ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

@pointing_to_the_true_religion


ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ ወደ ትክክለኛውና ወደ ተፈጠርንለት ሀይማኖት ማመላከት ነው.

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

22 Oct, 03:08


የነብዩ "ﷺ" ልጅ ኢብራሒም በሞተበት ቀን የጸሀይ ግርዶሽ ተከስቶ ነበር። ሰዎቹ ክስተቱን ከሳቸው ልጅ መሞት ጋር በማገናኘት የሀዘን ምልክት አድርገው ወስደውት ነበር። ኃላ ነብዩ ሙሐመድ "ﷺ" ሲሰሙ ግን መሳሳታቸው ገልጸው ገሰጿቸው። ጸሀይና ጨረቃ የአሏህ ﷻ ተአምራት/ምልክቶች መሆናቸውን የጸሀይ ግርዶሽም በአንድ ሰው ሞትም ሆነ ህይወት ምክንያት የሚፈጠር እንዳልሆነ አብራርተው ስህተታቸውን አረሙ።

አንድ ሀሰተኛ ነብይ ቢሆን መሠል ወርቃማ እድልን ፈጽሞ አያሳልፍም ነበር። ክስተቱን ተመርኩዞ አይደለም በተቃራኒው ሊናገር ይቅርና ሀሳቡን በማጠናከር "ተመልከቱ በልጄ መሞት ሰማይ እንዴት እንዳዘነ" በሚል ለዚህ ሀሳብ መጀመሪያውኑ የቀረቡ ሰዎችን በተሻለ ለማሳመን እድሉን ይጠቀምበት ነበር። ግን ለእውነተኛ ነብይ ከእውነት በላይ ማስረጃም ጉዳይም የለውምና ይህንን የሚያደርጉበት ምክንያት ስልነበራቸው ፈጽሞ አላደረጉትም፣ ማድረግም አይጠበቅባቸውም ነበር..!

የሕያ ኢብኑ ኑሕ
https://t.me/Yahyanuhe

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

21 Oct, 19:01


ፈጣሪ ሁሉን ዐዋቂ ነው።


۞ وَعِندَهُ مَفَاتِحُ الْغَيْبِ لَا يَعْلَمُهَا إِلَّا هُوَ ۚ وَيَعْلَمُ مَا فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ ۚ وَمَا تَسْقُطُ مِن وَرَقَةٍ إِلَّا يَعْلَمُهَا وَلَا حَبَّةٍ فِي ظُلُمَاتِ الْأَرْضِ وَلَا رَطْبٍ وَلَا يَابِسٍ إِلَّا فِي كِتَابٍ مُّبِينٍ

የሩቅ ነገርም መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው፡፡ ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም፡፡ በየብስና በባሕር ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ ከቅጠልም አንዲትም አትረግፍም የሚያውቃት ቢኾን እንጅ፡፡ ከቅንጣትም በመሬት ጨለማዎች ውስጥ የለም ከእርጥብም ከደረቅም አንድም የለም ግልጽ በኾነው መጽሐፍ ውሰጥ (የተመዘገበ) ቢኾን እንጅ፡፡(አል-አንዓም፡59)


وَأَسِرُّوا قَوْلَكُمْ أَوِ اجْهَرُوا بِهِ ۖ إِنَّهُ عَلِيمٌ بِذَاتِ الصُّدُورِ

(ሰዎች ሆይ!) ቃላችሁንም መስጥሩ፡፡ ወይም በእርሱ ጩሁ፡፡ እርሱ በልቦች ውስጥ ያለን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡(አል-ሙልክ ፡13

ከአንቀጾቹ እንደምንረዳው "አሏህ" ከርሱ ሊሰወርና ሊደበቅ የሚችል ነገር እንደሌለና ሰው ነገ ከነገ ወዲያ የሚናገረውን አስቀድሞ የሚያውቅ መሆኑን ነው።

የመጽሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፦

ዘፍጥረት 18
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ እግዚአብሔርም አለ፦ የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥
²¹ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤
እግዚአብሔር "ሶዶምና ገሞራ""ኃጢአት እንደሚሰሩ ሰምቶ ነበር ይሁን እንጂ የሰማው ነገር እውነት ይሁን አይሁን ሂዶ ማረጋገጥ ግድ ሆኖበታል። ማየት ማመን ነውና! ይህ የፈጣሪ ባሕሪ ነውን

በትህትና ትመልሱ ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁኝ።
እውነትን ፈትሹ መልካሙንም ያዙ
ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥20-21

ወሠላሙዐለይኩም።

✍️ ዙዙቲ ነኝ የወሒድ ተማሪ

https://t.me/Pointing_to_the_True_Religion

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

20 Oct, 19:31


በኮሜንት አበረታቷቸው፦ https://youtu.be/F_j1TQZK0_o?si=DfrRbkE6cPS5jMvC

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

19 Oct, 19:22


ግቡ ኡስታዝ ወሒድ እና ወንድሞች ገብተዋል

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

17 Oct, 21:25


ነጥብ ሁለይ
"ሐዲሱል ቁድሢይ"
"ቁድሥ" قُدْس የሚለው ቃል "ቀዱሠ" قَدُسَ ማለትም "ቀደሰ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ቅዱስ" ማለት ነው፥ የቁድሥ ገላጭ መደብ ደግሞ "ቁድሢይ" قُدْسِيّ ሲሆን "ቅዱሳዊ" ማለት ነው። በጥቅሉ "ሐዲሱል ቁድሢይ" حَدِيث الْقُدْسِيّ ማለት "ቅዱሳዊ ንግግር" ማለት ነው፥ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አላህም እንዲህ አለ" ተብሎ የሚናገሩት ንግግር ሁሉ ሐዲሱል ቁድሢይ ይባላል። ለምሳሌ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 13, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አላህም እንዲህ አለ፦ *“ከፆም በስተቀር የአደም ልጅ መልካም ሥራ ሁሉ ለራሱ ነው፥ ፆም ለእኔ ነው። እኔም ምንዳውን በእርሱ እከፍላለው"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ قَالَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ كُلُّ عَمَلِ ابْنِ آدَمَ لَهُ إِلاَّ الصِّيَامَ فَإِنَّهُ لِي وَأَنَا أَجْزِي بِهِ

ነቢያችን"ﷺ" ይህንን ወደ አሏህ አስጠግተው የሚነግሩን ቅዱሳዊ ንግግራቸው ከቁርኣን የሚለየው፦
1ኛ. ቁርኣን የአሏህ ንግግር ብቻ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በነቢያችን"ﷺ" ንግግር "አሏህ አለ" ተብሎ በኒስባህ መነገሩ ነው።
2ኛ. ቁርኣን አሏህ በጂብሪል በኩል የተናገረው የራሱ ንግግር ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በነቢያችን"ﷺ" ሕልም "አሏህ አለ" ተብሎ በኒስባህ መነገሩ ነው።
3ኛ. ቁርኣን ሲቀራ ዒባዳህ የሚፈጸምበት ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን አይቀራም፥ በመነበቡ ዒባዳም አይፈጸምበትም።
4ኛ. ቁርኣን እያንዳንዱ ሐርፍ መቅራት አስር ሐሠናት ሲኖረው ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በውስጡ ያሉትን በመታዘዝ እንጂ በመነበቡ ሐሠናት የለውም።
5ኛ. ቁርኣን በሡራህ፣ በአያት እና በጁዝ የተከፋፈለ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን በምንም አልተከፋፈለም።
6ኛ. ቁርኣን በውዱእ መንካት ሙስተሐብ እና ያለ ውዱእ መንካት መክሩህ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ያለ ውዱእ መንካት ሙባሕ ነው።
7ኛ. ከተራክቦ በኃላ ቁርኣን ለመንካት የጀናባህ ትጥበት ፈርድ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ያለ ጀናባህ ትጥበት መንካት ሙባሕ ነው።
8ኛ. በሐይድ ይ ያለች እንስት ቁርኣንን መንካት ክልክል ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይን ግን መንካት ሙባሕ ነው።
9ኛ. ቁርኣን ለነቢያችን"ﷺ" ነቢይነት ታምር ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ለነቢያችን"ﷺ" ነቢይነት ታምር አይደለም።
10ኛ. ቁርኣን ከፊቱ እና ከኃላው ውሸት እንይመጣበት አሏህ ሙሉ ለሙሉ እንደሚጠብቀው ቃል የገባለት የራሱ ንግግር እና በሙተዋቲር የመጣ ሲሆን ሐዲሱል ቁድሢይ ግን ሐዲስ ውስጥ ስለሚካተት መቅቡል እና መርዱድ አሉት። "መቅቡል" مَقْبُول ማለት "ቅቡል" ማለት ሲሆን ተቀባይነት ያላቸው የሚባሉት ሶሒሕ እና ሐሰን የሆኑ ናቸው። "መርዱድ" مَردُود "ውድቅ" ማለት ሲሆን ውድቅ ሐዲስ የሚባሉት ዶዒይፍ እና መውዱዕ የሆኑ ናቸው።

“አሏሁ አዕለም” اَللّٰهُ أَعْلَم‎

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

17 Oct, 21:25


ሐዲሱ አን-ነበዊይ እና ሐዲሱል ቁድሢይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

“ሐዲስ” حَدِيث የሚለው ቃል “ሐደሰ” حَدَّثَ‎ ማለትም “ተናገረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ንግግር” ማለት ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” በዐቂዳህ እና በፊቅህ ነጥብ ላይ የሚናገሩት ሐዲስ ሁሉ ወሕይ ነው፦
53፥3 *ከልብ ወለድም አይናገርም*፡፡ وَمَا يَنطِقُ عَنِ الْهَوَىٰ
53፥4 *እርሱ ንግግሩ የሚወረድ ወሕይ እንጅ ሌላ አይደለም*፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا وَحْيٌ يُوحَىٰ

“ወሕይ” وَحْي የሚለው ቃል “አውሓ” أَوْحَىٰٓ ማለትም “ገለጠ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ግልጠተ-መለኮት” ማለት ነው። “መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ” የሚለው ይህንኑ ሡናህ ዋቢና ታሳቢ ያደረገ ነው፦
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡ وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ

ታዲያ ቁርኣን እና ሐዲስ ልዩነቱ ምንድን ነው? አዎ! ቁርኣን ለፍዙ ሆነ መዕናው የአላህ ነው፥ ሐዲስ ግን ለፍዙ የነቢያችን”ﷺ” ሲሆን ማዕናው የአላህ ነው። “ለፍዝ” لَفْظ ማለት “ቃል”Verbatim” ማለት ሲሆን “መዕና” مَعْنًى ማለት “መልእክት” “እሳቤ” “አሳብ”notion” ማለት ነው። የቁርኣን ተናጋሪ አላህ ብቻ ነው፥ ቃሉም የወከለው መልእክቱ፣ “እሳቤው፣ አሳቡ የራሱ ነው። ሐዲስ ደግሞ መልእክቱ፣ “እሳቤው፣ አሳቡ የአላህ ሲሆን ቃሉ ግን የራሳቸው የነቢያችን”ﷺ” ነው። አላህ የሐዲስን መልእክት ሲያወርድላቸው እሳቸው በራሳቸው ባህል፣ ወግ፣ ልምድ፣ ክህሎት፣ ትውፊት ያብራሩታል። ይህ ሐዲስ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፥ እርሱም ሐዲሱ አን-ነበዊይ እና ሐዲሱል ቁድሢይ ነው።

ነጥብ አንድ
"ሐዲሱ አን-ነበዊይ"
“ነቢይ” نَبِيّ የሚለው ቃል “ነበአ” نَبَّأَ ማለትም “የሩቅ ወሬን አወራ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “የሩቅ ወሬ አውሪ” ማለት ነው፥ የነቢይ ገላጭ መደብ ደግሞ "ነበዊይ" نَبَوِيّ‎ ሲሆን "ነቢያዊ" ማለት ነው። በጥቅሉ "ሐዲሱ አን-ነበዊይ" حَدِيث الْنَبَوِيّ‎ ማለት "ነቢያዊ ሐዲስ" ማለት ነው፥ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ" ወይም "ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ" ተብሎ የሚናገሩት ንግግር ሁሉ ሐዲሱ አን-ነበዊይ ይባላል። ለምሳሌ፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 62
አቢ ዘር እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”የአንተ ፈገግታ በወንድምህ ፊት ለአንተ ሶደቃህ ነው”*። عَنْ أَبِي ذَرٍّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ تَبَسُّمُكَ فِي وَجْهِ أَخِيكَ لَكَ صَدَقَةٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 80, ሐዲስ 102
አቢ ሙሣ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ጌታውን የሚዘክር እና የማይዘክር ምሳሌ፥ ልክ እንደ ሕያው እና እንደ ሙታን ነው”*። عَنْ أَبِي مُوسَى ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ مَثَلُ الَّذِي يَذْكُرُ رَبَّهُ وَالَّذِي لاَ يَذْكُرُ مَثَلُ الْحَىِّ وَالْمَيِّتِ

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

17 Oct, 18:10


ከቁርኣን ውጪ ስለ አሏህ ንገሩን የሚሉን ከባይብል ውጪ ለሙሴ ነቢይነት አምጡ ሲባሉ መልሱ ይህ ነው።😂😂

http://t.me/Alfurqan12b

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

16 Oct, 17:34


◆▮ውይይት▮◆

"ደቀ መዛሙርት እና ሐዋርያት ምንድነው ልዩነቱ? "
"ስቅለት፣ቤዛ ማለት ምን ማለት ነው"
"ስቅለትን አስመልክቶ
"
ሌሎችም ትምህርቶች

◍ኡስታዝ ወሒድ
           🅥🅢
◍ ከወንድሞች
◍ሌሎችም

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

16 Oct, 17:30


ስለ ነቢያችን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ማወቅ የፈለገ ይሄንን የመምህሬን መጽሐፍ ገዝቶ ያንብብ የእውነት ያኔ እውነታውን ትረዳላችሁ ወገኖቻችንም የኛዎቹን ያልገዛችሁ ገዝታችሁ አንብቡ ባረከሏሁ ፊኩም.

https://t.me/Pointing_to_the_True_Religion

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

16 Oct, 01:56


ወገኖቻችን የሚያነሷት ጥያቄ ኢየሱስ ለዘላለም ከእናንተጋ ይኖራል ብሏል ነቢዩ ሙሐመድ ደግሞ ሞተዋል ስለዚህ. መንፈሥ ቅዱሥ ነው ይላሉ አለማንበባችሁን ነው የሚያንጸባርቀው ዘላለም የሚለው ያልተወሰነ ውስን ጊዜን ለማመልከት ይመጣል

“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16
እዚህ ጥቅስ ላይ" ዘላለም "ተብሎ የተጠቀመው ቃል" አዮን" ሲሆን ያልተወሰነ ውስን ጊዜ ለማመልከት ይመጣል

ተመልከት

“አንተ ወስፌ ወስደህ በቤትህ በር ላይ ጆሮውን ትበሳዋለህ፥ ለዘላለምም ባሪያ ይሆንልሃል። በሴት ባሪያህ ደግሞ እንዲሁ ታደርጋለህ።”
— ዘዳግም 15፥17

"ለዘላለምም ባሪያ ይሆንሃል" የሚለው ይሰመርበት !እዚህ አንቀጽ ላይ " ዘላለም" ተብሎ በግሪክ ሰፕቱጀንት የገባው ቃል አዮን ነው። ባሪያው ለጌታው ባርነቱ ጌታው በሕይወት እስካለ ድረስ እንጂ ለዝንተ ዓለም ማለት ካልሆነ እንግዲያውስ ሁለተኛው አጽናኝ መጥቶ ላልተወሰነ ውስን ጊዜ ይኖራል ማለት ነው። ወይም ከእሳቸው በኋላ የሚመጣ ነቢይ ስለሌለ የነቢያት መደምደሚያ ሆኖ በዘመነ መግቦት እና በግልጠተ መለኮቱ ለዘላለም እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ይኖራል ማለት ነው ተግባባን።።

ክርስቲያን ወገኖቻችን ሆይ! አሏህ ማስተዋሉን ይስጣችሁ።
ወሠላሙዐለይኩም።

✍️ከወሒድ ተማሪ ዙዙዬ
https://t.me/Pointing_to_the_True_Religion

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

15 Oct, 17:24


ኃጢአት ማስተሰረይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣንም ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ

የናዝሬቱ ኢየሱስ በአምላክ እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ ነበር፦
ሉቃስ 24፥19 እርሱም፦ ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት፦ "በእግዚአብሔር እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ"።

ይህ ነቢይ አንዳንዴ ቃል ብቻ ሲናገር ሽባ ይፈውስ ነበር፥ በአልጋ የተኛ ሽባ አምጥተውለት "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" ሲለው ያም ሽባ ተፈውሷል፦
ማቴዎስ 8፥8 የመቶ አለቃውም መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ በቤቴ ጣራ ከታች ልትገባ አይገባኝም፤ ነገር ግን "ቃል ብቻ ተናገር" ብላቴናዬም ይፈወሳል።
ማቴዎስ 9፥2 እነሆም፥ በአልጋ የተኛ ሽባ ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፦ አንተ ልጅ፥ አይዞህ! "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" አለው።

"ጽርፈት" ማለት "ስድብ"blasphemy" ማለት ሲሆን ኢየሱስ፦ "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" ሲል ከጻፎቹ አንዳንዱ "ይህስ ይሳደባል፥ ከአንዱ ከአምላክ በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል? ብለው አሰቡ፦
ማቴዎስ 9፥3 እነሆም ከጻፎቹ አንዳንዱ በልባቸው፦ "ይህስ ይሳደባል" አሉ።
ማርቆስ 2፥7 ይህ ሰው ስለ ምን እንደዚህ ያለ ስድብ ይናገራል? ከአንዱ ከአምላክ በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል? ብለው አሰቡ።

ስድብ ብለው ያሰቡት "ኃጢአት ሊያስተሰርይ የሚችለው አንዱ አምላክ ነው" ብለው ስላሰቡ ኢየሱስ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ስለተሞላ የዕውቀት መንፈስ ስላለው በልባቸው እንዲህ እንዳሰቡ በመንፈስ ቅዱስ አውቆ፦ "ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ? አላቸው፦
ማርቆስ 2፥8 ወዲያውም ኢየሱስ በልባቸው እንዲህ እንዳሰቡ "በመንፈስ አውቆ" እንዲህ አላቸው፦ በልባችሁ ይህን ስለ ምን ታስባላችሁ?
ማቴዎስ 9፥4 ኢየሱስም አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አለ፦ ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ?

እነርሱ በልባቸው፦ "እራሱን አምላክ አርጎ ያስባልን?"That’s blasphemy! Does he think he’s God?” (New Living Translation) ብለው ያሰቡት አሳብ ክፉ አሳብ እንደሆነ ለማመልከት፦ "ስለ ምን በልባችሁ ክፉ ታስባላችሁ" አላቸው፥ ስለዚህ "ኢየሱስ አምላክ ነው" ብሎ ማሰብ ክፉ አሳብ ነው። ታዲያ ኢየሱስ ኃጢአት ሊያስተሰርይ እንዴት ቻለ? ካልን አምላክ ስለሆነ ሳይሆን የሰው ልጅ ነውና ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ሥልጣን የሰጠው አምላኩ ነው፦
ማቴዎስ 9፥6 ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ።
ማቴዎስ 28፥18 ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይ እና በምድር ተሰጠኝ።

"ሥልጣን ሁሉ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! በምድር ላይ ኃጢአትን የማስተሰረይ ሥልጣን የሰጠው አንዱ አምላክ ስለሆነ "ተሰጠኝ" በማለት ይናገራል፦
ሉቃስ 10፥22 ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል።
ዮሐንስ 5፥27 የሰው ልጅም ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው።

ምን ትፈልጋለህ? ሁሉም ነገር ከአብ የተሰጠው ነው፥ ለኢየሱስ ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ብሎ እንዲፈርድ ሥልጣን ያገኘው በስጦታ ነው። ኢየሱስ ከራሱ ምንም አልተናገረም፥ "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" ብሎ የሚለውን እና የሚናገረውን ትእዛዝ የሰጠው የላከው ነው፦
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፥ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።

ኢየሱስ እኮ እንዲፈውስ የጌታ ኃይል የሆነለት ሰው ነው፥ ከራሱ ምንም ማድረግ የማይችለው እና ከላከው እየሰማ "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" በማለት ይፈርድ ነበር፦
ሉቃስ 5፥17 እርሱም እንዲፈውስ የጌታ ኃይል ሆነለት።
ዮሐንስ 5፥30 እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ "እንደ ሰማሁ" እፈርዳለሁ። የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።

የላከውን ፈቃድ ለማድረግ እንጂ የራሱን ፈቃድ የማያደርግ ኢየሱስ ሲፈውስም በላከው ፈቃድ ብቻ ነው። ይህ "ኃጢአትህ ተሰረየችልህ" ብሎ እንዲናገር ለዚህ ሰው ሥልጣን የሰጠው አምላክ እንደሆነ የገባቸው ሕዝቡ ለኢየሱስ ሥልጣን የሰጠውን አምላክን አከበሩ፦
ማቴዎስ 9፥8 ሕዝቡም አይተው ተደነቁ፥ ለሰውም እንዲህ ያለ ሥልጣን የሰጠ እግዚአብሔርን አከበሩ።

የናዝሬቱ ኢየሱስ አምላክ በእርሱ በኩል ተአምራትን ያደረገበት ሰው ነበረ፥ እየፈወሰ ሲዞር አምላክ ከእርሱ ጋር ነበረ እንጂ እራሱ አምላክ አልነበረም፦
የሐዋርያት ሥራ 2፥22 የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ።
የሐዋርያት ሥራ 10፥38 እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና።

"ማስተሰረይ" ማለት "ይቅር ማለት" ማለት ነው፥ ኃጢአትን ይቅር ማለት አምላክ ካስደረገ ሐዋርያትም ኃጢአትን ይቅር ይላሉ፥ እናስ ሐዋርያት አምላክ ናቸውን? በፍጹም፦
ዮሐንስ 20፥23 ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፥ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል" አላቸው።

አምላካችን አሏህ ለመርየምን ልጅ ለዒሣ ግልጽ ተአምራትን ሰቶታል፦
2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣንም ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ

ሽባ መተርተር፣ ዕውር ማብራት፣ ለምጻም ማንጻት፣ ሙት ማስነሳት ግልጽ ተአምራት ናቸው፥ ለዒሣ ተአምራት የሰጠውን አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

14 Oct, 22:45


አርካኑል ኢማን "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ናቸው፥ "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ማለት "ዶግማዊ"dogmatic" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ

"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا

“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا

"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا

አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ

እዚህ አንቀጽ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ማለት "ሁለተኛ ወይም ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ" ሳይሆን የመጀመሪያ እና ዐቢይ የዲን ቅርንጫፍ ነው፥ "ዐቂዳህ ምንድን ነው? ሲባል "እርሱ ሁለተኛ እና ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ ነው" ብሎ ከመናገር በላይ የሚያሳፍር ነገር የለም። አምላካችን አሏህ ፈሣድን ከሚያስፋፉ ኢሕዋኑል ሙፍሢዱን ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

14 Oct, 22:45


ዐቂዳህ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا

"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ!  ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،

እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

14 Oct, 01:15


https://t.me/mahircomp123

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

14 Oct, 01:13


🎥በዚህ ቻናል የተለቀቁ የቪዲዮ ትምህርቶች:-
-------------------------------------------------------
1▸ ዕዝራ የአምላክ ልጅ አልተባለም ?
2▸ ምድርን ተሸካሚው ፍጥረት (ኑን)
3▸ አራቱ የእግዚአብሔር ተሸካሚዎች
4▸ አንዱን ለያሕዌ ሌላውን ለአዛዝኤል
5▸ ጂብሪል በኃይል ለምን ያዛቸው ?
6▸ የአላህ ቃል (ቁርኣን) ፍጡር ነውን ?
7▸ ሰላምን የማይፈልገውስ ማነው ?
8▸ ሴቷ አምላክ (አምልኮተ ማርያም)
9▸ በቤት ሰራተኛ የተዘረረው አምላክ !
10▸ ለትንሽ ጉድ ሆኖ የነበረው አምላክ
11▸ የዝሙት ልጅ ማግባት ይቻላልን ?
12▸ ጊዜያዊ ጋብቻ (ሙትዓ) ይፈቀዳል
13▸ የኢየሱስ ሙግት በራሱ አንደበት ¹
14▸ የኢየሱስ ሙግት በራሱ አንደበት ²
15▸ የኢየሱስ ሙግት በራሱ አንደበት ³
16▸ የጣዖታዊያን ትምህርት በክርስትና¹
17▸ የጣዖታዊያን ትምህርት በክርስትና²
18▸ አስቀድመን ለሲዖል ተፈጥረናል
19▸ በማኅፀን ውስጥ ያለው አይታወቅም
20▸ ነገረ-ሦስትነት (መደብለ-አምልኮ)
21▸ እውን ይህ ክርስትና በታሪክ የለም ?
22▸ የፍቅር አምላክ ወይስ የሽብር ?
23▸ የአላህ ሁለቱም እጆች ቀኝ ናቸው ?
24▸ አምልኮተ-ሊቃውንት በክርስትና
.
.
.
®Sαlαh Responds 🎙
▸ t.me/mahircomp123

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

12 Oct, 18:17


▮◁🄳🄴🄱🄰🅃🄴▷▮
«እውን ኢየሱስ አምላክ ነውን ?»

□ ነገ | እሁድ | ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ኢንሻአላህ።።
https://t.me/path_of_the_prophets
ሁሉም ጋር ሸር አድርጉ ማንም እንዳይቀር

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

12 Oct, 00:12


◆▮ትምህርት▮◆

"አምልኮተ ማርያም"።
"ማርያም ከሥላሴ በላይ ትመለካለች!"
ክፍል¹
◍ወንድም አብዱል ከሪም 
◍ወንድም ዒምራን
◍ወንድም ሳለህ
◍ወንድም አሕመድ
          

ክርስቲያን መሆን ጉዳቱና ጉዱ

11 Oct, 19:35


◆▮ውይይት▮◆

"ምልኩስናን አስመልክቶ ሌሎችም ርእሶች የተዳሰሱባት ትምህርት"

ወንድም ዒምራን
◍ ወንድም ሳለህ
         🅥🅢
◍ ወናችን እስቴማ
◍ ሌሎችም

1,270

subscribers

137

photos

122

videos