Wolaita Sodo University CMHS otona campus

@wsuotona


Wolaita Sodo University CMHS otona campus

04 Oct, 18:36


የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡

** ** ***
ሴኔቱ በትናንትናውና በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የ2017 ዓ.ም የትምህር ዘመን አካዳሚክ ካላንደር ጉዳይን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያየቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በሴኔቱ የውይይት ጊዜ የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌ፤ በዩኒቨርሲቲው የሚሰሩ ማናቸውም ጉዳዮች በመንግስት ህግና ደንብ መሰረት ማለፍ እንዳለባቸው ጠቁመው የመማር ማስተማር፣ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን እንዲሁም መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚያግዙ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ሴኔቱ እንዲወስን አቅርበዋል፡፡

በዚሁ መሰረት ሴኔቱ በተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር ለንድፍና ለተግባር እንዲሁም ለላቦራቶሪ ሥራዎች የክፍያ መጠን፣ የዩኒቨርሲቲው መምህራን በታወቁ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ጆርናሎች ላይ ጽሑፍ (Article) ሲያሳትሙ የማበረታቻ ክፍያ እና በዩኒቨርሲቲው በክረምትና በማታ መርሃ ግብር በግል ለሚማሩ ተማሪዎች የመኝታና የምግብ አገልግሎት ለማቅረብ የመኝታና የምግብ አገልግሎት ክፍያ መጠንና የአከፋፈል ሁኔታ የተመለከቱ መመሪያዎችን ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

ክፍያዎቹ አገልግሎት ፈላጊውን አቅም ባገዘናዘበ እና ዩኒቨርሲቲውም የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን ማሳለጥ በሚያስችል መልኩ በአጥኚ ቡድን የቀረበ ሲሆን በመመሪያቹ ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ ተወስኖ ለተፈጻሚነት ሁሉም በኃላፊነት መንቀሳቀስ እንዳለበት ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በተለያዩ ኮሌጆች ትምህርታቸውን ጨርሰው ሳይመረቁ የቀሩ ተማሪዎች የምረቃ ጉዳይ፣ የጂኦግራፊያዊ መረጃ ሥርዓት (GIS) እና የሶሻል ወርከር (Social Worker) ትምህርት ስለማስጀመር በተመለከተ ሴኔቱ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

የታሪክ ትምህርት የጋራ ኮርስ (Common Course) ሆኖ በሁሉ ትምህርት ክፍሎች እንዲሰጥ እንዲሁም የ2017 ዓ.ም አካዳሚክ ካላንደር ሴኔቱ ተወያይቶ ያፀደቃቸው አጀንዳዎች መሆናቸውን ከውይይት መድረኩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ

➤ መስከረም 24/2017 ዓ.ም (ወሶዩ)

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

03 Oct, 17:23


RIP

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

03 Oct, 17:06


የሐዘን መግለጫ
*****
የወላይታ ሶዶ ዪኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ
ኮምፕርሄንሽቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና አገልግሎት ባልደረባ የነበሩ አቶ ዳንኤል ደረሰ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ ።
=====
አቶ ዳንኤል ደረሰ ከአባታቸው ከአቶ ደረሰ ዳቅቶ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አላኔ አኔቦ ወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ ወራዳ ሼላ መቄራ ቀበሌ 1985 ዓ.ም ተወለደው፤ ባደረባቸው ሕመም በሆስፒታሉ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ መስከረም 23/2017 ዓ.ም. በተወለዱ በ32 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ፡፡

አቶ ዳንኤል ደረሰ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሜድካል ማይክሮባይሎጅ ተመርቀው በሕክምና ላቦራቶሪ ሙያ ሲያገለግሉ የነበሩ፤ ትጉህ ፣ ታታሪና መልካም ስነምግባር ባለቤት ነበሩ።

አቶ ዳንኤል ደረሰ ባለትዳርና የአንድ ሴት ልጅ አባትም ነበሩ።

የወላይታ ሶዶ ዪኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ማኔጅመንት እንዲሁም መላው ስታፍ በአቶ ዳንኤል ደረሰ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ፤ ለቤተሰቦቹ ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና ሥራ ባልደረቦቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡

የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
መስከረም 23/2017 ዓ.ም

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

02 Oct, 17:53


#MoH

ጤና ሚኒስቴር በፅሁፍ ከሚሰጠው የብቃት ምዘና ፈተና በተጨማሪ #የተግባር ተኮር የብቃት ምዘና ፈተና|OSCE ለመጀመሪያ ጊዜ ሊሰጥ ነው፡፡

በዚህም ሰኔ 2016 ዓ.ም የተሰጠውን የመውጫ ፈተና አልፈው ዲግሪ ለያዙና የተግባር የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ለሚገኙ #የአንስቴዥያ ጤና ባለሙያዎች #የተግባር ተኮር የብቃት ምዘና ፈተና መስከረም 30/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ተፈታኞች ከሚፈተንበት ቀን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ማለትም መስከረም 29/2017 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (Orientation) መከታተል፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርባቸዋል።

ተፈታኞች በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡

ተመዛኞች ወደ ፈተና ጣቢያ ስትሔዱ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ Print አድርጋችሁ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡ በፈተናው ወቅት አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረም እንዳትዘነጉ ተብሏል፡፡

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

23 Sep, 09:39


የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ይፋ ሆኗል።

በ2017 ዓ.ም የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለሚማሩ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወሳል።

የተፈታኞች ውጤት ዛሬ ይፉ ሆኗል። ተፈታኞች የምዝገባ ቁጥር / Username በማስገባት ውጤታችሁን በተከታዩ ሊንክ መመልከት ትችላላችሁ
https://result.ethernet.edu.et/ngat_result

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

12 Sep, 15:04


ዶክተር ወኪል ወልዴ፤ በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንሰና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ፤
ተማሪዎችን እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ! አደረሰን ! በማለት በዓሉን ከተማሪዎች ጋር አከበሩ

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

10 Sep, 18:51


ለመላው የኮሌጃችን ክሊኒካል ፣ አስተዳደርና አካዳሚክ ስታፍ እንዲሁም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ትምህርት ላይ ያላችሁ ተማሪዎቻችንና በጤና እክል በሆስፒታላችን ሕክምና ላይ የምትገኙ ወገኖቻችን፤

እንኳን ለ2017 .አዲስ ዓመት በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ! አደረሰን !

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
ውድ ወገኖቼ ፦
አዲሱ ዓመት ሠላም የሚያብብበት፣ ዕድገት ብልጽግና እውን የሚሆንበት እንዲሁም አብሮነት፣ መከባበርና መተሳሰብ የሚጎለብትበት እንዲሆንልን እመኛለሁ።

ዓመቱ ፦በአዲስ መንፈስ ተነቃቅተን ፣ በተሻለ ተቋማዊ ሪፎርም ተሰናስለን በውጤታማ ተግባቦት ፣ ተመካክረንና ተባብረን የተሻለ አገልግሎት ለሕዝባችን የምናሳልጥበት ዓመት እንዲሆን በጋራ እንሠራለን እያልኩ፤ አዲሱ ዓመት የሠላም ፣ የእርቅ ፣ የፍቅርና የመቻቻል እንዲሁም የመከባበር እንዲሆን እመኛለሁ ።

ዶክተር ወኪል ወልዴ፤
በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንሰና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ።

ጳጉሜ ❺ 2016 ዓ.ም

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

12 Aug, 12:46


የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የጤና ባለሙያዎች በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የዚሁ ፈተና ምዝገባ ከነሀሴ 06 - 15/2016 ዓ.ም የሚከናወን ስለሆነ ፈተናውን የምትወስዱ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከላይ ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
-በሰኔ 2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የፋርማሲ ሙያ የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች በጤና ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና መውሰድ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እያሳሰብን ከላይ በተጠቀሰው ዌብሳይት ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡

- በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እያሳወቅን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

- እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳስባለን።

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

- ከዚህ በፊት የብቃት ምዘና ፈተናውን ተፈትናችሁ ያላለፋችሁ ወይም አዲስ ተመዛኞች ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ/Link/ በመጫን ስማችሁን በመፈለግ ስልክ ቁጥራችሁን እንድታስገቡ እያሳሰብን ከዚህ በኋላ ውጤት የምታዩት ወይም ማንኛውም ከብቃት ምዘና ፈተና ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማግኘት የምትችሉት ባስመዘገባችሁት ስልክ ቁጥር መሆኑን እየገለጽን ይህንን መረጃ ሳታሟሉ ቀርታችሁ ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር ኃላፊነት የማንወስድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

(https://docs.google.com/spreadsheets/d/118unZ6bK8AGLIfMfmFIxCNbeccMkP4yz8kfGBGsGk7s/edit?usp=sharing)

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

07 Aug, 14:31


የብቃት ምዘና ፈተና ለወሰዳችሁ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
____

በMedicine, Nursing, Public Health, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing, Emergency & Critical Care Nursing, Surgical Nursing, Physiotherapy እና Human Nutrition ሙያዎች ተመርቃችሁ በሰኔ 19/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር እና በጤና ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የመውጫ እና ብቃት ምዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከነሀሴ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን (username) በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል [email protected] ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር(username) እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ማሳሰቢያ፦
በትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ዲግሪ የያዛችሁና የጤና ሚኒስቴርን የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች ስም ዝርዝራችሁን ከ03/12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለክልል የጤና ተቆጣጣሪ አካላት የሚላክ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ አሟልታችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች ይህን ተከትሎ በሚወጣ ማስታወቂያ የተግባር ምዘና(OSCE) ፈተና የምዝገባ መርሃ ግብር ስለሚወጣ በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንዲሁም ለፈተናው ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

04 Jul, 16:30


Congratulations To All Graduate Classes medical student Of WSU  @27/10/2016EC.🎉🎉🎉👩‍🎓👨‍🎓

Wolaita Sodo University CMHS otona campus

04 Jul, 07:25


የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለ16ኛ ጊዜ በተለያዩ ፕሮግራሞችና የትምህርት መስኮች ያስለጠናቸውን ከ800 በላይ ተማሪዎች ዛሬ ያስመርቀል።

ዩኒቨርሲቲው በጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ፤ ሕክምና
ዶክትሬትና አነስቴዢያን ጨምሮ 8 መቶ 59 ተማሪዎችን ዛሬ ያስመርቃል፡፡

ከአጠቃላይ ዕጩ ተመራቂዎች መካከል፦ 04 በዶክትሬት ድግሪ (Ph.D) ፣ 446 በማስተርስ ድግሪ እንዲሁም 409 በመጀመሪያ ድግሪ መሆናቸው ተገልጿል።

በዕለቱ ከሚመረቁ 8 መቶ 59 ተማሪዎች 671 ወንዶች ሲሆኑ 188 ሴቶች እንደሆኑም ተመላክቷል።

ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችን እና የምሩቃን ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ .,

CONGRATULATIONS!!
➤ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም