🌹...ክፍል 10...🌹
.
እያልኩ ከግቢያቸው በር ላይ በሀሳብ መወዝወዝ የጀመርኩ ሳይታወቀኝ ሰፈር ደረስኩ።
ውስጤ ሌላ ኤፍሬም ያለ እስኪመስለኝ ከትናንት ማታ ጀምሮ ቃልኪዳን አምናህ ነውና የተኛችው ጫፏን እንዳትነካት እያለ ሲሞግተኝ የነበረ አንድ ሌላ ስሜት እኔ ያሻኝን አስቤ ፍቅርን ከስሼ እስካበቃ በጥሞና ሲያደምጠኝ ቆየና እንደጭረስኩ ድንግገት ተከስቶ •••
የፈለገ ቢሆን ማታ አግኝተኻት ጥዋት አፈቀርኩሽ ! የኔ ሁኚ ስትላት ማመን ቢከብዳት ጭራሽ ሹፈት እና ስላቅ ቢመስላት በሷ አይፈረድም። አንተም አሁን ውስጥህ የተቀጣጠለው ስሜት በውሃ የሚጠፋ ግዚያዊ እሳት ይሁን ምንም የማያጠፋው እውነተኛ ፍቅር ለመለየት ግዜ ያስፈልግሀል።
ምን አጣደፈህ•••? እውነቷን ነው እኮ ቃል •••በጣም ተጣደፍክ እኮ! ቆይ ያንተ ካላት የት ትሄዳለች•••? ተረጋጋ ኤፊ ተረጋጋ •••እያለ ሲሞግተኝ ጆሮዬን አልይዘው አልደፍነው ነገር ንግግሩ ከውስጤ እንጂ ከደጅ አይደለምና ተቸገርኩ።
አይ ቃል እሷ ጨቀጨከኝ ትላለች ። እኔ ኤፍሬም አንድ ሆኜ ሳለ እኩል ሁለት ቦታ ሰንጥቃ ከራሴ ጋር እያጨቃጨቀችኝ እንደሆነ አንድ ቀን ይገባት ይሆናል እያልኩ ባጃጄን በር ላይ አቁሜ ገባሁና ፍራሼ ላይ ተጠቅልዬ ተኛሁ።
እኔና ቃል ከሷ ካልመጣና ግድ ካልሆነብኝ በስተቀር በስተቀር በየቀኑ አገኛታለሁ። አብረን የተወሰነ ሰአት አሳልፈን እንለያያለን።
ከዛች ቀን በኋላ በየቀኑ ሁሌም ባገኘኋት ቁጥር •••እንደማፈቅራት፣ ቀሪ ህይወቴን በሙሉ ከሷ መለየት እሷን ማጣት እንደማልፈልግ ስልነግራት የመሸም የነጋም ቀን የለም።የሷ መልሶች ግን እጥር፣ ቁጥብ ያሉ ናቸው። ቃልዬ የውስጧን ስሜት ዘክዝካ በግልፅ የማትናገር ልጅ ነች ። ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ከአንደበቷ ይልቅ ሁኔታዋ አስተያየት እና ስሜቷ ነበር የኔ እንደሆነች የሚነግረኝ።
የኔ ፍቅር ስላት ያንተ አይደለሁም የእናት እና የአባቴ ነኝ ማለቷን ትታ ወዬ ኤፍዬ ማለት የጀመረችባትን ቀን መቼም አረሳትም ። እንደዛ ማለት ከጀመረች ሁለት ሳምንት ሆናት። ቢሆንም የፍቅር ጥያቄህን ተቀብያለሁ ፣ ያንተ ሆኛለሁ፣ ብላ በአንደበቷ እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ። በቃ ያንን መስማት እና ማረጋገጥ ሁሌም እፈልጋለሁ።
ቃልዬ አውቃለሁ የኔ ነሽ ግን ከአንደበትሽ መስማት እፈልጋለሁ እባክሽ ንገሪኝና ልቤን አሳርፊያት ስላት •••
"እንዴ ኤፍዬ እቺ ልብህ ዛሬም እየዘለለች ነው እንዴ ኪኪኪኪኪ" በቃ ትስቃለች ። እኔን እያስጨነቀች መሳቋ ያናድደኝ እና እንደማኩረፍ እላለሁ። ያኔ መለስ ትልና•••
"እሺ ኤፍሬሜ እንድነግርህ ከፈለክ ደግመህ ጠይቀኝ?"
"ምንድን ነው እምጠይቅሽ?"
"በቃ የባለፈው ጥያቄህ ግዜ ስላለፈበት አሁን ያለህን ስሜት ትክክለኛውን በደንብ ንገረኝና ድጋሚ ጠይቀኝ !" ትለኛለች።
የልቤን ያንጀቴን ፍቅርና መውደዴን ፣ ስስይና ናፍቆቴን ሁሉ አንድ ባንድ ስነግራት ምስጥ ብላ ስታደምጠኝ ትቆይና •••
"እ ንገሪኛ •••?" ስላት።
" አይ ኤፍዬ•••••" ትልና ያን ፍልቅልቅ ሳቋን በረጅሙ ትለቀዋለች !።
ወንዝ እያሳሳቀ ይወስዳል እንዲሉ እሷ እየሳቀች እኔ አበቃልኝ።
አይደለም ገንዘብ እና ጉልበቴን ፣ አይደለም ሀሳብ እና ማንነቴን ነፍሴን እስከመስጠት የምሳሳላት የልቤ ንግስት ሆና አረፈችው።
እሷ አጠገቤ ስትኖር እና ሳትኖር ያለኝ ማንነት ተራራቀ። ሲላት ብዝት ትልልኝና በፈለኳት ሰአት ሁሉ አገኛታለሁ። ሲላት ጥፍት ፣ ድርግም ፣ ስልካንም ጥርቅም ታደርገውና ነፍሴን በናፍቆት ሲቃ ታዋትታታለች ።ከሁሉም በተለየ ሁኔታ እኔ አጠገብ ሆና የማታናግረው አንድ ስልክ ናላዬን ያዞረው ጀምሯል። ማነው•••? ምንድን ነው? ለምን እንደሌሎቹ ስልኮች አጠገቤ ቁጭ ብለሽ አታናግሪም ብያት አላውቅም ። ልላትም አልፈልግም። ምክንያቱም ቃልዬ ጨቅጫቃ ወንድ አትወድም።
እሷ ምንም ታድርግ እኔ ውስጥ ያለው ፍቅር ሀይሉን እየጨመረ ፣ አጠገቤ ስትኖር በፍቅር እያሰከረ፣ ሳትኖር በናፍቆት ልብና አንጀቴን እየቦረቦረ ••••ፍቅር በዘፈን ይብስ እንደሁ እንጂ ላይቀንስ ላይወጣ ነገር•••
ብክን ••• ብክንክን ፣ ብትን••• ብትንትን
ያደርጋል ወይ መውደድ••••? ያደርጋል ወይ ፍቅር የሚል ዘፈን ••• በየመንገዱ ያዘፍነኝ ጀመር ...
በቃ ከሷ ውጪ ማሰብ፣ ከሷ ውጪ ማውራት፣ እሷ ጋር ካልሆነ ማንም ጋር መሄድ ከማንም ጋር መዋል አስጠላኝ።እሷን ለማግኘት ስል የማታ ስራዬን ወደ ቀን ቀየርኩት።
ለስራ ስወጣ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት በኔ ባጃጅ ላይ በኮንትራትም በመደበኛው ሂሳብም ወደፈለገበት አቅጣጫ ለመሄድ የኔን ባጃጅ የሚጠቀም ማንኛውንም ግለሰብ በእኩል አይን ማየት ቢኖርብኝም ወደነቃል ዩንቨርስቲ አቅጣጫ የሚሄድ ተሳፋሪ ግን ለኔ ንጉስ ነው። በኮንትራት ሂሳብ ከሆነ ከየትኛውም የድሬ ዳዋ ሰፈር ወደ ግቢ አቅጣጫ ለሚሄድ ሰው ግን ሂሰቤ ቅናሽ ነው።
እዛ ሄጄ ቃልን ባላገኛት እንኳን እዛ አከባቢ ደርሼ ያለችበትን ግቢ አይቼ መመለስ ልዩ ደስታ ይሰጠኛል።
የሚያስተውለኝ ተሳፋሪ የለም እንጂ ቢኖር ወደ ግቢ ስሄድ የማሳየው ፈገግታ፣ ተሳፋሪውን የማጫውተው ጫወታ፣ባጄጅ ውስጥ የምከፍተው ሙዚቃም ፣ የማስከፍለው ሂሳብም ከሌላው ይለያል። እስካሁን አላጋጠመኝም እንጂ አንድ ቀን ወደ ግቢ ወይም ወደዩንቨርስቲው አከባቢ ያደረስኩት ያው ሰው በሌላ ግዜ ሌላ ቦታ እንዳደርሰው ቢሳፈር••••" ሹፌር ምነው ባለፈው ስትስቅ ስትጫወት አልነበር እንዴ ዛሬ አኩርፈሀል በሰላም ነው•••? ችግር አለ እንዴ•••? " ብሎ መጠየቁ የማይቀር ነው።
የምን ችግር እንዲህ ያደረገኝ ፍቅር ነው እለው ይሆን ? የጠየቀኝ የለም እንጂ እለዋለሁዋ! ቃልዬን እንዴት እደማፈቅራት ቀኑን ሙሉ ባወራ መች ይሰለቸኛል። ምናልባት የሚሰማኝ ካልሰለቸው በስተቀር እኔ አይሰለቸኝ።
ነገር ግን አብሮኝ ለሚኖረውና በጣም ለምወደው ጓደኛዬ እስካሁን ስለቃልና ስለኔ ትንፍሽ አላልኩም።
ብዙ ግዜ በተለይ " ኤፊ ምነው እንቅልፍ እንቢ አለህ እንዴ?" ብሎ ሲጠይቀኝ ልነግረው ይዳዳኝና•••
ገና ••••••" አንድ ቀን ሸኝቻት ስንሰነባበት ፍቅር ሲያደናብረው አቅጣጫ በሳተው ከንፈሬ ከሳምኩት ከግማሽ ከንፈሯ ውጪ እስካሁን ምኗንም አልነካሁም" ብዬ እንደተናገርኩ •••
" እና እስከዛሬ ከቃል ጋር ምንም አላደረጋችሁም ኤፊ ? ፈዘዝክ፣ ቀዘዝክ ፣ቀዘቀዝክ እያለ
ወቀሳ አይሉት ሙገሳ፣ ምክር አይሉት መፈክር •••• ብቻ •••••" ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው እንዲሉ የፍቅሬን ክብደት ሳይሆን የኔን ፈዛዛነት እያነሳ የሚያዥጎደጉድብኝን ያን ምላሱን አስበውና እፈራለሁ። ይቅርብኝ ቃልዬ እንዴት በፍቅር እንደነደፈችኝ •••? በዚች አጭር ግዜ ውስጥ ከምን ውስጥ አውጥታ ምን ውስጥ እንደከተተች እንኳን ለሱ ላብራራለት እና ላስረዳው ለራሴስ መች በቅጡ ገባኝ ! ይቅርብኝ !" እልና መናገሬን እተወዋለሁ።የውስጤን ትኩሳት ከራሴ ጋር ብቻ እያወራሁ መታመሜን ቀጥያለሁ።
አይ ቃልዬ እንዴት እንዴት ነው ያፈቀርከሽ ግን•••? ሰው ለካ እንደዚህ በፍቅር ጨርቁን ጥሎ ብን••• ብትን •••ብትንትን ይላል። ግን ህመሙ ደስ ይላል። እየታመሙ መደሰት ፣ እየተደሰቱ መታመም የሚቻለው በፍቅር ብቻ ነው። ሀያ አምስት አመት ሙሉ ስኖር ይሄን ፍቅር አላውቀውም ።
50 ላይክ ቡኋላ ክፍል 11 ይለቀቃል🌹
𝗝𝗼𝗶𝗻 𝘂𝘀
https://t.me/mentalebe
https://t.me/mentalebe