ባለራዕይ ወጣት

@msganabezemaye


፤ ራእይ ባይኖር ሕዝብ መረን ይሆናል፤ ሕግን የሚጠብቅ ግን የተመሰገነ ነው። "
(መጽሐፈ ምሳሌ 29:) @Blssed3
ለምክር, ለፀሎት እና ለማንኛውም መፅሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄ ☞ +251913129945

አጋር ቻናልች ➭ @yedestaye_elilta

YOUTUBE CHANNEL
https://youtu.be/UZMRCkiVgFI

ባለራዕይ ወጣት

22 Oct, 05:50


@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

29 Sep, 06:52


    
ይህንን እውነት  ለ 5 ሰዎች
🤳Forward ያድርጉ፡፡ 🙏
👇👇👇👇

🔱 #አለምን_የምናሸንፍበት_መንገድ

#ዳግመኛ ያልተወለደ ሰው ከወንድ ፈቃድ ብቻ የተወለደ ሰው አለምን አያሸንፍም ይህን አለም ወይም የዚህ አለም ክፋትን ማሸነፍ የሚቻለው ከእግዚአብሔር በመወለድ ነው፡፡

#ከእግዚአብሔር የተወለደ ከማይጠፍው ዘር የተወለደ በውስጡ አለምን ያሸነፍውን የክርስቶስ ዘር ወይም የአሸናፊነት ዘር ያለበት ሰው ብቻ አለምን ያሸንፍል፡፡

     #Share ያድርጉ🙏

#ለኔ_ህይወት_ክርስቶስ_ነው  

🔹🀄️🀄️ሉን 🔹
@msganabezemaye
@msganabezemaye

🔺 #share_ማድረጎን_እንዳይረሱ 🔺

ባለራዕይ ወጣት

28 Sep, 08:08


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_48

" ጸሎቴን ያልከለከለኝ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይመስገን ። " መዝ 66 : 20

#እግዚአብሔር ጸሎትን የምሰማ ብቻ ሳይሆን ሰምቶ መመለስ የምችልም  ነው ፤ ለሚናችሁ እግዚኤር ይስጣችሁ ብሎ የምሄድ የሰው ልጅ ነው እንጂ የእኛ አምላክ አይደለም ፤ የእኛ አምላክ የልጆቹን እንባ ና ፀሎት አይቶ ና ሰምቶ የሚመልስ ነው ።

# ስንት ጊዜ ማረኝ ብላችሁ በምህረቱ ምራችሁ በእርሱ ቸርነት ሊያጣፋችሁ ከመጣ ሀጢያት አለፋችሁ ። እኔ ግን እንደ መዝሙረኛው በእግዚአብሔር ምህረት ብዙ ማይታለፋ ቀናትን በምህረቱ አልፋ ዛሬ ለምስጋና በቅቻለሁ ።

#የእለቱ መልዕክቴ ጸሎታችሁን ለመለሰው ና ለሚመልሰው እንዲሁም ምህረቱን ከእናንተ ላላራቀው ይልቁንም በላያችሁ ላበዛው ለእግዚአብሔር ምስጋና ታቀርቡ ዘንድ ነው ።
                           
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

27 Sep, 09:31


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_47

" እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤ ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ ። "
መዝ 17 : 15

#አንዳንድ ሰው እኔ  ምሳዬን ሳልበላ ብዘል ያን ያህል ችግር የለውም ግን ቁርሴን መዝለል አልችልም ይላሉ ፤ በተቃራኒው ለሎች ደግሞ ቁርሴን ቢዘል ብዙም አይከብደኝም ግን መሳዬን ዘልዬ  መቆዬት አልችልም ይላሉ ።

#ነገር ግን አብዘኞቻችን ለስጋችን የሚያስፈልገውን ነገር ሰአቱን ጠብቀን እንደምንመገበው ሁሉ ለነብሳችን የእግዚአብሔር ቃል ና ፀሎት በእየለቱ እንመግባት ይሁን  ?

#ቡና ካልጠጣሁ ምንም ተነቃቅቼ ልሰራ አልችልም ካልጠጣሁ ብዥ ይልብኛል እንላለን ግን ክብሩን ተርበን ና ተጠምተን ክብርህን ካላየሁ አብሮነት ርቆኝ መኖር አንችልምና ራስ ግለጥልን ብለን  ጠይቀነው እናውቅ ይሁን ?

#የእለቱ መልዕክቴ የሚያልፈውን መብል ና መጠጥ ብቻ አንራብ ፣ አንጠማ  የማያልፈውን ሕይወትን የምያድሰውን የእግዚአብሔር ክብር እንራብ ፣ እንጠማ የሚል ነው ።

                               
  መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

25 Sep, 06:47


ፍቅር

ፍቅር እደዚ ነው እኔ አይቸዋለሁ፡
ብዙ ንብረት ነበር ባባቴ ቤት ሳለሁ፡
ጥጋቤ በዛና ከዛ ከሞቀው ቤት፡
አባቴን በትእቢት እዲህ ተናገርኩት፡
በላ ድርሻየን ስጠኝ ራሴን ልቻልበት፡
እሂን መጠየቄ የለብኝም ስተት፡
አሁን ስጠኝና ቶሎ ልሂድበት፡
አባቴ በኔ ላይ እጂጉኑ ቢያዝንም፡
ኧረ የድርሻየን አልከለከለኝም፡
ወጣሁ ካባቴ ቤት ከሞቀው ጓዳየ፡
በገንዘብ በሀብት በራሴ ታብየ፡
ያላዩትን ሀገር ናፋቂ ሆኩና፡
የምታምር መስሎኝ አለም ስትለኝ ና፡
ገዘቤን በተንኩት ውርሴ መና ቀረ፡
ሰውም በኔ ስራ እጂጉን አፈረ ፡
ድህነት ወረሰኝ እጂግ ተጓሳቆልኩ፡
እኔም ከራሴ ጋ እዲሁ ተማከርኩ፡
እዴው ባባቴ ቤት ተመልሸ ብሄድ፡
እደልጂነቴ ባይኖርም መወደድ፡
ልጂነቱ ቀርቶ እደ ባርያው ልሁን፡
ኧረ ይሻለኛል ናፈኩኝ ያቺን ቀን፡
አባቴ ሲያየኝ ገና ከሩቁ፡
የቆሸሸውን ልብስ ቶሎ አውልቁ፡
የደለበውን ለልጀ ረዱ፡
የጠፋው ልጀ ተመለ ሰልኝ፡
እያለጮኸ በይኖቹ እያየኝ፡
ታዲያ ፍቅር ከዚ በላይ አለ፡
በደልን ሳይቆጥር ባለም ላይ ያየለ፡
በደሌን ሳይቆጥር እዲህ የወደደኝ፡
የሰማዪ አባቴ ስሙ ይክበርልኝ፡፡
❤️ፍቅር በደልን አይቆጥርም!

         ለሌሎች እንዲደርስ share አድርጉ

@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

24 Sep, 06:20


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_46

" ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው ።" ሮሜ  13 : 10

#ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ነው ፤  ለምን ከተባለ ማንኛቸውም መጽሐፍ ቅዱሳዊ  ሕጎች መሠረታቸው ፍቅር ነው ፤ ሰውን ና እግዚአብሔርን በመውደድ ላይ የተመሠረቱ ናቸውና ።

#ለምሳሌ ፦ አንድ ሰው እግዚአብሔርን የምወድ ከሆነ ከእርሱ ውጪ ለላ አማልዕክት አታምልክ የምለውን ሕግ ይፈጽማል ። ሰውን ወይም ባለእንጀራውን የሚወድ የሰውን ነገር አይሰርቅም ፣ የሚወደው ከሆነ አይዋሽም  እውነትን ይናገራል ።

# እኛ ራስ ወዳድ ስለሆን የእግዚአብሔር ሕግ መጠበቅ አቃተን እንጂ ፍቅርማ ቢኖረን ሕግን መጠበቅ ቀላል ነበረ ።

#የእለቱ መልዕክቴ ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ነውና  በፍቅር እንመላለስ  ፍቅር ከየትኛውም የፀጋ ስጣታ ይበልጣልና በፍቅር እንኑር የምል ነው ።
                                  
  መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

18 Sep, 05:18


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_45

" አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ ። "
ሰቆቃው ኤርምያስ 5 : 21

#እግዚአብሔር ራሱ ወደ እርሱ ካልመለሰን እኛ በራሳችን አቅም መመለስ አንችልም ፤ ስለዚህ ከእርሱ መስመር ወጥተን ከሆነ መልሰን ብለን እንጠይቀው ።

#ያነ ለመንፈሳዊ ነገር ገና ልጅ ሳለን ወደ ነበር የፀሎት ና የቃል ጥማት ና ርሃብ መልሰን እንበለው ።
አቤቱ ወደ ቀድሞ ፍቅራችን ፣ መከባበራችን ና መደማመጣችን መልሰን ፤ ዘማናችንንም እንደ ቀድሞ አድስ ።

#እግዚአብሔር ወደ እርሱ መንጌድ ና ሀሳብ ይመልሰን  ፤ የያነውን ፍቅር ዳግም ያፋስስብን ። አሜን
                             
  መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

17 Sep, 06:28


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_44

" አቤቱ ጌታችን፥ ስምህ በምድር ሁሉ እጅግ ተመሰገነ፥ ምስጋናህ በሰማዮች ላይ ከፍ ከፍ ብሎአልና "
መዝ 8 : 1

#እግዚአብሔር  በክብሩ ና በግርማው ከጥንትም ጀምሮ የታወቀ ነው ፤ ከእርሱ  ጋር በክብር ይሁን በምስጋና ለላ የምስተካከለው ማንም የለለው ነው  ።

#በምድር ሁሉ እጅጉ የተመሰገነ ምስጋውም በሰማያት ሁሉ ላይ ከፍ ብሎ የታየ ከእግዚአብሔር ለላ አናውቅም  ።

#የእለቱ መልዕክቴ ይህን በምድር ሁሉ የተመሰገነውን በሰማያትም ሁሉ ላይ ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን ስም እኛም በኑሮአችን ና በሕይወታችን አልቀን እናሳይ የምል ነው ።  ተባርካችሃል !!

                               
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

16 Sep, 04:04


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_43

" በዚህ የምትኖር ከተማ የለችንምና፥
ነገር ግን ትመጣ ዘንድ ያላትን እንፈልጋለን።" ዕብ 13:14

#አሁን ያለንባት አገር ወይም ከተማ የዘላለም መኖራችን  አይደለችም ። ይች ያለንባት ከተማ የእንግድነት ጊዛችን ማረፋያ እንጂ የእኛ አይደለችም ፤ የእኛ አገር በሠማይ ነው ፤ እኛ የሚትመጣዋን አዲስቷን ኢየሩሳሌምን በናፍቆት እንጠባበቃለን ።

# ይች አሁን በእግድነት ያለንባት ከተማ ደስታ ና ሀዘን ፣ ማግኘት ና ማጣት ፣ ዝቅታ ና ከፍታ የሚፈራረቁባት ናት ፤  የሚትመጣው አዲስቷ ከተማ ግን ሀዘን ና ለቅሶ የማይሰማባት ዘውተር በጉ ብርሃኗ የሆናት ናት ።

#የእለቱ መልዕክቴ የሚትመጣዋን አዲስቷን ከተማ እየሩሳሌምን በናፍቆት እንጠብቅ የሚል ነው ።
#አሜን ማራናታ ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና

                          
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

14 Sep, 05:12


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_42

#ለእግዚአብሔር ዝማሬ ና አምልኮ  በሚናቀርብበት ጊዜ ፍፁም ደስታ ከእርሱ የሆነ ውስጣችንን ና መንፈሳችንን መቆጣጠር ይጀምራል ።

#ነፍሳችን በጣም  የሚትደሰተው መቼ ነው ? ካልን ስጋዊ ምኞቶቻችን የተሳኩ እለት ሳይሆን  በአምላኳ ሕልውና  ተወርሷ እርሱን ከፍ ስታደርግ ና ስታመልክ የዋለች እለት ነው ።
ለዚህ  ነው መዝሙረኛው ዝማሬን ባቀርብሁልህ ጊዜ ከንፈሮቼ ደስ ይላቸዋል፥  አንተ ያዳንሃትም ነፍሴ ያለው ።

#የዛሬ መልዕክቴ በየትኛውም ጊዜ ፣ ሁኔታ ና ቦታ ለአምላካችሁ የሚሆን ዝማሬ ከአፋችሁ አይጥፋ ፤ ምክንያቱም በዚህ በቅጽበት በምትለዋወጠው አለም ና  ሕይወት ውስጥ የነፍስ ደስ ማግኘት የምቻለው እርሱን በማክበር ና በማምለክ ውስጥ ነውና ።
                                 
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

13 Sep, 05:55


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_41

" ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል ። "
መዝ 63 : 3

#መዝሙረኛው ዳዊት ለምን ምሕረትህ  ከሕይወት ትሻላለች አለ ? ካላችሁ  በሕይወት ለመቆየት ራሱ ያለ እግዚአብሔር ምሕረት ስለማይቻል ነው ።

#ያለ ምሕረቱ ሕይወት የለም ፤ ሕይወት የሚትቀጥለው በእግዚአብሔር ምሕረት ነው ።
ያለነው ና እየኖርን ያለነው ሀብት ፣  ንብረት ና እውት ስላለን አልያም ጤነኛ ስለሆንን ሳይሆን ምህረቱ በእኛ ላይ ስላላለቀ ነው ።

#ለዚህ ነው መዝሙረኛ ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል ያለው ፤ እኛም እግዚአብሔርን ስለ ምሕረቱ ሊናመሰግነው ይገባል ።
እግዚአብሔር ሆይ ስለበዛው ምሕረት ክብር ና ምስጋና ይሁንልህ ። አሜን
                               
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

12 Sep, 07:04


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_40

" የላከኝም ከእኔ ጋር ነው፤ እኔ ደስ የሚያሰኘውን ዘወትር አደርጋለሁና አብ ብቻዬን አይተወኝም አላቸው ። "
ዮሐ 8 : 29

#የላከን ፣ የጠራን ና እንድናገለግለው የሾመን እግዚአብሔር በቃ ልካችሃለሁ ፣ ጠሪቻችሃለሁኝ አገልግሉኝ ብሎ ብቻ አይተወንም ሁል ጊዜ እርሱ የእኛ ጋር ነው ።

#ይህን የተናገረው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የላከው አብ እንደሆነና የተላከውም አባቱ የለካውን አጀንዳ ፈጽሞ ደስ እንዲያሰኝው እንደሆነ ይናገራል ።
አባት ደግሞ ደስ የሚያሰኘውን ና በፈቃድ የሚሄደውን ልጅ መቼም ቢሆን አይተወውም ።

#በቃ  እየተነተንኩኝ አላበዛባችሁም  ብቻችሁን አይደላችሁም አብ ከእናንተ ጋር ነው ።
ብቻዬን አይደለሁም አብ ከእኔ ጋራ ነው !! 
#ሀለ_ሉያ_ሀለ_ሉያ_ሀለ_ሉያ_ሀለ_ሉያ_ሀለ_ሉያ
                        
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

11 Sep, 05:20


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_39

" የአይሁድ ጠላቶች ሊሠለጥኑባቸው በነበረው ቀን፥ አይሁድ በጠላቶቻቸው ላይ እንዲሠለጥኑ ነገሩ ተገለበጠ ። " አስ 9 ፡ 1

#በእግዚአብሔር ጥበቃ ውስጥ ያሉት ሰዎች ላይ ጠላት  በእነርሱ ላይ የመሰልጠን ሰልጣን የለውም ።
አይሁድን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ጠላት በሀማ በኩል ቢነሳም ልያጠፋቸው ግን አልቻለም ይልቁን ለራሱ ጥፋት  አመጣ  ፤ ጠላት (devel) በአይሁድ በኩል ክርስቶስ እንዳይመጣ ነበር ድብቁ አላማው አልተሳካለትም እንጂ ።

#ዛሬም  ይመኛታል እንጂ ጠላታችን ዲያብሎስ በክርስቶስ ያሉት ምንም ሊያደርግባቸው አይችልም  ፤ በእርሱ ላይ  እንሰለጥናለን እንጂ በእኛ ላይ የመሰልጠን ስልጣን የለውም ።
#ጠላት አጠፋሀለሁ ስልህ ወኔ ጉደ ብለህ አትደንግጥ እንዶም የክብር ቀን  ከፊቴ አለ ብለህ ምሆነውን አሳጣው ።

#የዛሬው መልዕክቴ በክርስቶስ ለሆናችሁ ጠላት በእናንተ ላይ ያሰበው ክፍ አሳብ ወደ ራሱ ተገልብጦበታልና አትስጉ ዛሬ ለእናንተ የደስታ ና የድል ቀን ነውና ።
ለአይሁድም ብርሃንና ደስታ ተድላና ክብርም ሆነ ። አስ 8 : 16
                              #በመልካሙ
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

10 Sep, 05:39


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_38

" ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥
እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ። "
1ኛ ዮሐ 4 : 8

#የትኛውም ለፍቅር የምንሰጠው definition እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፤ የምለውን በፍፁም ልተካው አይችልም ። because  እግዚአብሔር ፍቅርን የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን ፍቅር ራሱ እግዚአብሔር ሰለሆነ ነው ።

#ፍቅር እግዚአብሔር ነው ካለን  ደግሞ አንድ ሰው ፍቅር የለውም ካልን ያ ሰው እግዚአብሔርን አይውቅም እንዲያውም እግዚአብሔር የለውም  ።

#እንዴ በጌታ ሆኖም እያመለከውም እያገለገለውም ከሆነ እግዚአብሔርን አያውቅም ማለት ነው ?  አዎ አያውቅም ስጀመር በፍቅር የማይመላለስ ሰው በጌታ ነው ማለት ራሱ አሳፍር ነገር  ነው ፤ ፍቅር የለለው ሰው አምልኮ ና አገለግሎት Artificial ነው ።

#የዛሬው መልዕክቴ በፍቅር እንኑር ፤ በፍቅር ከኖርን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ይኖራልና ። እርሱ እንደወደደን እኛም እርስ በራስ አጥብቄን እንዋደድ ። የጌታ ፀጋ ና ፍቅሩ ይብዛላችሁ ። አሜን !!
      
                         
መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

09 Sep, 04:52


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_37

"  የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው "
ምሳሌ 1 : 7

#የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት እንጂ ፊደልን መቁጠር አይደለም ።
የትኛውም አይነት እውቀት ና ጥበብ እግዚአብሔር መፍራት በውስጡ የለለው ከሆነ ምንም ዋጋ የለውም ።

#እግዚአብሔር የምባል የለም በምርመሬ ደርሸበታለሁ  ከምል  ምሁሩ ነኝ ማይም በዚች አለም እውቀት ና ጥበብ ማይሞ የሆነ ግን እግዚአብሔር አለ ብሎ የምያምን ሰው ይሻላል ።

#እግዚአብሔርን መፍራት ማለት ለእግዚአብሔር ትዕዛዝ ተገዥ መሆን ነው ። በምትፈራው ና በምታከብረው ሰው ፊት እርሱ የማይወደውን ነገር ለማድረግ እንደማትደፍር ሁሉ እግዚአብሔርን የምትፈራው ከሆነ እርሱ የማይወደውን ነገር ለማድረግ አትሞክርም ። Because የእግዚአብሔር አይኖች በስፍራ ሁሉ ናቸው ።

#የዛሬው መልዕክቴ  ሁሉም እንቅስቃሳችሁ እግዚአብሔርን በመፍራት ና በማክበር ውስጥ ይሁን ።
የምር ወዳችሃለሁ ተባረኩልኝ !!
                       
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

06 Sep, 06:57


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_36

"  አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና ። "
ገላ 6 : 3

#አንዳንዴ ምንም ሳንሆን ምንም የሆነን ስመስለን  ምንም እንዳልሆነ የምናውቅበት ጊዜ ስመጣ ምንም እንዳልሆንን ይገባናል ።  ትግስተኛ የሆንክ ስመስልህ ትግስተኛ መሆንህ የሚረጋገጠው ትዕግስትህን የሚፈትን ነገር ስገጥምህ ነው ።
ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ የምመስለው ሰው ራሱን ያስታል ።

# ልጅ ሳለው የሕንድ ፊልሞችን አይ ነበርና ፤  ፊልሙን ካየሁ ቦሀላ ያየሁትን አክተር ለመምሰል እንዴ እርሱ እራሜድ እበላ ና አድርግ ነበር ። አንዴ ሻሩካን ለላ ቀን ሰለማን ካን ለመሆን እጥር ነበር ግን እነርሱን ለመሆን ካለመቻለ በላይ ያጣሁት የራሴን ማንነት ነበር ።

#አንዳንዴ የሆነ መንፈሳዊ ፕሮግራም ተካፍላችሁ ስትወጡ እንዴ እናንተ ጻድቅ እግዚአብሔርን የምፈራ የለለ ይመስላችሃል ፤ ሀጢያት የምባል ነገር ነክታችሁ የምታውቁ ይመስላችሃል ። ግን መስላችሁ ነው እንጂ እናዳልሆናችሁ ካዛ ቦታ ስትወጡ ታውቁታላችሁ ።

#የዛሬው መልዕክቴ በአጭሩ ምንም ሳትሆነ የሆናችሁ ለመምሰል አታስመስሉ ፤ ራሳችሁን አታታልሉ ።
                               
መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

05 Sep, 07:38


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_35

"  የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ ፤ "
መክ 12 ፡ 1

#አሁን ያለህ አቅም ጉልበት ፣ ጊዜ ፣ ጤና እስከ መጨረሻው ካንተ ጋር ላይዘልቁ ይችላሉ ።  ሰጣንም እግዚአብሔር ልገለገልና ልያገለግለው የምፈለግው ወጣት ነው ። NOT FORGET እግዚአብሔር በአካል ብቻ ሳይሆን በመንፈሱም ወጣት የሆነ ሰው ይፈልጋል  ።

#ጉልበትህ ሳይከዳህ አሁን  በሙሉ  ሀይል ወጣትነትህ ለእግዚአብሔር ብትሰጥ ከሀላ ሀላ ፀፀት ትድናለህ ።
ይህን አባባል አልቀበለው ክርስቲና ና ሱፍ ከ40 አመት ቦሀላ ያምራሉ የምለውን ፤ ክርስቲንማ የምያምረው በትኩስ ሀይል ራስን ለእግዚአብሔር ስያስገዙ እንጂ በከዘራ በአራት እግር እየሄዱ ስኦልን ስለፈሩ ብቻ የምከተሉት ልሆን አይገባም ።

#እናም በጉበዝናችሁ ወራት የፈጠራችሁ ፈጣሪ የፈጠራችሁን አለማ አስብ ደግሞ ለእርሱ ኑሮ ምክንያቱም ሁሉም አሁን እንዳለ ሆኖ አይቀጥልምና ።
                             
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

04 Sep, 06:20


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_34

"  ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን ። "
ሮሜ  11 : 36

#ሰው ሆይ ሁሉም የሆነው ከእግዚአብሔር ፣ በእግዚአብሔር ና ለእግዚአብሔር ነው ።  Not include ክፍ ነገር for example ሀጢያት  ፣ ክፍት ፣ ሰጣን ፤ እግዚአብሔር ሁሉን ስፈጥር መልካም ና የምጠቅም  ለክብሩ መገለጫ እንዲሆን ነው እንጂ ክፍ ና መልካም ብሎ ለይቶ ልዝናናባቸው አይደለም  ።

#ወደ ዋናው  ነጥቤ ስመጣ አንተ የተፈጠርከው ከእርሱ ፣ በእርሱ ና ለእርሱ ክብር እንዲትኖር ብቻ ነው ። አይ እኔ ከእርሱም ፣ በእርሱም ለእርሱም ክብር አይደለም የሚትል ከሆነ ትልቁ አባትህ ሰጣን እጁ ዘርግቶ የውድቀቱን ጽዋ ለአንተም ልያስጎነጭህ በስስት እየጠበቀህ ነው ፤ ይስጥህ ብዬ አልረግምህም ከዚህ ከንቱ ሀሳብ ይጠብቅ ብዬ ልፀልይልህ እንጂ  ።

#የዛሬው መልዕክቴ በአጭሩ የተፈጠላችሁት ከእርሱ ፣ በእርሱ ና ለእርሱ ክብር እንድትሩለት ነውና ፤ መኖር የሚያስችላችሁን ፀጋ እርሱ ራሱ ያብዛለችሁ ። አሜን !!

                                  
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

03 Sep, 08:00


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_33

" ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ ።  "
መዝ 84 : 10

#ካለ እርሱ ከሚታሳልፋት ብዙ ቀናቶች ይልቅ ከእርሱ ጋራ የሚታሳልፋት አንዲቷ ቀን ብዙ ዋጋ ና ትውስታ አላት ።
በሀጢያት ከሚታገኙት ጊዛዊ ደስታ ይልቅ እንኳን ተከብራችሁ ይቅርና በቤቱ ተጥላችሁ ብትኖሩ እንኳ ታተርፋላችሁ እንጂ አትከስሩም ።

#ወዳጆቼ የዛሬው መልዕክቴ በየትኛውም ሁኔታ ፣ ጊዜ ና ቦታ ይሁን ያለ እርሱ አብሮነት አትሁኑ ፤ ከምንም ና ከማንም በላይ ለእናንተ የምያስፈልጋችሁ እግዚአብሔር ብቻ ይሁን ።
     
                             
  መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉
@msganabezemaye
@msganabezemaye

ባለራዕይ ወጣት

01 Sep, 09:26


#የእለቱ_መልዕክት_ቀን_32

"  እግዚአብሔርን እንዲያውቁ በግልጥ ይናገራሉ፥ ዳሩ ግን የሚያስጸይፉና የማይታዘዙ ለበጎ ሥራም ሁሉ የማይበቁ ስለ ሆኑ፥ በሥራቸው ይክዱታል ። "
ቲቶ 1 : 16

#ብዙዎቻችን  እግዚአብሔርን ያወቅነው ይመስለናል እንጂ አላወቅነውም ። ስለ እግዚአብሔር ቢንጠየቅ ቡዙ ተትነን የምንናገረው ነገር አለን ማለት እግዚአብሔርን እናውቀዋለን  ማለት አይደለም  ፤ ምክንያቱም ስለ እግዚአብሔር  ማወቅ ና እግዚአብሔርን ማወቅ ስለምለያዩ ማለት ነው ።

#ስለ እግዚአብሔር የሚያውቁ ስለ እርሱ እውቀት ብቻ ያላቸው ሰዎች ናቸው ፤ ያውቁታል ግን ያን ያወቁትን ነገር አይኖሩትም እናውቀዋለን ብለው ብናገሩ እንኳ መጽሐፍ አውቀው የማይኖሩትን በተግራቸው የማይገልጡትን   ካህድዎች ናቸው ይላል ።

#በትክክል እግዚአብሔርን ማወቅ ማለት   ፦ እርሱ ቅዱስ ነው ከሰውም ቅድስናን ይፈልጋል የምል ነገር ስለ እርሱ ካወቅ ያን መቀድስ ያስፈልጋል የሚለውን እርሱ ከማይፈልገው ነገር በመለየት በተግባር ከገለጥከው በእውነትም እግዚአብሔር የቅድስና አምላክ መሆኑ ገብቶሃል ማለት ነው ።

#የዛሬው መልዕክቴ እግዚአብሔርን በአንደበታችን ብቻ የምናብራራው ሳንሆን ኑሮአችንም እርሱ የምያብራራው ይሁን የምል ነው ። ምክንያቱም በአንገበታችን ያብራራነውን የማንኖረው ከሆነ ፣ የማንታዘዘው ከሆነ ፣ የሚያሳፍር ሕይወት ካለን በአንደበት የተናገርነውን በስራችን እናፈርሰዋለንና ። #እግዚአብሔር የተናገርነው ና ያወቅነው ነገር ኖሬን ማሳየት እንድንችል በፀጋው ይርዳልን ። አሜን
                                    
   መልዕክቱን ለለሎች #share  አድርጉ 🙏
          ይህን ቻናል   join 👉

@msganabezemaye
@msganabezemaye