በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ውድ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ሰነበታችሁ እንኳን ለአፈ በረከት ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ የእረፍት በዓልና ለሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣ ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ🙏🙏🙏
ከሥር በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በጉራጌ ሀገረ ስብከት በምሁርና አክሊል ወረዳ ቤተ ክህነት በአጣጥ ቀበሌ በልዩ ስሙ የዋሽወራ ቅዱስ ቂርቆስ እና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣ ቤተ ክርስቲያን ሲሆን በአካባቢው 18 ምእመናት ቢቻ ያሉበት አጥቢያ ነው ታዲያ አሁን እየተገለገሉበት ያለው ቤተ መቅደስ ከእርጅናና በክረምት ወቅት ከሚደርስበት የጎርፍ ጥቃት እየተሸረሸረና እየተቦረቦረ ቤተ መቅደሱ ሊፈርስ ከጫፍ ድርሷል ማለት ይቻላል ታዲያ ይህን ታሳቢ በማድረግ በአካባቢው በአሉት ምእመናት ተነሳሽነት ከሥር በምስሉ የምታዩትን ቤተ መቅደስ በአስቸኳይ እየተሰራ ይገኛል ግን በአጥቢያው ያሉት ምእመናት ከአቅማቸው በላይ እያደረጉ ይገኛሉ ግን አሁን ላይ የማቴሪያል እጥረት አጋጥሟቸዋል ይህን ደግሞ ለማድረግ ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ የእኛን የሁሉም ኦርቶዶክሳውያን እገዛ ይፈልጋሉ ታዲያ የሁላችንም ግዴታ ነው ይህን ቤተ መቅደስ ማነጽ ምክንያቱም የኃያሉ የልዑል እግዚአብሔር ማደሪያ ስለሆነ የሁላችንም በአርባና በሰማንያ ቀን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት ስለሆነ ዘወትር በጸሎት በቅዳሴ እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ስለሆነ ቤተሰብ እንኳን እንመስርት ብንል የጋቢቻ ሥርዓታችን የምንፈጽምበት ስለሆነ በነፍስም በሥጋም ብንታመም የምንፈወስበት ቤት ስለሆነ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን የምንቀበልበት ስለሆነ እንዲሁ ከሥጋ እረፍታችን በምናርፍበት ጊዜ እንኳን ጸሎተ ፍትሐት ተፈጽሞልን የሥጋችን ማርፊያ ስለሆነ ብናዝን ብንደሰት መጽናኛችን ማመስገኛችን ስለሆነ ይህ ሁሉ አገልግሎትና ፀጋ የምናገኘው የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ስናንጽ ነውና ሁላችንም የአቅማችንን በመርዳት ይህን ቤተ መቅደስ እናስፈጽም እግዚአብሔር ዋጋ ሲሰጥ ብዙ የሰጠ ትንሽ የሰጠ አይልም የሁላችንም ዋጋ በሰማይ እኩል ነው ስለዚህ የአቅማችንን እንስጥና ቤቱን እናንጽ እያልን በአምላከ ቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ስም እናሳስባለን🙏🙏🙏
አሁን ላይ የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች
፩, ድንጋይ የውሃ ልኩ ማንሺያ የሚሆን
፪, ሲሚንቶ በጣም ፈተና የሆነ ነገር ነው።
፫, በርና መስኮት
፬, ቀለም እነዚህ ዋንኞችሁ ናቸው በዚህ ሁሉ በረከት መሳተፍ ያስፈልጋል ሌላው ለጸሎትና ለልዩ ልዩ አገልገሎቶች የሚውሉ ንዋየ ቅዱሳት እጣን፣ዘቢብ፣ጧፍና ሻማ ድጋፍ ማድረግ ይቻላል።
👉ድጋፍ የምታድርጉበት አካውንት በቤተ ክርስቲያኑ ስም የተከፈተ ያለው ንብ ባንክ ነው ቁጥሩም፦ 7000028803977 ነው።
ምን አልባት በንግድ ባንክ መላክ የምትፈልጉ የግለሰብ አካውንት አለ እሱም፦ 1000535092797 ዮሐንስ ጌቱ በዚህም ገቢ ማድረግ ይቻላል አደራውን ማድረስ ስለምችል ነው ወገኖቼ ታዲያ ገቢ ከአደረጋችሁ በኋላ እስሊፑን ላኩልን የግድ ለማድረስ ማወቅ ያስፈልጋል ማለት ነው።
ለበለጠ መረጃና ገቢ ማድረጋችሁን ለማሳወቅ፦ 0996990485 ቀሲስ ኃይለ ቂርቆስ የቤተ ክርስቲያኑ አለቃ።
👉0945173873 ዲያቆን በረከት ሞገስ አስተባባሪና አገልጋይ ነው።
👉0937076125፣0912241064 ዮሐንስ ጌቱ በእነዚህ የስልክ አድራሻዎች መረጃ መጠየቅም መስጠትም ትችላላችሁ ማለት ነው።
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን!