እንዲህ እንደዋዛ...
ዛሬ ሮመዳን ከገባ 27 ቀን ሞላው?!! ጊዜው እንዴት ይሮጣል።
በወጉ ሳንጾመው፣ በአግባቡ ቁርዓኑን ሳንቀራው፣ ከታሀጁድ ሶላት ጋር በደምብ ሳንላመድ... እውነትም " አያመን መዕዱዳት– የተቆጠሩ ቀናት" ።
እነዚህ ቀናቶች መች ከሮመዳን ብቻ ከእድሜያችንም ነው አጉድለው የሄዱት።
የሰው ልጅ የቀናት ጥርቅም ነው ። በየቀኑ እየጉደለ ይሄዳል። ልክ battery full እንደሆነ ሞባይል በቀን የአገልግሎት ውሎው እየጎደለ እንደሚደሄው ሁሉ።
ጊዜ ህይዎት ነው ወርቅ አይደለም። ወርቅን በገንዘብ ልትገዛው ትችላለህ፣ የዓለምን ንብረት ሁሉ ኢንቨስት ብታደርግ ግን አንድን ቀን መግዛት አትችልም።
እዲህ እንደዎዛ ህይዎት ተጠንጥና ወደ ማይቀረው ጉዞ እንሄዳለን። አሰተዎይ ማለት ታድያ በሰው ልጆች ውስጥ ደማቅ አሻራ ትቶ ያለፈ ነው። የበጎ አሰተወፅኦ ፋናው አህጉራትን አቋርጦ ያበራለት ነው።ለማህበረሰቡ የመልካም ነገር ተምሳሎት ሆና ታሪክ ማህደር ላይ የሰፈረ ነው።
" His life is done, but his legacy is not" የተባለለት ነው።
ቀሪውን ቀናቶች አላህ ይባርክልን
# ረበና ተቀበል ሚንና ኢነከ አንተ ሰሚዑል ዐሊም።
ወቱብ ዐለይና ኢነከ አንተ ተዋቡ ረሒም♡