Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

@hamzaps


ሐምዛ ት/ቤት የተማሪዎችን ዉጤት እና ስነ-ምግባር ማሻሻል ቀዳሚ ተግባሩ ነው፡፡
መገኛ አየር ጤና ግራር ኮንዶሚኒየም ፊት ለፊት ሐምዛ መስጅድ ጎን
ስልክ 011-36 93-365
ኢሜይል [email protected]

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

22 Oct, 17:57


ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች በነገው ዕለት የሐሳብ መለዋወጫ ደብተራቸው ላይ አያይዘን የምንልክ ይሆናል::

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

22 Oct, 17:52


ተማሪ
ናዲያ ታሪኩ
አብዱልማሊክ ሚፍታህ
ሰልዋ ዘይኑ
ፋጡማ ሙህዲን
ካሊድ ሸምሡ
አብደላ ሙህዲን
አዩብ ሳዲቅ
ኢንቲስሳር ነስሮ
ለተማሪዎች ተወካይ ምርጫ ከላይ በተያያዘው ቅፅ መሠረት ራሳችሁን አዘጋጁ።

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

21 Oct, 12:55


#AddisAbaba #Education

“ በሂሳብና እንግሊዘኛ መፅሐፍት ላይ እጥረት በመታየቱ ተጨማሪ ህትመት እየተካሄደ ነው ” - አ/አ ትምህርት ቢሮ

በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት መፅሐፍ ማሳተም ላይ እንደ አገር በተለያዩ ትምህርት ቢሮዎች ክፍተቶች እንዳሉ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት በ2017 የትምህርት ዘመን መፅሐፍትን አሳትሞ ለተማሪዎች ማዳረስ ተቻለ ? ሲል ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጥያቄ አቅርቧል።

የቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በሰጡት ቃል፣ “ በተወሰኑ ትምህርቶች ላይ፤ ሂሳብና እንግሊዘኛ መፅሐፍት  እጥረት በመታየቱ ምክንያት ተጨማሪ ህትመት እየተካሄደ ነው። ሪዘርቭም እያደረግን እንገኛለን ” ሲሉ ተናግረዋል።

የመፅሐፍት እጥረቱ በምን ደረጃ ነው ? ሲል ቲክቫህ ላቀረባቸው ጥያቄ በምላሻቸው፣ “ ይህንን ሬሽዎ በተለይ ከግል ትምህርት ቤቶች አካባቢ ላይ ያለ ችግር ነው ” ብለዋል።

“ እነርሱም መፅሐፉን ወስዶ ለማሰራጨት ፍላጎት ማጣት፣ ይሄ ደግሞ የራሳቸው መፅሐጽት አትመው ለመሸጥ ከሚመነጭ ነገር ስለሆነ እሱ ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እየወሰድን ትምህርት ቤቶች ወስደው ለተማሪዎቻቸው ተደራሽ እንዲያደርጉ አድርገናል ” ነው ያሉት።

“ ከሁለተኛ ደረጃና ቅድመ አንደኛ ደረጃ በስተቀር ለሁሉም አንድ ለአንድ ተዳርሷል ” ሲሉም ተናግረዋል።

“ ለሁለተኛ ደረጃም ትምህርት ሚኒስቴር አሳትሞ ሰሞኑን ባስገባው መሠረት ለሁሉም ተማሪዎች ማዳረስ ተችሏል" ያሉት ኃላፊው፣ " ባለፉት ሁለት ዓመታት በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ተማሪዎቻችን ጋር ተደራሽ ለማድረግ ተሞክሯል” ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ ከተማሪዎች ምገባ ጋር በተያያዘ መጋቢ እናቶች ከኑሮ ውድነቱ ጋር በተያያዘ የሚከፈላቸው ገንዘብ አነስተኛ መሆኑን ይገልጻሉ።

ይህንኑ በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ማብራሪያ የጠየቅናቸው ዘላለም (ዶ/ር)፣ “ በተማሪ 22 ብር የነበረው በዚህ ዓመት ወደ 32 ብር አሳድጎላቸዋል። ስለዚህ ያ ጥያቄ ተመልሷል ማለት ነው ” ብለዋል።

“ በቀን 800 ሺሕ ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ ይመገባሉ ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተያያዘም በትምህርት ቤት አካባቢዎች ያሉ ሱስን የሚያበረታቱ ቤቶች እንዳሉ፣ ይህም ተማሪዎችን ከዓላማቸው የሚያደናቅፍ ከመሆኑ አንጻር በቂ ትኩረት ተሰጥቷል? ሲልም ቲክቫህ ጥያቄ አቅርቧል።

ዘላለም (ዶ/ር) በምላሻቸው፣ “ትክክል ነው። የተማሪዎችን ሀሳብ፣ ልቦና የሚሰርቁ ጉዳዮች በትምህርት ቤት አካባቢዎች እንዳይኖሩ ባለፉት ዓመታት ጠንካራ እርምጃ ወስደናል” ብለዋል።

“ ከ3000 በላይ የሚደርሱ የተለያዩ መማር ማስተማር ሂደቱን ሊያውኩ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ እርጃ ተወስዷል ” ብለው፣ “ አሁንም እንደዛ አይነት ፍላጎቶች በትምህርት ቤቶች ብቅ ብቅ እንዳይሉ መልሶ ጠንካራ እርምጃና ክትትል ያስፈልጋል ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

16 Oct, 15:47


Share 'Language Dep..docx'

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

14 Oct, 17:44


የመልእክት ማስተካከያ ውድ ወላጆች በነገው እለት ተማሪዎች 8:30 ይለቀቃሉ ብለን የላክነው መልእክት ላይ ማስተካከያ ያደረግን ሲሆን መደበኛወ ትምህርት ጥናትን ጨምሮ ለሙሉ ቀን የሚቀጥል ይሆናል።
እባከዎትን መረጃውን ለሎች ያጋሩ

ጀማል ካሳው

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

14 Oct, 13:56


(إِنَّا لِلّهِ وَإِنَّـا إِلَيْهِ رَاجِعونَ
የትምህርት ቤታችን ዋና ስራ አስኪያጅ እናት በማረፋቸው የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ለእርሳቸው ደግሞ አላህ በራህመቱ እንድቀበላቸው እንመኛለን።

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

12 Oct, 06:47


ለህፃናት ፓርላማ እጩ የሆኑ ተማሪዎች ለፈተና የሚዘጋጁበት ሞጁል።

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

01 Oct, 14:54


በአዋሽ ባንክ ክፍያ ለመፈፀም

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

29 Sep, 16:33


ውድ ወላጆች በዛሬው እለት በነበረን ውይይት ላይ ላደረጋችሁ የነቃ ተሳትፎ እጅግ አድርገን እናመሠግናለን።

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

28 Sep, 11:51


ለውድ ወላጆቻችን ለነገው ቀጠሮ ኣችን ዝግጅታችን ተጠናቋል።

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

26 Sep, 10:03


የስብሰባ...

Hamza School/ሐምዛ ት/ቤት

22 Sep, 11:03


ፐረሰንታይል ከ90 በላይ ያላችሁ ተማሪዎች የሽልማቱ ተካፋይ እንድትሆኑ ተጋብዛችሗል።

1,111

subscribers

996

photos

27

videos