Yeka Subcity Teachers Association

@yekateachersassociation


yeka subcity teachers association channel

Yeka Subcity Teachers Association

22 Oct, 07:40


የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ እየተሰራ ነው

አዳማ፤ ጥቅምት 7/2017(ኢዜአ)፦ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት መምህራን የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻል እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ገለፀ።

37ኛው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክር ቤት ጉባዔ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት ዮሐንስ በንቲ(ዶ/ር) በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት የመምህራን መብት በተለይም ጥቅማ ጥቅምና የሚያጋጥማቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት የሙያ ማህበሩ እየሰራ ይገኛል።

በተለይም በትምህርት ጥራት መረጋገጥ፣ በየደረጃው የሚካሄደው የማህበሩ ምርጫ፣ መምህራን በሀገራዊ ምክክር በሚኖራቸው ተሳትፎ ላይ  በሚኖራቸው ሚና ላይ ጉባዔው በጥልቀት ይመክራል ብለዋል።

መምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲያገኙ ማህበሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በእስካሁኑ ሂደትም ከ120ሺህ በላይ መምህራን በሀገር አቀፍ ደረጃ የመኖሪያ ቤትና ቤት መስሪያ ቦታ ማግኘታቸውን ለአብነት አንስተዋል።

መምህርነት የሚኖረው ጥራቱን የጠበቀና የተሻለ የመማር ማስተማር ሥራ ሲኖር ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የትምህርት ጥራት ችግሮችና ጉድለቶችን የሚለዩ ጥናቶችን በማካሄድ የመፍትሄ ሐሳቦች ለመንግስትና ባለድርሻ አካላት እያቀረቡ መሆናቸውን አንስተዋል።

በተለይ የትምህርት ቤቶች የፋይናንስ ድጋፍ ፈንድ የማሰባሰብና አቅማቸውን የማጎልበት፣ የትምህርት መርጃ ቁሳቁስና ተያያዥ ግብዓቶች እንዲሟሉ እንዲሁም ቤተ ሙከራዎች እንዲደራጁ ማህበራቸው ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም እንዲሁ።

ከጉባዔ ተሳታፊዎች መካከል የኦሮሚያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዋቅወያ ቶሌራ በበኩላቸው ባለፈው ዓመት የመምህራን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ በተደረገው ጥረት በክልሉ ከሶስት ሺህ በላይ መምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የትምህርት ጥራት ጉዳይ የማህበሩ ቀዳሚ አጀንዳ መሆኑን ገልጸው፤ የመብት ጥያቄ ብቻ ማቅረብ ሳይሆን በሙያችን የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ እየሰራን ነው ብለዋል።

ከመምህራን ጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰሩ መሆኑን በማንሳት።

በአዳማ ከተማ ለሶስት ቀናት በተሰናዳው ጉባዔ ላይ ከሁሉም ክልሎችና ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የመምህራን ማህበር አመራር አባላትና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጋበዙ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

መረጃዎቻችንን፦

በዩቲዩብ፡- https://www.youtube.com/channel/UCSjaw-eGJSkvcXHyTpQyT1Q
በቴሌግራም፡- https://t.me/EthiopianNewsA
በድረገጽ፡- https://www.ena.et/
በትዊተር፡- https://twitter.com/ethiopiannewsa?lang=en
የኢዜአ ዜናዎችን በአጭር የስልክ መልዕክት ለማግኘት፡- 9111
ፈረንሳይኛ ድረ-ገጽ https://www.ena.et/web/fre
አረብኛ ድረ-ገጽ https://www.ena.et/web/ara
በአፋን ኦሮሞ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/TajaajilaOduuItoophiyaa/
በትግሪኛ ፌስቡክ፦ https://ww.facebook.com/ethiopianewsagencytigrigna/
በአፍ ሱማሌ ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/ethiopianewsagencyafsoomaali
በአፍ ሱማሌ ድረ-ገጽ፦ https://www.ena.et/web/som
በአፋርኛ ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/ethiopianewsagencyqafarafa
በአፋርኛ ድረ-ገጽ፦ https://www.ena.et/web/aar አድራሻዎቻችን ያገኟቸዋል።

Yeka Subcity Teachers Association

22 Oct, 07:39


የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ከጥቅምት 7-9/2017 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ ሲያካሄድ የነበረውን 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቀቀ።

           ስብሰባው በማህበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የተጀመረ ሲሆን የማህበሩ የ2016 ዓ.ም የስራ አፈፃፀምና የኦዲት ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ወይይት ተደርጓል ።
መምህራንን እየተፈታተነ ያለው ከፍተኛ የኑሮ ውድነት፣ ረጅም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው መምህራን የደረጃ እድገት ወይም የእርከን ጭማሪ አለመኖር፣ በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደሞዝ በጊዜ አለመከፈል ብሎም እየተቆራረጠ በፐርሰንት መከፈል፣ ያለመምህራን ዕውቅናና ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደሞዝ መቆረጥ፤ ይሄንን የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት፣ ቀደም ብሎ የተጀመረው የመምህራን የመኖሪያ ቤት እና የመሥሪያ ቦታ በሚፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ ያለመሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ደግሞ ጭራሽ አለመጀመሩ፣ በትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ተደራራቢ ግብር መቆረጡ፣ የመጽሐፍትና ሌሎች ግብአቶች እጥረት፣ የክረምት መምህራን ስልጠናና ያጋጠሙ ችግሮች ...ወዘተ በተሳታፊዎች በአስተያየት እና በጥያቄ መልክ ተነስተዋል።

          በቀረቡት ጥያቄዎች ዙሪያ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ኮራ  ጡሹነ  እና በት/ት ሚንስቴር የመምህራንና ትምህርት አመራሮች ዴስክን ጨምሮ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከመምህራን ጥቅማ ጥቅም ጋር በተያያዘ እየታየ ያለው ጥያቄ የተጀመረው የትምህርት ሴክተር ሪፎርም ተጠናቆ ተግባራዊ ሲሆን ብዙ ጉዳዮች እንደሚፈቱ ገልፀዋል ።

            ምክር ቤቱ የዩኒቨርስቲዎችን ጨምሮ የሁሉንም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መምህራን ማህበራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና  በተለያዩ አጀንዳዎች ለአብነት በትምህርት ጥራት፣ በመምህራን መብትና ጥቅም፣ በየደረጃው አየተገነቡ ስለሚገኙት የህንፃ ግንባታዎች፣ በምርጫ አፈጻጸም መመሪያ፣ በዘንድሮው አመት ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ማዕከላዊ ፅ/ቤት ድረስ ስለሚካሄደው የመምህራን ማህበር አመራሮች ምርጫ፣ የማህበሩ ሪፎርም ሰነድ ዝግጅት፣ በማህበሩ የሴት አመራሮች ኮከስ አጀንዳ፣ በሀገራዊ ምክክር የመምህራንና የማህበሩ ሚና፣ በሀገራዊ ሠላምና ወደብ የማግኘት መብትን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርጓል ።

           በስብሰባው ላይ በ36ኛው ምክር ቤት ያልተሳተፈዉ የአማራ ክልልን ጨምሮ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የማህበሩ የምክር ቤት አባላት ፣ የዩኒቨርስቲዎች መምህራን ማህበር፤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት፣ ከትምህርት ሚንስቴር፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ ከሥራና ክህሎት ሚንስቴር ተወካዮችና የተማሪ ወላጆች ማህበር ፕሬዝዳንት  ተገኝተዋል።

           በመጨረሻም የማህበሩ የ2017 በጀት ዓመት የሥራና በጀት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት እና የአቋም መግለጫ ከተነበበ በኋላ ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር እና በሰጡት የስራ አቅጣጫ ስብሰባው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

         የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ለምክር ቤት ስብሰባው መሳካት አስተዋፅኦ ላደረጉት ለኦሮሚያ ክልል እና ለአዳማ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበራት ምስጋናውን ያቀርባል።

Yeka Subcity Teachers Association

06 Oct, 16:30


ማስታወቂያ!


(መስከረም 25/2017 ዓ.ም)




መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- [email protected]

Yeka Subcity Teachers Association

05 Oct, 12:54


እንኳን በመላው አለም ለሚከበረው የመምህራን ቀን October 5 አደረሳችሁ!!

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር !!

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የአለም መምህራን ቀንን ከመስከረም 30 - ጥቅምት 1/2017 ዓ.ም ድረስ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በተለያዩ መርሀግብሮች ያከብራል!

Yeka Subcity Teachers Association

01 Oct, 17:58


ማሳሰቢያ

ከላይ ስማቹህ የተዘረዘራቹህ መምህራን የምደባ ደብዳቤ በቀን 22-23/1/2017 ዓ.ም ብቻ የምደባ ደብዳቤ እንድትወስዱ እናሳስባለን!!

Yeka Subcity Teachers Association

22 Sep, 13:01


ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ እና ለዚህ እድሜ ተመጣጣኝና ተስማሚ በሆነ በጨወታ የማስተማር ስነ ዘዴ ላይ የተመሰረተ የትምህርት ቤት ሁላጤ ( School transformation) ተግባራትን ለማከናወን ከደብረ ብርሃንና አሰላ የመምህራን ትምህርት ኮሌጅ ጋር በጋራ በመስራት በሞግዚትነት እየሰሩ የሚገኙትን የትምህርት እድል በመስጠት ለደረጃው ብቁ የሆኑ መምህራንን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በቀጣይ አዲስ ሰልጣኞችን ለማስገባት ከኮሌጆቹ ጋር ስምምነት ላይ ስለተደረሰ  በግልና በመንግሰት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሞግዚትነት የስራ መደብ ላይ እየሰሩ የሚገኙና ለመማር ፍላጎት ያላቸውን በመስፈርቱ መሰረት
መስፈርት፡-
➢ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቅድመ አንደኛ ተማሪዎች ሞግዚት ሆነው እየሰሩ ያሉ እና በቋሚነት የተቀጠሩ (በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚሰሩ)
➢ ከ10ኛ ክፍል አጠናቀው የተቀጠሩ ውጤታቸው 2፡00 ነጥብ እና በላይ የሆነ(ለመንግስትም ለግልም)
➢ ከ12ኛ ክፍል አጠናቀው የተቀጠሩ በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚሰሩ 150 እና በላይ እንዲሁም ለግል ትምህርት ቤት አመልካቾች 200 እና በላይ ያላቸው ጉለሌ ክፍለከተማ ትምህርት ጽ/ቤት 7ኛፎቅ በመገኘት ሙሉ መረጃ ዋና እና ኮፒ በመያዝ መመዝገብ ትችላላችሁ
ማሳሰቢያ፡-
➢ የተመለመሉት አካላት በበጋ የት/ት ፕሮግራም (በእረፍት ቀናት) ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ይሆናል፡፡

 
 

Yeka Subcity Teachers Association

18 Sep, 10:50


የመኖሪያ ቤት የሌላቸው መምህራን በማህበር ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ተገመገሙ።

(መስከረም 8/2017 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ የመምህራን ማህበር አመራሮች እንዲሁም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር እና የህብረት ስራ ኮሚሽን የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና የቢሮ ኃላፊ ተወካይ ወይዘሮ ታጋይቱ አባቡ በውይይቱ ባስተላለፉት መልዕክት የመኖሪያ ቤት የሌላቸው መምህራን ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራትን በመገምገም በቀጣይ በፍጥነት ወደ ግንባታ በመግባት መምህራኑ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ በበኩላቸው መምህራን የቤት ባለቤት እንዲሆኑ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከምዝገባ ጀምሮ እስካሁን እያደረጉ ለሚገኘው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ ማህበራቱን በማደራጀት ወደ ቀጣዩ ስራ መግባት እንደሚገባ አመላክተዋል።

የመንግስት ሰራተኞች የጋራ ህንጻ የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀት እና አፈጻጸም ደንብ ቁ.129/14 መሰረት መምህራኑን ለማደራጀት የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት በህብረት ስራ ኮሚሽን አማካይነት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ ማጠቃለያ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን 30% ቆጥበው ወደ መደራጀት ለመግባት የተመዘገቡ መምህራንን ወደ ግንባታ እንዲገቡ ከባንክ ጋር የማስተሳሰር እና መሬት የማቅረብ ስራ በሚመለከታቸው አካላት መሰራት እንደሚገባ በመጠቆም በሂደት እየቆጠቡ ለመደራጀት የተመዘገቡትን የቁጠባ ባህላቸውን አሳድገው ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ እንዲገቡ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- [email protected]

Yeka Subcity Teachers Association

15 Sep, 12:31


መልካም የመውሊድ በዓል!

Yeka Subcity Teachers Association

11 Sep, 08:36


ፍቅር እስከ መቃብር ተከታታይ ፊልም ከዛሬ መስከረም 1 ጀምሮ መታየት ይጀምራል።

“ፍቅር እስከ መቃብር” ተከታታይ ፊልም በአዲሱ ዓመት ከዛሬ መስከረም 1 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ለተመልካቾች መቅረብ እንደሚጀምር ተገልጿል።

ፊልሙ፥ በኢቢሲ ዜና ቻናል ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እና በመዝናኛ ቻናል ደግሞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ይተላለፋል፡፡ እንዲሁም በድጋሚ ምሽት ከዜና በኋላ በሁለቱም ቻናሎች ይተላለፋል ተብሏል፡፡

“ፍቅር እስከ መቃብር” ልብ ወለድ መጽሐፍን ወደ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ቀይሮ ለማቅረብ ከ'ሰው መሆን ፊልም ፕሮዳክሽን” ጋር የተፈራረመው በ2015 ወርኃ የካቲት ላይ ነበር።

በስምምነቱ ወቅት ፊልሙ 48 ክፍሎ፤ እንዲሁም ድራማው በአማካይ 45 ደቂቃ ርዝማኔ እንደሚኖረውም ተነግሯል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

Yeka Subcity Teachers Association

11 Sep, 06:17


እንኳን ለ2017 ዓ.ም አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ

🔤አዲሱ አመት

የሰላም

የፍቅር

የመቻቻል

የመተሳሰብ

የአንድነት

የለውጥ እና

የውጤት አመት ይሆን ዘንድ እንመኛለን!!

⭐️ መልካም አዲስ አመት ⭐️


⭐️የካ ክ/ከተማ ምህራን ማህበር  ⭐️

Yeka Subcity Teachers Association

05 Sep, 16:19


የስራና ተግባር ትምህርት አይነቶች መምህራን ምልመላ መስፈርት.pdf

Yeka Subcity Teachers Association

05 Sep, 16:19


ማስታወቂያ፡-
በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች አዲስ ለሚጀመረው የስራና ተግባር ትምህርት ለማስተማር የሚፈልጉ የትምህርት ዝግጅታቸው የሚጋብዛቸው የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ነባር መምህራን ከዚህ በቻች ያለውን መስፈርት የሚያሟሉ ከሆነ ሃሙስ እና አርብ ማለትም 30/12/2016 ዓ.ም እና 01/13/2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት የትምህርት ማስረጃቸውን ይዘው በመምጣት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ ለ፡- መረጃው ሁሉም መምህራን እንዲደርሳቸው ይደረግ

Yeka Subcity Teachers Association

05 Sep, 16:11


የስራና ተግባር ትምህርት አይነቶች መምህራን ምልመላ መስፈርት.pdf