔታ ውስጥ በመግባት በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት በመዋጀት ነው።

ነገረ መለኮት (Theology)

26 Jul, 15:34


👉የቤተክርስቲያን አስተምህሮ👈
በምዕራብ ቤተክርስቲያናት ዘንድ አንዱና ዋነኛው አወዛጋቢ የነበረው ጥያቄ የቤተክርስቲያን ቅዱስነትን በሚመለከት ነበር። ዶኔቲስት የተባሉ አፍሪካዊ የክርስቲያን ቡድኖች በአሁኗ አልጄሪያ የነበሩ፣ በሰሜን አፍሪካ  እያደገና ተጽዕኖ እየፈጠረ በነበረው የሮም ቤተክርስቲያን ላይ ትልቅ ቅሬታ ነበራቸው። ዶኔቲስቶች የሚከራከሩበት አንዱ ሀሳብ "ቤተክርስቲያን የቅዱሳን አካል ነች፣ ለምንም አይነት ኃጢአተኛ ቦታ የላትም!"ይላሉ። ይህ ሀሳብ በተለይ በንጉስ ዳዮክሌቲያን በ303 ዓ.ም. ትልቅ ስደት በተነሳበት ጊዜ እጅግ አስፈላጊ ነበረ፣ እንዲሁም በ313 ዓ.ም. በቆስጠንጢኖስ መለወጥ ድረስ ይህ ሀሳብ የጸና ነበር። በዚህ የመከራና የስደት ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስን በግልሰብ ደረጃ መያዝ ሕገወጥነት ነበር። በጥቂት ስልጣን ባላቸው ክርስቲያኖች ዘንድ ብቻ ነበር የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ የነበረው። እነርሱም በስደቱ ምክንያት ወደ ዋሻ ውስጥ ለመኖር ተገደዱ። ከስደቱ ማብቃት በኋላ ብዙ "ትራዲተርስ" የላቲን ቃል ሲሆን "የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ በእጃቸው የነበሩ ሰዎች" የሚጠሩበት ነው፣ ቤተክርስቲያንን ተቀላቀሉ። ዶኔቲስቶች ከሌሎች ጋር ለመቀላቀል ፍላጎት በማሳየት በራሳቸው ይሄን ውሳኔ ወሰኑ። አውግስቲን ስለዚህ ሀሳብ ሙግትን ሲያቀርብ "ቤተክርስቲያን ጻድቃንንና ኃጢአተኞችን "ሁሉንም ያቀፈች አካል" ናት ይላል። በተለያየ ምክንያት እና በስደት ጊዜ የእምነት መዛባት የገጠማቸውን ሰዎች ከቤተክርስቲያን ማሳደድንና ማስወጣትን ተቃውሟል። የቤተክርስቲያን አገልግሎት እና የስበከት አስፈላጊነት መሰረት ያደረገው በአገልጋዮቹ ቅዱሳን መሆን ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ ማንነት ላይ ነው።
ይህንን በተመለከተ ዶኔቲስቶች ያነሱት ቤተክርስቲያንና ስርዓቶቿን በተመለከተ ጥያቄያዊ ሙግቶች አብዛኛዎቹ በተሀድሷውያንም ዘመን ተነስተው ነበር።