ላገባችሁም ላላገባችሁም
<< አዎ ልክ ልኩን ንገሪው, ልኩን አሳይው, ደግ አደረግሽ, ዝም እንዳትይው, ፍርድ ቤት እንገትረዋለን, እንዴት ቢንቀን ነው, ማንነታችንን አላወቀም >> የሚል ዘመድ ማለትም እህት ወይም ወንድም አንዳንዴም ወላጅ ካለሽ ትዳርሽ ፈርሷል:: ወላጆች ብዙ ጊዜ እንደዚያ አይሉም::
ማናችንም ቢሆን ብሶታችንን ወደሚያደምጠንና ወደሚያዳምቅልን እንሄዳለን:: ልክ ቁስል ሲያኩት እያስደሰተ እንደሚስፋፋውና የዝንብ መቀለጃ እንደሚሆነው የትዳር ውስጥ ትናንሽ ግጭቶችን ወደ ሚያዳምቅልን ሰው ከወሰድነው ቤታችን አበቃለት::
ከቤታችን እጅግ ምርጥ የምንላት እህት በጣም ኢምንት በሆነ ነገር ተጋጭታ በአቅራቢያው ወደሚገኙ እህቶቿ ቤት ሄደች:: በእርግጥ ሁሌ ይዘያየራሉ:: የዚያ ቀን ግን ጫን ያለው ሆነ:: ከሁላችንም በሰል ያለች የኔ ታናሽ አለች:: (በነገራችን ላይ የእኛ ጎሳ ከጉ^ራጌ ውስጥ ነገር አዋቂ ከሚባለው ነው:: አምባይ ይባላል:: መሪው የጥራዳም ናቸው:: የነገርን ምንጭ, መሄጃና መግቢያ ከግሽ ዐባይ እስከ ሜዲቴራኔያን በደንብ ያውቃሉ:: እነሳቸው ፍርድ አሰጣጥ ላይ ብዙ ጊዜ ተከታትያለሁ:: ሥርዓቱ ኃይማኖተኛ ነኝ የሚሉት ቢያፈርሱትም ባሕሉ ግን አለ)::
እና ታናሼ ደወለችላት:: << በአባታችን አጥንት ይዤሻለሁ ፀሐይ ሳትጠልቅ ቀድመሽ ወደ ቤትሽ ተመለሽና ጉዳይሽን እናየዋለን:: ሴት ልጅ ትታ አትወጣም:: ነውር ነው:: የወጣችበት ቤት ይርቃታል:: ከእኛ መሃል ማንም ባል አይሆንሽም ብላ ጮኸችባት:: እና ሌላኛው ወንድሜን ልከን አጅበው አስገቧት:: እነሆ ሌላ ልጅ ወለደች:: ማሻአላህ ምርጥ ኑሮ ይኖራሉ:: ችግሩ ቢራዘም ኖሮ የእህቶቻችንን ቤቶች ልናራርቅ ነበር:: አንድ ግቢ ሁላ ቤት ገዝተው የሚኖሩ እህቶች አሉኝ::
በወቅቱ "የታባቱ" ምናምን ማለት የጀመሩ አይጠፉም:: ሴት ወልይዋ (ተያዧ ማለትም አባት, አጎት, ወንድም) ወይም በሰል ያለ የውስጥ ሰው ቶሎ ጣልቃ ገብቶ ከዚያ ከነገር circle ⭕️ መንጭቆ ማውጣት የግድ ነው:: የሚያኗኑርም ከሆነ ሴቷን መቆጣትና ቶሎ መመለስ እንዲሁም ለእርሱ የተሻለ የሚባል ሰው ልኮ ተወያይቶ ለእርሱም ቁጣ የሚያስፈልገውም ከሆነ ተቆጥቶ ነገሩን እዚያው እፍን ማድረግ ነው:: Major የሚባሉና ትዳር ውስጥ የማያኗኑሩ ችግሮች ከተስተዋሉ በአደባባይ ነውር መገላለጥ አያስፈልግም:: ቆርጦ ማሳረፍ::
ከትናንትና ወዲያ አንድ ወንድም ጋር ስንጨዋወት ያደረገውን ነገረኝ:: እህቱ ከባሏ በትንሽ ጉዳይ ተጣልታ አዳማ (ናዝሬት) እህቷ ጋር ተሳፈረች:: ወንድም ጉዳዩን እንደሰማ በመኪና ቀደማት:: እህታቸው ቤት ተገናኙ:: ትንሽ እንደተጨዋወቱ ወንድም እሳት የጎረሰ ሰው መሰለ:: እኔ ወንድምሽ እያለሁ እንዴት እንደዚህ ያደርጋል, ሸሪዓ ፍርድ ቤት እንገትረዋለን ብሎ አሟሙቆ አዲስ አበባ እናታቸው ቤት ይዟት መጣ:: ካላሟሟቀላት አትመጣም:: ታድራለች:: ነገር ይቀዛዝናል:: ከዚያ ባሏ ጋር ሄዶ ችግሩን አደመጠ:: ከሁለቱም እንደሰማው በጣም ተራ ግጭት ነው:: ቀድሞ ሄዶ እንዳመጣት ለቧላ ከነገረውም መናናቅ ይመጣል:: በቃ ከአዳማ ሄጄ ላምጣት ብሎ እናቱ ቤት ገብቶ እህት ውየኻደመች መቃም ጀመረ:: ልክ አዳማ ደርሶ መልስ የሚሆን ያህል ሲሆን በምሽት ይዟት ቤቷ አስገባት:: ይኸው ማሻአላህ ብዙ ልጆች ወልደዋል::
ሚስት ስታገቡ ከእጮኛችሁም ባሻገር ተያዧ ላይ ትኩረት አድርጉ:: በተለይ አግብታ የማታውቅ ከሆነ:: አግብታ የምታውቀዋ ሕይወት አስተምሯታል:: የምታደርገውን ታውቃለች:: ስለዚህ አባት ነገር ያውቃሉ ወይስ በልጆቻቸው ላይ ቸልተኛ ናቸው? ለሚስታቸው እንዴት ያሉ ሰው ናቸው? እናትስ? አጎቶቿስ? ወንድሞቿስ? እህቶቿስ? ብለህ በስሱ የዳሰሳ ጥናት ያስፈልጋል:: ባሕሉን አለመልቀቅ ነው::
*********
በንግሥናህ አጥር ማለትም በትዳርህ ቅጥር ግቢ አጉል እጄን ልስደድ የሚል ያንተ ዘመድ ካለ እጁን ቁረ^ጠው ማለቴ አጥርህን ዝጋ:: አንተም እጅህን ሰብስብ:: ወሬ አታውጣ:: ነውር ነው:: በሷም በኩል የሚገቡ ከሆነ አጥሯን እንድትዘጋ ምከር:: መፍትሔ ካላገኘ ግን እንዲያርፉ በግልጽ ንገራቸው:: ምክንያቱም ሚስትህ ብትሄድ ባል አይሆኑዋትም:: ስለዚህ ቁስል የሚያክ ጥፍራቸውን ቁረጥ:: በከዘራ አንቆራጥጥ:: አዎና!!! ለወሬ አይመቻቸውም:: ያው የሰው ትዳር ሲበጠብጡ ተዠለጡ ነው የሚባለው:: ፍርድ ቤት ቢኬድ እንኳ ይፈረድባቸዋል:: ሚስትህ ካንተ ይልቅ ዘመዶቿ የሚቀርቧት ከሆነ ድምጽ በማያሰማ የጥቁር አንበሳ ሐኪሞች መቀስ ቆርጠህ እዚያው ቀላቅላትና ይቧኩ::
@ Hasen injamo
🌹#ከአንድ_በላይ_አግባ 🌹