ጃን ያሬድ | Jan Yared

@jann_yared


እግዚአብሔርን አመስግኑ ምህረቱ ለዘላለም ነውና!!!

ማን ነው ህይወትን ማግኘት የሚፈልገው

ማን ነው ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል መማር
የሚፈልገው 

ማን ነው ስለ እመብርሀን ስለ ድንግል ማርያም
መማር ማወቅ የሚፈልገው

  እንግዲያውስ አሁንኑ ይፍጠኑ እና ይቀላቃሉ 

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:02


ዐሥራ ሦስት የአብነት ደቀ መዛሙርት ዲቁና ተቀበሉ

| ጃንደረባው ሚድያ | ግንቦት 6 2016 ዓ.ም.|
አዲስ አበባ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በጃን እስጢፋኖስ ላለፉት ሁለት ዓመታት በአዳር የአብነት ትምህርት ያስተማራቸውንና መሥፈርቱን ያሟሉ ዐሥራ ሦስት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሄኖክ አንብሮተ ዕድ ማዕረገ ዲቁናን ተቀብለዋል:: የኢጃት ቦርድ ሰብሳቢ ዲ/ን ዶ/ር ዳዊት "ኢጃት ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በጃን ማዕተብ ከሰባ በላይ ንዑሰ ክርስቲያንን ለምሥጢረ ጥምቀት ፣ ብዙኃንን በጃን ዮሐንስ ለምሥጢረ ንስሓና ቁርባን ፣ በጃን ቃና ዘገሊላ ደግሞ ለምሥጢረ ተክሊል ያበቃ ሲሆን አሁን ደግሞ ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ለምሥጢረ ክህነት አብቅቶአል" ብለዋል::

"ዲያቆናቱ በአግባቡ የተማሩና ለአገልግሎት ዝግጁ የሆኑ ናቸው" ያሉት የጃን እስጢፋኖስ ሰብሳቢ መምህር ኤፍሬም ሲሳይ ሲሆኑ "ተማሪዎቹ ምንም ዓይነት ትምህርት ሳይኖራቸው ወደ ኢጃት መጥተው በአግባቡ ተምረው ለዚህ በመብቃታቸው እጅግ ደስ ብሎናል:: ትምህርት ሳይጨርሱ ወዴትም እንዳይሔዱ በማስገደድም በአበው ልማድ መሬት ላይ እየተኙ በሌሊት እንዲማሩና ከአብነት ትምህርቱ ጋር መሠረታዊ ነገረ ሃይማኖትም እንዲማሩ ተደርጓል" ብለዋል:: በማያያዝም "በቅርቡ ሱባኤ እስጢፋኖስ የተሰኘ የዲያቆናት ብቻ ሱባኤ ጉባኤ ለማካሔድም ዝግጅታችንን ጨርሰዋል ብለዋል" ዲያቆናቱን አስተምረው ለዚህ ካበቁ መምህራን መካከል አንዱ የሆኑት መምህር ኃይለ ኢየሱስ ተሻለ በበኩላቸው "ወደ አገልግሎት ለመግባት በአግባቡ ደጅ ጸንተውና የአገልግሎቱን ምንነት ተረድተው ለዚህ መብቃታቸው ቤተ ክርስቲያንን የበለጠ ለማገልገል ያስችላቸዋል:: ለዚህ ደርሰው ማየታችን ለኢጃት ትልቅ ደስታ ነው" ብለዋል::

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:02


ነጻ የሚያወጣ ፍቅር

|ጃንደረባው ሚድያ | መጋቢት 2016 ዓ.ም.|

✍🏽 ዮርዳኖስ ዘሪሁን እንደጻፈው

ንፁህ እና እውነተኛ ፍቅር ለምንወደው ሰው ያለ ምንም ገደብ ታላቅ ነፃነትንና ሰላምን ይሰጣል። ይህም ሰላም እና ነፃነት የሚፈጠረው ከምንም በላይ አብልጠን የምንወደው ሰው ከቶ በኛ ቁጥጥር ውስጥ እንዲሆን ባለመፍቀዳችን ነው። ማለትም አንድን የምንወዳትን ወፍ በማሰርያ ውስጥ አስረናት የኛ እንድትሆን ከማድረግ ይልቅ እንደልቧ እንድትበር ፈቅደን ነገር ግን ቤት አዘጋጅተንላት በነጻነት በራሷ ፍላጎት ተመልሳ ወደሰራንላት ቤት እንድትመጣ ነፃነትን መስጠት እንደማለት ነው።

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:01


Channel photo updated

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:01


Channel name was changed to «ጃን ያሬድ | Jan Yared»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:00


Channel name was changed to «ጃን ያሬድ /Jan Yared»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 May, 12:00


Channel name was changed to «ጃን ያሬድ -Jan Yared»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

29 Dec, 00:22


+ " ጽኑ እምነት " +

ይህ መዳን አለባቸው ባልናቸው የሕይወት አንዱ ችግሮቻችን ውስጥ ቢመጣ አይለወጥ ይሆን ሕመሙን ባታስታግስም ከአንተ አልርቅ አልክድህ ወዳንተ እጠጋለሁ ፀናለሁ እንል ይሆን ከድህነት ባታድነኝም ባጣም አንተን ከማጣት አይበልጥብኝም አልክድልህም እስርነቴ አመታት ቢያልፍ ሰው መሳለቂያ ሆኜ አፋቸው እንደ እሳት ቢበላኝ እያየህም ባታስፈታኝ አልክድህም እንል ይሆን ለእኔ ግን ማንፀና ምንደክም ይመስለኛ ትግስት ባለመግኘት ይቻላቸዋል ብለን ወደምናስብው ወደ ቆሙ ወደማይሰሙ ጣዖታት ምንሮጥ ።

ዳንኤል 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል ፥
¹⁸ ነገር ግን፥ ንጉሥ ሆይ፥ እርሱ ባያድነን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ አሉት።

የሦስቱን ወጣቶች እምነት "አባ ሄሮኒመስ" ሲገልፅ
‹‹ እግዚአብሔር እንደሚያድነን እናምናለን አሉ በኃጢአታቸው ምክንያት ከምድራዊው እሳት ባያድነንም ከዘላለም እሳት እንደሚያድነን እናምናለን ፥ የምናምነው በዚህ ዓለም ኑሮ ብቻ አይደለም ። በሰማያዊውም በሚመጣውም ሕይወት እናምናለን ። የምናምነው ከነበልባል ለማምለጥ ስንል ብቻ አይደለም ፣ ይህንን እሳት በማምለጥ ዘለዓለማዊ እሳት ውስጥ እንወድቅ ይኾናል ፥ ስለዚህ ማድረግ የምትፈልገውን ፣ እቶኑን አዘጋጅ ፣ ያም ለመንፃታችን ይሆናል ›› ። " ይለናል ። ነዶ ከማያልቀው እሳት ያድነናል ከአሁኑ ይልቅ ዘላለማዊውን እያዩ የፀኑ እምነተ ጠንካሮች ። በእነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያቶች ላይ ብቻ አዳኝነቱን ተስፍ ምናደርግ አለን እስከሺበታችን ጊዚያቶች ግን ጌትነቱ ትዝ ማይለን የወጣትነታቸው ሕይወት እሱን ከማመን ያላስቆማቸው እንዲፈሩት የተጣሉበት እሳት ፈርቶአቸው ያላቃጠላቸው እንዲመላለሱበትም መንገድ ያበጃጀላቸው ለአምላካቸው ባሳዩት ጽኑ እምነት ነው ።

ጃን ያሬድ | Jan Yared

26 Dec, 17:49


Check out መንፈሳዊ የህይወት ምክር: https://t.me/MenfesawiMkr

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:59


እግዚአብሔርን አመስግኑ ምህረቱ ለዘላለም ነውና!!!

ማን ነው ህይወትን ማግኘት የሚፈልገው

ማን ነው ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል መማር
የሚፈልገው 

ማን ነው ስለ እመብርሀን ስለ ድንግል ማርያም
መማር ማወቅ የሚፈልገው

  እንግዲያውስ አሁንኑ ይፍጠኑ እና ይቀላቃሉ 

ከሲዖል የሚጠብቅ የእግዚአብሔር ቃል
እንዳያመልጥዎ

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:58


#ዕጣንና_ጽንሃ_በቤተክርስቲያን

#ዕጣን
ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዕጣንን የተመላ ሰማያዊ ማዕጠንት በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እየሰገዱ ለአለም ድህነት የሚለምኑበት ነዉ፡፡ በቤተክርስቲያን ካህናት መንፈቀ ሌሊት ፡ በነገህ ጊዜ በቅዳሴ ጊዜ በየማዕዘኑ ዕጣን ያጥናሉ ቅዳሴውን ጸሎቱንና ልመናዉን ወደ እግዚአብሔር ያሳርጉበታል ፡፡

ስለ እጣን የመፅሀፍ ቅዱስ ማስረጃ

ዘጸ 30፥1 የዕጣን መሰዊያዉን ስራ ከግራር እንጨት አድርገው።

ዘጸ 30፥35 በቀማሚ ብለሀት እንደተሰራ፥ በጨዉም የተቀመመ ንጹህና ቅዱስ እጣን አድርገው፡፡

ዘጸ 30፥34 እግዚአብሄርም ሙሴን አለዉ፦ ጣፋጭ ሽቱ ዉሰድ የሚንጠባጠብ ሙጫ በዛጎል ዉስጥ የሚገኝ ሽቱ፥ የሚሸትትም ሙጫ፥ ጥሩም ዕጣን ዉሰድ የሁሉም
መጠን ትክክል ይሁን፡፡

ዘፀ 40፥5 ለዕጣንም የሚሆነዉን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ታኖራለህ፥ በማደሪያዉም ደጃፍ ፊት መጋረጃዉን ትጋርዳለህ፡፡ ዘጸ 40፥27 የጣፋጩን ሽቱ ዕጣን አጠነበት፡፡

ዘሌ 10፥1 የአሮንም ልጆች ናዳብና አብድዩድ በየራሳቸዉ ጥናዉን ወስደዉ እሳት፥ በላዩም ዕጣን አኖሩበት በእግዚአብሔር ፊት እሱ ያላዘዛቸውን ሌላ እሳት አቀረቡ፡፡

ዘሌ 16፥12 በእግዚአብሔር ፊት ካለዉ መሠዊያ ላይ የእሳት ፍም አምጥቶ ጥናዉን ይሞላል፥ ከተወቀጠውም ከጣፋጭ እጣን እጁን ሙሉን ይወስዳል ወደ መጋረጃውም
ዉስጥ ያመጣዋል፡፡

ዘኁ 16፥7 ነገም በእግዚአብሔር ፊት እሳት አድርጉባቸው፥ ዕጣንም ጨምሩባቸው እንዲህም ይሆናል እግዚአብሔር የሚመርጠው እርሱ ቅዱስ ይሆናል እናንተ የሌዊ ልጆች
ሆይ እጅግ አብዝታችኀል ብሎ ተናገራቸው፡፡

ዘዳ 33፥10 ፍርድህን ለያዕቆብ፥ ህግህንም ለእስራኤል ያስተምራሉ ፤ በፊትህ ዕጣንን፥ በመሰዊያህም የሚቃጠል መስዕዋት ይሠዋሉ፡፡

መዝ 140፥2 ጸሎቴን በፊትህ እንደ እጣን ተቀበልልኝ ፥ እጅ መንሳቴም እንደሰርክ መስዕዋት ትሁን፡፡

ማቴ 2፥11 ወደ ቤትም ገብተው ህጻኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር እዩት፥ ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥኖቻቸዉንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤን አቀረቡለት፡፡

ሉቃ 1፥10 በዕጣንም ጊዜ ህዝቡ ሁሉ በዉጭ ቆመውዉ ይጸልዩ ነበር፡፡

ራእ 5፥8 መጽሀፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንሰሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳዳቸም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ፡፡

ራእ 8፥3 ሌላም መለአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለዉ በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ
እጣን ተሰጠዉ

#ጽንሃ

ጽንሃ የእጣን ማሳረጊያ ወይም ማጠኛ ነው። ሦስት ሰንሰለቶች አሉት። ሰንሰለቶቹ ሶስት መሆናቸው የሚስጢረ ሥላሴ ምሳሌ ነው። በሰንሰለቶቹ ላይ ቢያንስ አስራ ሁለት (12) ቢበዛም ሃያ አራት (24) ሻኩራዎች ይኖሩታል።
‘’ሻኩራ’’ ማለት ሶስቱ ሰንሰለቶች ላይ ያሉት ክብ ነገሮች ናቸው። የሻኩራዎቹ ቁጥር አስራ ሁለት (12) መሆኑ የሐዋሪያት ምሳሌ ነው። ሃያ አራት (24) መሆኑ ደግሞ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ምሳሌዎች ናቸው ። ከስሩ እጣኑ የሚቀመጥበት ሙዳይ የመሰለ ክፍል የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ሲሆን: መለኮት ከሥጋዋ ሥጋ ነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ ሰው መሆኑን ያመለክታል። ፍሙ የጌታችን የመለኮትነቱ ምሳሌ ሲሆን እጣኑ እንደሚቃጠልና መዓዛው ሁሉን እንደሚያውድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ብዙዎች ኃጢያት ራሱን መስዋዕት በማድረግ አቅርቦ ዓለሙን ሁሉ ማዳኑን ያሳያል።

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:58


1  አቤቱ አምላኬ ፥ ባንተ ታመንኹ፤ ከሚያሳድዱኝ ዅሉ አድነኝና አውጣኝ ፥

2  ነፍሴን እንደ አንበሳ ነጥቀው እንዳይሰብሯት ፥ የሚያድንና የሚታደግ ሳይኖር።

3   አቤቱ አምላኬ ፥ እንዲህስ ካደረግኹ ፥ ዐመፃም በእጄ ቢኖር ፥

4   ክፉ ላደረጉብኝም ክፉን መልሼላቸው ብኾን ፥ ጠላቴንም በከንቱ ገፍቼው ብኾን ፥

5   ጠላት ነፍሴን ያሳዳት ያግኛትም ፥ ሕይወቴንም በምድር ላይ ይርገጣት ፥ ክብሬንም በትቢያ ላይ ያዋርዳ ት።

6   አቤቱ ፥ በመዓትኽ ተነሥ ፥ በጠላቶቼ ላይ በቍጣ ተነሣባቸው፤ አቤቱ አምላኬ ፥ ባዘዝኸው ትእዛዝ ንቃ።

7  የአሕዛብም ጉባኤ ይከቭኻል ፥ በእነርሱም ላይ ወደ ከፍታ ተመለስ።

8   እግዚአብሔር በአሕዛብ ይፈርዳል፤ አቤቱ ፥ እንደ ጽድቄ ፍረድልኝ ፥ እንደ የዋህነቴም ይኹንልኝ።

9   የኃጥኣን ክፋት ይጥፋ ፥ ጻድቁን ግን አቅና፤ እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል።

10  እግዚአብሔር የጽድቅ ጋሻዬ ነው ልበ ቅኖችን

የሚያድናቸው።

11 እግዚአብሔር የእውነት ዳኛ ነው ፥ ኀይለኛም ታጋሽም ነው ፥ ዅልጊዜም አይቈጣም።

12 ባትመለሱ ግን ሰይፉን ይስላል ፥ ቀስቱን ገተረ አዘጋጀም፤

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:57


Channel name was changed to «ጸሎት - 𝐓𝐒𝐄𝐋𝐎𝐓 𝐓𝐮𝐛𝐞»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:56


Channel photo updated

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:53


Channel name was changed to «ጸሎት - 𝐓𝐒𝐄𝐋𝐎𝐓»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

02 Sep, 19:50


Channel name was changed to «መንፈሳዊ የሕይወት ምክር»

ጃን ያሬድ | Jan Yared

15 Aug, 19:26


Channel photo updated

ጃን ያሬድ | Jan Yared

01 Aug, 21:27


"ሰው ምንድን ነው?"
ከ ሐመር መጽሔት ፳፯ኛ ዕትም የተወሰደ

ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረው ሰው ግሩምና ድንቅ ሆኖ የተፈጠረ ፍጡር ነው፡፡ (መዝ.፻፴፰÷፲፬) ሰው አስቀድሞ በፈጣሪው በልዑል እግዚአብሔር ሲፈጠርም አፈጣጠሩ በብዙ መንገድ ከሌሎች ፍጥረታት ልዩ ሆኖ የተፈጠረ ክቡር ፍጥረት ነው፤በሥነ ፍጥረት ትምህርት እንደተማርነው እግዚአብሔር በዓለም ያሉ ፍጥረታትን በኃልዮ (በሐሳቡ ይሁኑ በማለት) በነቢብ (በቃል በመናገር ይሁኑ በማለት) ሲፈጥር ሰውን የፈጠረው ግን በገቢር በእጆቹ ነው፡፡ ነቢዩ “እጆችህ ሠሩኝ፤ አበጃጁኝም” ብሎ እንደመሠከረ፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በእርሱ መልክና እንደ ምሳሌው አድርጎ ነው፡፡ “እግዚአብሔርም አለ፥ ሰውን በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር” ተብሎ እንደተጻፈ፡፡

የእግዚአብሔር መልክ የሚባለው እንደ ምንድን ነው ቢሉ አበው እንዳስተማሩት የእግዚአብሔር መልክ የሚባለው ቅድስና፣ ፍቅር፣ ቸርነት፣ ነጻነት፣ ጥበብ፣ ገዥነት፣ ክብር፣ ንጽሕና፣ ፍትሐዊነት፣ ርኅራኄ፣ አሳቢነት፣ ዕውቀትና የመሳሰሉት ነው፡፡ እነዚህ የአምላካችን የእግዚአብሔር የባሕርይው መገለጫዎች የሆኑ ነገሮች ሰው በተፈጠረ ጊዜ በጸጋ ተሰጥተውታል፡፡ (መክ.፯÷፳፱፣ ዘሌ.፲፱÷፪፣ ሉቃ.፮÷፴፮፣ ፩ኛጴጥ.፩÷፲፮)

እነዚህን የቅድስና መንፈሳዊ ባሕርያት መገለጫዎች እያጎለበተና እያሳደገ ሲሄድም ሰው የእግዚአብሔር ምሳሌ ወደ መሆን ይደርሳል፡፡

ሰው ምንድነው? የሚለውን ጉዳይ በእውነትና በእምነት ስንረዳም በሰው ሰውነት ውስጥ የእግዚአብሐርን ፈታሒነት፣ ከሀሊነት፣ ቸርነትና ባዕለጠግነት እንዲሁም ዐዋቂነቱን፣ ነባቢነቱንና ዘለዓለማዊነቱን እናውቃለን በመጨረሻም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እንደርሳለን።

አንድ ገበሬ በራሱ እርሻ ላይ ያሻውን ዘር ሊዘራ ይችላል፤ ከእርሱም በቀር በእርሻው ላይ ማንም አያዝም፡፡ አስቀድመን እንደተናገርነው እኛ በክርስቶስ ወርቀ ደም የተገዛን የእርሱ እርሻዎች ነንና የእርሱ እርሻ በሆነ ሰውነታችን እንደ ዐረምና ቋያ የሆነ ክፉ ነገርን፣ የኑፋቄና የክህደት ትምህርቶችን፣ እርሱን የሚያስክዱ ሰብዓዊነትን፣ መተባበርንና መተዛዘንን የሚያጠፉ ርዕዮተ ዓለምንና ፍልስፍና መሰል መራዥ አስተሳሰቦችን፣ የነፍሳችንን ነገር ሙሉ ለሙሉ አስለቅቀው ለሥጋችን ፈቃድ ብቻ እንድንኖር የሚገፉ ዲስኩሮችን እንዳንዘራ ልንጠነቀቅ ይገባናል

“ሰው ክቡር ፍጥረት ሆኖ ሳለ አላወቀም፡፡ ነገር ግን እንደሚጠፉ እንስሳት መሰለ” ተብሎ እንደተናገረ እንዳንሆን፡፡ (መዝ.፵፰÷፲፪)

ምንጭ፡ ሐመር መጽሔት ፳፯ኛ ዕትም ፳፻፲፩ ዓ.ም

ጃን ያሬድ | Jan Yared

01 Aug, 21:22


Channel photo updated

ጃን ያሬድ | Jan Yared

30 Jul, 06:44


እነሆ፥ ቢገድለኝ ስንኳ እርሱን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ፤ ነገር ግን መንገዴን በፊቱ አጸናለሁ።

መጽሐፈ ኢዮብ። 13:15

@Hollybible81 🀄🀄

ጃን ያሬድ | Jan Yared

29 Jul, 18:38


በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው። ዐውሎንም ጸጥ አደረገ፥ ሞገዱም ዝም አለ። ዝም ብሎአልና ደስ አላቸው፤ ወደ ፈለጉትም ወደብ መራቸው።

መዝሙረ ዳዊት 107:28-30

1,537

subscribers

1

photos

1

videos