FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

@focusinternationalministry


NEW CREATION MANIFESTATION

👉በዚህ ቴሌግራም ቻናል #በፎከስ #ሚንስትሪ #ትምህርቶች ይቀርባሉ፡፡
እንዲሁም
#የፀሎት#የነፃ መውጣትና#የፈውስ አገልግሎት የምትፈልጉ#እንዲመለስላችሁ የምትፈልጉትን#ጥያቄ ያላችሁ#Facebook ላይ
👉 #Woubshet #Humaso የሚለውን #follow
        👉በማድረግ ማቅረብ ትችላላችሁ 👇
https://www.facebook.com/whumaso

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Oct, 13:40


. #እግዚአብሔርን #መፍራት #እንማር. አንብቡት👇
:- መዝ34፤1 ዛሬ ዛሬ ብዙ አይነት ትምህርቶች በበዙበት ዘመን ፣ብዙ አይነት ትምህርት ለመማር የምንሰለፈውንና ፣ በየሚዲያው ተጥደን የምንውለውን ያህል እግዚአብሔርን ስለ መፍራት ለመማር የሚፈልግ ሰው መሆን አለመፈለጋችንን ያህል ክስረት የለም።
እግዚአብሔር መፍራትን የሚያስተምሩንን እንፈልግ።

:- እግዚአብሔርን በመፍራት ለመኖር የሚፈልግ እግዚአብሔርን ስለመፍራት እውቀትን ይፈልጋል አጥብቆ ይማራል ፣ እግዚአብሔርን መፍራት በትምህርት ነው የሚመጣው። መዝ34፤1 ዘዳ14፤23, 17፤19, ምሳ2፤5, 9፤10
ምሳ15፤33።

:- መዝ 34፤1 እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ ትልቁ ትምህርቱ ለትውልዱ ከምንም ነገር ( ከገንዘብ፣ከፃታ፣ ከቁሳቁስ..) በላይ የሚያስተምረው ፤ እግዚአብሔርን መፍራትን ነው።

:- 2ዜና26፤5 በተለይ በዚህ ዘመን ከምንም ነገር በላይ ልንፀልይ የሚገባን ነገር ቢኖር እግዚአብሔር መፍራትን የሚያስተምሩንን ሰዎች እግዚአብሔር እንዲያስነሳልን ነው።

:- ኢዩብ28፤28, ትልቁ ጥበብ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ፤ ስለ ብዙ ነገሮች ማወቅና መተንተን ሳይሆን። ምሳ1፤7, 9፤10

:- ኢዩብ15፤4 እግዚአብሔርን መፍራት በእግዚአብሔር ፊት ሊቋረጥ የማይገባው አምልኮም ነው። it is #worship

:- መክ12፤13 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት :-
የእግዚአብሔርን ህግ ወይም ቃል በተግባር መኖር ማለት ነው። በተጨረማመ ሀይማኖተኛ ፉት መታየትና መንፈሳዊ ንግግር በማብዛት መንፈሳዊ መስሎ ለመታየት መሞከር ሳይሆን።። it is #obedance to the word !

:- ምሳ3፤7 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት:- ለሁሉ ነገራችን እግዚአብሔርን በመታመን መኖር ማለት ነወ
it is #Trusting God.

:- 2ዜና19፤7 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት :-
- ሌላውን ሰው ላለመበደል መትጋት
- በሰው ፊት አለማዳላት። ዘር። ሀብት ማእረግ እያየን
- ጉቦ አለመስጠትም አለመቀበልም ነው።

:- ምሳ8፤13 ,መክ5፤7 እግዚአብሔር መፍራት ማለት :-
- ክፉ ድርጊትንና መንገድን መጥላት ማለት ነው
- ከትእቢተኛነትና አልታዘዝ ባይነት ወቶ ትሁትና ታዛዥ መሆን ማለት ነው
- በአንደበቱ ጠማማነት ፣ስድብን፣ውሸትን የማይናገር ሰው መሆን ማለት ነው

:- ሮሜ13፤18, መዝ14፤6 እግዚአብሔርን መፍራት የሌላቸው ሰዎች ፤ የሰላምን የእርቅን መንገድ አይቀበሉም

:- ዘዳ6፤13, 10፤20 እግዚአብሔርን ስለ መፍራትን እንድንማር ብቻ ሳይሆን ፤ እግዚአብሔርን በመፍራት እንድንኖር ታዘንማል። it is a #commandment

:- መክ5፤7 በንግግራችን ሁሉ እግዚአብሔርን እንድንፈራ ማስጠንቀቂያ ተሰቶናል ።when we #talk let us fear God

:- ዘፍ20፤11 እግዚአብሔርን መፍራት የሌለበትን ቦታ ለይተን ማወቅና ከዚያ ስፍራ ስፍራ መሸሽ ፣ካልሆነም በጥንቃቄና በጥበብ መመላለስ ይገባናል። run away or walk in wisdom , when you see the place that no fear of God .

:- ምሳ10፤27, 14፤27, 24፤4 ኢሳ33፤6 ምሳ19፤2 እግዚአብሔርን የመፍራት ጥቅሞችና ትሩፋቶች :-
- ዘመንን ታረዝማለች
- ከሞት ወጥመድ ታስመልጣለች
- የህይወት ምንጭ ናት
- ትህትናና ክብርን ታስገኛለች
- ባለጠግነት፣ክብርና ህይወት ታስገኛለች
- ወደ ህይወት ይመራል
- በጥጋብ ያኖራል
- ከክፉ ነገር ይጠብቀናል
- በዘመናችንን የሰላምና የፀጥታ ፣የጤንነት ያደርግልናል

👉 በመጨረሻም እግዚአብሔርን ወደ መፍራት እሚወሰወዱንን ትምህርቶች ፈላጊ፣ እግዚአብሔርን መፍራትን ለትውልዳችን የምናስተምር አስተማሪዎች፤ እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖር ልጆች መሆን ይብዛልን።
ትውልዴ ሆይ በቃ እግዚአብሔር በሁሉ እንፍራ !!🙏
ፓስተር ውብሸት ነኝ
ከ focus international ministry/solas 🙏

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

13 Oct, 13:03


. #አምልኮ #ለእግዚአብሔር #ብቻ ! 🙌
#አምላካችን :- በሙሉ #ልባችን ፣#ሀሳባችን እና #ሀይላችን #የምንወደውና #የምናገለግለው ነገር ሁሉ ነው።

#አምላካች :- ከምንም ነገር በላይ የምንወደው ፣ የምናከብረው ፣ የምንፈራው ፣ጊዜአችንን የምንሰጠው ፣ ገንዘባችንን የምናውልበት ፣ ያለ ማቋረጥ የምናስበው፣ የምንታመንበት ፣ ተስፉ የምናደርገው ፣ለሰዎች ሁሉ ለማሳየት የምንተጋለት ነገር ነው።

#አምልኮ ማለት :- ለዚያ ከሁሉ በላይ ላደረግነው ፣ለምንወደው የምንሰጠው ምላሽ እና በመታዘዝ ፣ በመቀደስ ፣ በትህትና ፣ በፍትህ ፣ በምህረት ፣ በመስጠትና በመሰጠት ፣ እንዲሁም በመዝሙር ጭምር የሚገለጥ ኑሮ ነው።
#አምልኮ ማለት :- በህይወታችን አምላክ ካደረግነው ጋር ያለን #ጤናማና #ቅዱስ የሆነ #ግኑኝነት እና #ምላሽ ነው። !
#አምላካችን ማለት:- በሙሉ #ልባችን ፣#ሀሳባችን እና #ሀይላችን #የምንወደውና #የምናገለግለው ነገር ሁሉ ነው።
ስለዚህ :-
👉ሰይጣንን እና የባእድ አማልክትን፣ ሙታንን አታምልኩ
👉ራሳችሁን (ውበታችሁን፣እውቀታችሁን፣ችሎታችሁን አታምልኩ)
👉ቤተሰባችሁን፣ ልጆቻችሁን፣ አታምልኩ
👉ገንዘባችሁን እና ቁሳቁስን አታምልኩ
👉ሀይማኖታችሁን ፣ዘራችሁን፣ ባህላችሁን አታምልኩ
👉ሚዲያ አታምልኩ ፣ ስራችሁን አታምልኩ።
" እኔና ቤቴ እግዚአብሔርን እናመልካለን "፣ እናንተም ይህንን ፅሁፍ የምታነቡ ሁሉ የምታመልኩትን( ከሁሉ በላይ የምትወዱትን፣ ሁሉ ነገራችሁን የምትሰጡትኑ፣ የምትታመኑትን፣ የምትፈሩትን፣ የመትሰውለትን ዛሬ ምረጡ ?!ለጣኦታት ፣ ለገንዘብ ፣ለራሴ፣ ለባህሌን አላመልክም !
መዝሙር ጋበዝኳችሁ
የአስቴር አበበን።። ሳሙኤልን እንካ !!

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

05 Oct, 14:14


#እንንቃ #ሁሌም #መንፈሳዊ #ጦርነት #ውስጥ #ነን !
:-ሰይጣን በር ከፈትንለት አልከፈትንለት እኛን መዋጋት አይተውም። መንፈሳዊ ጦርነት ውስጥ ነን ! ሰይጣን ቀልዶ አያውቅም ፣ መቼም አይዘናጋም! መቼም አይራራም!
:- ሰይጣን ከእኛ በበለጠ በብዙ ልምድ ፣ ዘዴ ለዘመናት የተካነ ነው ፤ በማሳት ፣ በመክሰስ፣ በመፈታተን፣በማታለል፣ በመጣል፣ ተስፉ በማስቅረጥ ፣አደጋ በማድረስ፣ በመለያየት ፣ በማድከም ፣ ብዙ ተቃዋሚዎችን ቀብቶ በማስነሳት፣ ክፉ በሳቦችን በመላክ።

:- ዳግም የተወለድን በሙሉ የጌታ በመሆናችን፣ በሱ መንግስት ላይ በበቀል እንደተቀባን ስላወቀ ፣ ህልማችን የሚያደርስበትን ኪሳራ ስለሚያውቅ፣ እኛ ብንባረክ ፣ጤና ቢኖረን፣ ብንበረታ ኪሳራውን ያውቃልና።

:-ስለዚህ በብዙ የእግዚአብሔር ሀይል ፣ የፀሎት ትጋት፣ በመንፈሳዊ ጦርነት መጋደል ፣በመንቃት መመላለስ ሁሌም ያስፈልገናል።
2ቆሮ2፤11 ኤፌ6፤10-16 ራእ12፤9-11 2ቆሮ10፤3-7, 11፤3

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

02 Oct, 11:59


. "#መንፈስ #ቅዱስ #ይሙላባችሁ " ኤፌ5፤18
. ነገራ ነገር፣ አለምና የአለም ኮተት፣ ወሬ ሀሜትና ጥላቻ
፣ዘረኝነትና ምቀኝነት ፣ቅንአትና ትእቢት ፣ቂምና ክፉት፣ እኔነትና እልከኛነት ፣ዝሙትና ርኩሰት አይሙላባችሁ። መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ።🔥🙏🔥
እርሱ ሲሞላባችሁ በየቀኑ :-
:-ሀይልና ልዩ ልዩ የፀጋ ስጦታዎች ትሞላላችሁ ትበረታላች
:- ደስታ ፣ሰላም፣እረፍትና ሀሴት ይሞላባችኀል
:- ንግግራችሁ በጨው እንደተቀመመ የፀጋ ቃል ይሆናል
:- በቅድስና ለመኖር ሀጢአትን እንቢ የማለት አቅም ታገኛላችሁ
:- ህይወታችሁ በፍቅርና በይቅርታ የተሞላ ይሆናል።
:- ሰጪዎች ትሆናላችሁ
:- የእምነት መንፈስ ይሞላባችኀል
:- እርሱ ትሁት ያደርጋችኀል ግብዝነትና ትእቢት ይወገዳል
:- የምታሁት ህልምና ራእይ አጋንንታዊና በእርኩሰት የተሞላ አይሆንም
:- በምድራዊው ኮተትና በአለማዊ ነገሮች ፍቅር ልባችሁ አይወረስም
:- በእሳት የተሞላ ፤አጋንንት አብሮት የማይኖር ሰው ትሆናላችሁ
:- ያለማቋረጥ በአላማችሁ ላይ ያተኮራችሁ ፣በመንፈስ የምትቃጠሉ ትሆናላችሁ።
:- በፀሎት በምስጋና በአምልኮና በመንፈሳዊ ውጊያ በበቀል ይሞላናል
:- ለነፍሳት ሸክም ወንጌልን ላልዳኑት ለመናገር ያነሳሳናል በድፍረትም ይሞላናል
ነገራ ነገር፣አለምና የአለም ኮተት፣ ወሬ ሀሜትና ጥላቻ፣ዘረኝነትና ምቀኝነት ፣ቅንአትና ትእቢት ፣ቂምና ክፉት ፣እኔነትና ግትርነት እልከኝነት፣ ዝሙትና አመፅ አይሙላባችሁ። መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ።
ይሄን እያነበባችሁ አሁን በመንፈስ ቅዱስ እሳት ይሙላችሁ ጌታ። 🔥🙏🔥

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

25 Sep, 02:57


. #ጠላቶቻችሁ #ይሳቀቁ #የአባቴ #ብሩካን #ሳቁ
. ደስታ ነፃ የወጣ ሰው ህይወት መገለጫ ነው።በአጋንንት
እስራት ውስጥ ያለ ሰው ሰላምና ደስታ የራቀው፣ፊቱ ጨምዳዳ ነው።
. ደስታ ለሌሎች ሰዎች መልካምን የማሰብና የማድረግ ውጤት ነው።በሰው ላይ ክፉት ያረገዘ መቼም አይደሰትም
. በእግዚአብሔር መንፈስ ቁጥጥር ስር በሙላት ስትሆን ደስታህ ሞልቶ ይፈሳል። መንፈስ ይሙላባችሁ። አሜን
. በእግዚአብሔር የመታመን የእምነት ኑሮ ውጤት ነው።
የሚጨነቅ ሰው ደስታው የተነጠቀበት በራሱ የታመነ ነው
. ደስታ በበጎ ህሊና በንፁህ ልብ የመመላለስ ውጤት ነው።
ቅንነቱን ያጣ ፣በልቡ ቂም የያዘ ፣ መቼም ደስታ አያይም
. ደስታ የሁሉ ነገራችን ምንጭ ጌታን ብቻ የማድረግ ውጤት ነው። በጌታ ላይ አይናችንን ፣ተስፉችንን ስናደርግ ደስታ አይናፍቀንም ፣በሙላት እንኖረዋለን እንጂ።
. ደስታ በአላማ የተሞላ ፣በራሱ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሰው መገለጫ ነው።
. ደስታ የፀሎት ህይወት ያላቸው ሰዎች ሰማያዊ ሀይል ነው
"የእግዚአብሔር ደስታ ሀይልችን ነው "
:- ደስተኛ ስትሆን ጠላት የሚደነግጥብህ፣ ሀይልህ ብዙ ፣በስጋ ጤናማ፣ በመንፈስ ቅዱስ እየተሞላህ ፣በብዙ ፀጋ የምታገለግል እና ለአከባቢህ ሁሉ ሰላምና ሳቅን የምታጋራ ሞገሳም ትሆናለህ። .

በአጋንንት እስራት ውስጥ ያለ ሰው ደስታ የራቀው፣ፊቱ ጨምዳዳ ነው። ጌታ የፈታው ፣ሰማይ ብድራቱ ፣ኢየሱስ ጌታው የሆነ ሰው ይደሰታል ፤ ደስታው አይወሰድበትም።
REJOICE IN THE LORD ፊሊ4፤4
እስቃለሁ ጠላቴ እያየ እስቃለሁ ሁኔታው እያለ እስቃለሁ
"ሰይጣን ይሳቀቅ ጌታ ያላችሁ እናንተ ሁሌም ሳቁ " p wou
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Sep, 10:08


.በልዩ ልዩ #ፈተና #መከራ #ስደት ለምታልፉ ሁሉ :- ጠላት
1:- እግዚአብሔርን ከማመን፣ ከመከተልና ከማምለክ
2:- እግዚአብሔርን ከማገልገል ከጥሪአችሁ እናንተን ማውጣትና ማስቆም ስለሚፈልግ ነው ይህንን ሁሉ እያደረገባችሁ ያለው ስለዚህ :-
:- ይህ ሁሉ በእናንተ ላይ የተቀመጠ ታላቅ ፀጋ ፣የተለየ አላማና ጥሪ እግዚአብሔር በአናንተ እንዳለው ሰይጣን ስለሚያውቅ ፣ እናንተ አምልጣችሁ ብዙዎችን ቤተሰቦቻችሁን እንደምታስመልጡ ስለገባው፣የእናንተ ነገ በብዙ በረከት ፣ ክብርና ከፍታ እንደሆነ ስለተረዳ፣ ቀንቶ ፣ተናዶ፣ እኛን ከዚያ ለማስቀረት ፈልጎ ነው።
:- በምንም አይነት የህይወት ውጣውረድ፣ በምንም አይነት መከራና ፈተና እንዲሁም ልባችሁን የሚያሳዝን ነገር ውስጥ ብታልፉም ከመስቀሉ ስር ፣ከፀጋው ዙፉን አትጥፉ።
:-አገልግሎታችሁን አታቁም። የጠራችሁ ሰው ሳይሆን እግዚአብሔርን ነው። የከፋባችሁ ፣ፊታቸውን ያጠቆሩባችሁ ፣ የገፋአችሁ ሰዎች እንጂ እግዚአብሔር አይደለም። እግዚአብሔር እንደሆነ ፍቅሩ ለእናንተ ዛሬም ያው ነው፣ በእናንተ ላይ ያለውን አላማውን፣ ሀሳቡን ፣ጥሪውን ፣አልቀየረም። ይልቁኑ በዚህ ሁሉ በብዙ አበርትቶ ፣ አስተምሮ በሚበልጥ እጥፍ ፀጋና ሀይል በበቀል ያስነሳችኀል።
:- የዛሬ ማጣት ፣ በገፋት ፣መናቅ ፣ የሰው እጅ ማየት ቀን አልፎ በብዙዎች የምትፈለጉበት፣ለሌሎች የምትትረፈረፉበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። በምንም አይነት ችግር ውስጥ ብትሆኑም እንኳን አምልኮና አገልግሎታችሁን አታቁሙ። እግዚአብሔር የሚያመልኩትን ከመከራ ያወጣቸዋል።
:- የትዳር መፍረስና ግጭቶች ፈተና፣የገንዘብ እጦት፣በወዳጅ መከዳት፣ የስም መጠልሸት ፣ በሀሰት ክስ፣ በሰዎች ደባ ፣ በስራ ማጣት ፣ በስጋ በሀጢአት መውደቅ ፣በልዩ ልዩ ህመሞች ውስጥ ብታልፉም እነዚህን 3 ነገሮች አስተውሉ :-
1:- በብዙ መከራ የፀናውን፣ የታገሰውን የአምላኩን ፈቃድ ማድረግ ሳያቆም ጥሪውን ፈፅሞ ያለፈውን ኢየሱስን ተመልከቱት። እርሱ ከፊቱ ያለውን ደስታ እያሰበ በመስቀል ፣በመከራ እንደታገሰ እናንተም ከፊታችሁ ያለውን ደስታና ታላቅ ብድራታችሁን እያሰባችሁ ታገሱ።
#ዕብ12፤1-4
2:- የትኛውም አይነት ችግር ውስጥ የምታልፉት እግዚአብሔር ስለማይወዳችሁ፣ ስለማያይ፣ ለመከራ ስለፈጠራችሁ፣ጠላታችሁ ከእግዚአብሔር በላይ ስለሆነ ወይም እናንተ ከአለም ሁሉ ህዝብ የተለየ ሀጢአተኛ ስለሆናችሁ አንደ አይደለ ማወቅ አለባችሁ። ብዙ የእምነት አባቶቻችንም በብዙ ልዩ ልዩ መከራ፣ፈተናና ስደት አልፈዋል። #ዕብ12፤1
3:- የኔ የተለየ ነው ፣አትበሉ ከማጉረምረም ተጠበቁ ፣ ሌሎች ብዙዎች አሉ እንደ እናንተው በልዩ ልዩ መከራ የሚያልፉ። ይህ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ የማይፈቅድ ፣ የፀጋውን አቅም በእናንተ ያስቀመጠውን የሚተማመን እንደሆነና በፀጋው ችላችሁ ፣ፀንታችሁ እንደምታልፉት ዛሬን እመኑ። በመጨረሻም ከመከራው ጋር መውጫንም እግዚአብሔር እንደሚያዘጋጅላችሁ አትርሱ። ይህ መጨረሻችሁ አይደለም ማለፊያችሁ እንጂ የከፍታ፣የመትረፍረፍ፣ የክብር ዘመን ከፊታችሁ ስላለ ፤ በትግስት፣በመፅናትና በእምነት አምልኮአችሁንና አገልግሎታችሁን ቀጥሉ።
#1ቆሮ10፤13
ወደ ኀላ በሚያፈገፍግ፣ አቋራጭን ለመጠቀም በሚቸኩል፣ በሚያጉረመርም ሰው ነፍሱ ደስ አትሰኝም።
" ፃድቅ ግን በእምነት በህይወት ይኖራል"#ዕብ10፤38-39
:- መከራ ውስጥ ከመግባታችሁ በፊትም ከገባችሁ በኀላም ፀልዩ
:- በምንም አይነት መከራ ውስጥ ሆናችሁ ጌታን ማምለክ፣ ማመስገን እና ማገልገላችሁን አታቁሙ።
ወንድማችሁ የእግዚአብሔር ሰው ፓስተር ውብሸት ነኝ
Focus international ministry/solas

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Sep, 15:30


#አጋንንት #ማስወጣት እና #ነፃ #መውጣት ባለበት በዚያ
1:- መንፈስ የሆነው ጌታ ኢየሱስ በጌትነቱ በትንሳኤው ሀይል በዚያ በሙላት የመኖሩ ምልክት ነው 2ቆሮ3፤17
"ጌታ ግን መንፈስ ነው የጌታ መንፈስ ጌታ በሆነበት
በዚያ አርነት "
2:- የእግዚአብሔር መንግስት በዚያ በሙላት የመኖሩ ምልክት ነው
ሉቃ11፤ 20
3:- ለአማኞች የልጅነት ስልጣናቸው መመለሱና በዚያ ስልጣን የመመላለስ ምልክት ነው
ማር16፤17 ሉቃ10፤19
4:- ሰይጣን በኢየሱስ ትንሳኤ የመሸነፉና ስልጣኑን የመገፈፉ ምልክት ነው
ቆላ2፤15 ማቲ28፤18
5:- በመንፈስ ቅዱስና በሀይል አጋንንትን በማስወጣት
ፀጋ የመቀባታችን ምልክት ነው
ሐዋ10፤38
6:- በመካከላችን ነፃ አውጪው መንፈስ ቅዱስ በስራ
ላይ በበላይነት ተገልጦ እንዳለ ምልክት ነው።
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

12 Sep, 08:06


🎆🙏 የምስራች
"እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም"
ሮሜ8፤1
የቀድሞ የአሁን የወደፊቱ ሀጢአታችን ሁሉም፣በፈሰሰው የኢየሱስ ደም ይቅር ተብሏል።

ኢየሱስ አንዴ ለሁሌ ሞቶልናል!
ስለዚህ
" ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤" ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።"ሮሜ 4:7-8
ብፁእ ነኝ !
የቆጠረልንን ትተን ያማይቆጠርብንን መቁጠር እናቁም !
"ቀንና ለሊት በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞች ከሳሽ ተጥሏል " ራዕ12፤10
የሰውን ሀጢአት ቆጠራ ላይ ያላችሁ የሰይጣን የከሳሹ አገልጋዮችና ፤ የራሳችሁን ደብቃችሁ ሌላውን ለመውገር ድንጋይ ይዛችሁ ፤ያላችሁት ግብዞች ,
ያላችሁት በኢየሱስ ፊት መሆኑን ላስታውሳች ፤ እንዲያውም ደስ ይበላችሁ የእናንተም አይቆጠርባችሁም !!

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

08 Sep, 16:16


. " #በራሳችሁ #መንገድ #ላይ #አጠብጥቡ"
አንዳችን ከሌላችን መገፉፉት፣መጠላለፉ ያቆሳስለናል፣
ያዘገየናል፣ሀይል ያባክንብናል፣ ለጠላት በር ይከፍታል .!
"እያንዳንዱም በመንገዱ ላይ ይሮጣል..አንዱም ከአንዱ ጋር አይጋፉም ፤እያንዳንዱም በመንገዱ ይጠበጥባል፣ በሰልፉም መሀል ያልፉሉ እነርሱም አይቆስሉም" ኢዩ2፤7-8
አንዳችን ሌላችንን ልንረዳ እንጂ ልንጎዳ አልተፈጠርንም
" "WE ARE NOT CALLED TO COMPET EACH OTHER,BUT TO COMPLETE EACH OTHER "
:- በአላማችን ላይ ስናተኩር ፣ መስመራችንን ጠብቀን ስንሮጥ ሀይላች እና ፍጥነታችን እየጨመረ ይሔዳል
:- አንዳችን ከሌላችን ጋር መገፉፉት ትተን በመደጋገፍ ወደ ህልማችን ፍፃሜ ሁላችንም እንደርሳለን።
:- የእግዚአብሔር መንግስት ሌላውን በመቅደማችንና በመብለጣችን ሳይሆን የኛን ሀላፊነት በመወጣታችን ብቻ ነው የሚሸልመን። አትድከሙ ላላውን ለመብለጥ
:- በአላማው ላይ በማተኮር ፣ለሌላው ሩጫ እንቅፉት ከመሆን የተቆጠበ ሰው የራሱን ፍፃሜ ክብር ያያል
:- በራሱ መስመር ላይ በማተኮር በሚገጥሙን ፈተናዎች፣ ተቃውሞዎችና ተግዳሮቶች ወደ ኀላ #ሳናፈገፍግ በትእግስት፣ ራሳችንን በመግዛት እና በእምነት ፣በተስፉ ተሞልተን እንሩጥ ሩጫችንን። መውረሳችን አይቀሬ ነው
:- አንዳችን ከሌላችን መገፉፉት ብዙ ቁስለኛ ያበዛል፣
ይል ይጨርሳል፣ ከራሳችን ፍፃሜ ክብር ያዘገየናል።
በራሳችሁ ጉዳይ ላይ አተኩሩ #1ተሰ4፤11
:- በሰላምና በፀትታ መኖር ከፈለጋችሁ
:- ስኬታማ እና ፍሬያማ መሆንና መብዛት ከፈለጋችሁ
የምንሸለምበትን ሩጫ እንሩጥ
p woub 🦅🎯🔥
focus international ministry/solas
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

01 Sep, 08:53


. #የሰው #እጅ #የለበትም #100% #ፀጋ ብቻ ነው

ኢየሱስ ማለት :-#ፀጋና #እውነት ማለት ነው ዮሐ1፤15,17
ኢየሱስ ህግ ሰጪውም ህግ ፈፃሚውም እሱ ኢየሱስ ነው።
ይህ ነው ወንጌል
"የሆንኩትን ሁሉ #የሆንኩት፣በኔ የተሰራው ሁሉ #የሰራው #ፀጋወ ብቻ ነው።"። #1ቆሮ 15፤10

"እኔ ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ በእኔ ይኖራል" ገላ2፤20
መንፈሳዊነት እኛ የምንኖረው ህይወት ሳይሆን ኢየሱስ ራሱ በእኛ የሚታይበት፣የሚሰራበት፣የሚኖርበት ህይወት ነው።

ኢየሱስ ህግ ሰጪውም ህግ ፈፃሚውም እሱ ነው።ይህ ነው ወንጌል
:- " እኔም አልፈርድብሺም ..ሐጂ ....ደግመሽም ሀጢአትን አትስሪ"
ዮሐ8፤ 11
ኢየሱስ የትላንት ሀጢአቷን ብቻ ሳይሆን ይቅር ያለው ፣ከዚህ በኀላ በቅድስናም የምትኖርበትን አቅም ነው የሰጣት። ሰው በራሱ አቅም
ሀጢአት አለመስራት መለወጥ አይችልም። የፀጋው ውጤት ነው የቅድስና የተለወጠ ህይወት። ቲቶ2፤11-14

:- ፀጋ ማለት የዳንነት ፣የሚለውጠን ፣የቆምንበት፣የምንኖርበት፣
የምናሸንፍበት፣ የምንሰጥበት፣ የምንወድበት ፣ይቅር የምንልበት ሁሉ
ነገራችን ነው። በራሳችን ከፀጋው ውጪ የምንጥረው፣ህይወት በፍፁም የፀጋ ህይወት ፣የፅድቅ ፍሬ ፣ እግዚአብሔር የሚደሰትበት እና
የሚቀበለውም ህይወት አይደለም።

:- መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን ፣በውስጣችን ያለው እግዚአብሔር የሚቀበለውን ፣የሚደሰትበትን የፀጋ ህይወት በእኛ ለመግለጥ ነው።
:ገላ5፤22 የመንፈስ ፍሬ የሰው የጥረት ውጤት አይደለም የፀጋ እንጂ"

:- 1ቆሮ 15፤10 2ቆሮ12፤8-10 ጳውሎስን ያዳነው፣ የለወጠው ፀጋው፣ በሱ የተሰሩትን ተአምራት የሰራው ፀጋው፣የፃፋቸውን መልእክቶች ሁሉ ያፃፈው ፀጋው፣ በዚያ ሁሉ መከራ ፣ስደት፣ መከራ ያቆመው ፣ ያበረታው ፀጋ ነው። ከፀጋው ውጪ የራሱ የሆነ ብቃት የሌለው እንደኛው ደካማ ስጋ ለባሽ የሆነ ፣ በብዙ የሚፈተን፣የሚያዝን፣
የሚሳሳት ሰው ነበረ። ኤፌ1፤7 የፀጋው ክብር የተመሰገነ ይሁን።

ዛሬም በእኛ ህይወት ፀጋው ብቻ ነው 100% የሰው እጅ የለበትም
"በህግ ልትፀድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከፀጋው ወድቃችኀል " ፅድቅ ፣ቅድስና የፀጋው ውጤት እንጂ በራስ ጥረትየሚመጣ፣የሚኖር ህይወት አይደለም። እንፍቀድለት ለፀጋው።
:- መፍጨርጨር ፣ጌታንም ለማገዝ መጣር እናቁምና ለመንፈስ ቅዱስ፣ለፀጋው ራሳችንን እናስገዛ፣ እኔ አልችልም አንተ በእኔ ትችላለህ ፣አንተ ለፈለከው ህይወት ፈቅድልሀለሁ አንተ በኔ ኑር በሉት በህይወታችሁ በእርሱ ፀጋ በሆነ ፣በጥረት ያልሆነ፣መለወጥ ይሆናል፣
ያስቸገራችሁን ሱስ ተነቅሎ ሔዶ ታዩታላችሁ፣ትደነቃላችሁም።

ገላ2፤20 " እኔ ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ በኤ ይኖራል"
100% ፀጋው ብቻ
ፓስተር ውብሸት ነኝ የፀጋው ፍሬ።
focus / Solas international

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

31 Aug, 14:00


. #ከሰይጣን #የከፋም #አለ #ለካ
:- በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ አንድም ቦታ #ሰይጣን #ከሰይጣን ሲዋጋ፣ሲጣላ እርስ በርሱ ሲከፉፈል አይታይም።
:- ሰይጣን እንኳ እርስ በእርሱ #አይለያይም #አይበላላም #አይካሰስም፣#አይጠላላም፣እንዲህ አንዱ ሌላውን ሊበቀል፣ሊጎዳ ፣ሊያጠፉ አይተጋም።
" እርስ በእርስዋ የምትለያይ #መንግስት ሁላ ትጠፉለች፤ #እርስ በእርሱ #የሚለያይ #ከተማም ሁሉ ወይም #ቤት #አይቆምም። ማቲ12፤25
" እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግስት ሁሉ ትጠፋለች ቤትም በቤት ላይ የወድቃል"... ሰይጣን ደግሞ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግስቱ እንዴት ይቆማል ? #ሉቃ11፤17-18

:- አንዱ ወንድም ሌላው ወንድሙ ጋር፣አንዱ አገልጋይ ከሌላው አገልጋይ ጋር፣ አንዱ ሀይማኖት ከሌላው ሀይማኖት ጋር፣አንዱ ብሔር ከሌላው ብሔር ጋር ፣ እርስ በእርሳችን ስንጓተት፣ስንጠላለፍ፣ስንካሰስ፣ ስንወነጃጀል፣ ስንጣላ ፣ ሰይጣን እንኳን የሌለው ባህሪይ ያለን አንድ አዲስ ፍጡር የሆንን ያህል ይሰማኛል፣ የኛ የኢትዮጲያውያንና ኤርትራውያንን ባህርይ ሳይ። ኤረ ወገን እንንቃ ሰው እንሁን።

:-እኛ ኢትዮጲያውያን ከሰይጣን እንኳ የከፉ ተግባር፣አላማ ውስጥ ተጠምደን መገኘታችን ምን የሚሉት እርግማን ፣የክፉት ጥግ ፣ጨለምተኝነት እንደሆነ ሳስብ አዝናለሁ

:- አጋንንቶች ሲሸነፉ እንኳ ተባብረው ፣ተያይዘው ፣ተደጋግፈው የጋራ አላማቸውን ለማሳካት ፣የፈለጉትን ስፍራ ፣ግለሰብ ለመያዝ ፣ ጠላቶቻችን ናቸው ያሉትን ለማጥቃት ሲተጉ፣እኛ ኢትዮጲያውያን ፣የገዛ ወንድማችንን፣ሀገራችንን ለማጥፉት ለሊትና ቀን ከጋራ ጠላቶቻችን ጋር እንኳን ሳይቀር የምንስማማው ነገር በጣም ለማመን አይደለም ለማሰብ የሚከብደኝ የክፉት ፣የራስን ወንድም፣ወገን፣ሀገር የመጥላታችን የምቀኝነታችን ጥግ ያሳየኛል።

:- እርስ በእርሳችን ስንካሰስ፣ ስንቆሳሰል፣ ስንዋጋ፣ አንዱ የሰራውን ሌላችን ስናፈርስ፣ አንዳችን ሌላችንን ለመጉዳት ጉድጓድ ስንቆፍር ፣ በውሸት በፈጠራ ክስ ስም በማጠልሸት ስንጠመድ፣ አንዳችን ሌላው የሰራውን መልካም ስራ ከማድነቅና ከማመስገን ይልቅ ለማጣጣል ፣ ያለመሰልቸት ስንጋጋጥ ኤረ ምን አይነት የጉድ ህዝብ ነን ያሰኛል።

:- በሌላው ሀገር ሰዎች አንዱ ለአንዱ መስዋእት ሆነው ፣ድልድይ ሆነው፣ ህይወታቸውን፣ ሀገራቸውን ሲቀይሩ ፣እኛ በራሳችን ሀገር እንኳን ተረዳድተን ሰርተን ከመለወጥ ይልቅ፣ እኛ የኛኑ ሰው ለመግደል፣ለማክሰር ፤በየጠንቋዩ ቤት ሊቱን ሙሉ ስንዞር እናድራለን።

:- በዚህ ከቀጠልን የቤተክርስትያን ትልቁን ተልእኮ እንዴት መወጣት እንደሚቻል ፣እንደ ሀገር እንዴት ሳንፈራርስ በአንድነት ፀንተን እንደምንቀጥል፣ እንደ ቤተሰብ የሚቀጥለውን ትውልድ እንዴት መታደግ እንደምንችል አላውቅም። ቆም ብለን ቢያንስ ቢያንስ ባንደጋገፍ ፣ ወዳጅ መሆን ካልቻልን ጠላት አንሁን፣
ከጠላት ጋር አናብር። ብዙ የማያስማሙን ጉዳዮች ቢኖሩ እንኳ በዋና ነገሮቻችን ላይ ተስማምተን ፣ተደጋግፈን ፣እንደ ቤተሰብ፣እንደ ቤተክርስቲያን ፣እንደ ሀገር ፣ ህልውናችንን ለማስቀጠል፣ እየመጡ ያሉትን ከፊታችን የተጋረጡብን የመበታተን አደጋዎች ብናስቀር፣ መቆሳሰል ብንተው ይበጀናል።
. ከሰይጣን የከፋን አንሁን ፣ ሰይጣን እንኳን እርስ በርሱ አይባላም፣አይመቀኝም፣አንዱ አንዱን ሊያጠፉ እንቅልፍ አቶ አያድርም። ሰው ነንና ሰው እንሁን። 🙏😭🇪🇹🇪🇷
! መልእክት ነውና ጆሮ ያለው ይስማ ? https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

30 Aug, 07:53


#ልባርካችሁ #እውነተኛ #ወዳጅ #ይስጣችሁ #ያድርጋች !
#እውነተኛ #የልብ #ወዳጅ #እንሁን
:-ከጀርባ የማያማችሁ ፣ሚስጢራችሁን የሚጠብቅ
:-በችግራችሁ ቀን ማንም በማይደርስላችሁ ቀን ሚደርስላችሁ
:-ለውድቀታችሁ ጉድጓድ እየቆፈረ ስማችሁን እያጠፉ የማይዞር
:-ከመጣ ከሔደው ጋር የማይነፍስ ፣በክፉ ቀን የማይከዳ
:-ከጠላቶቻችሁ ጋር ማይመክርባችሁ
:-ሁሉ ሲሸሹአችሁ ፊታቸውን ሲያዞሩ ፊቱን የማያዞርባችሁ
:-በበረታችሁ ቀን ብቻ ሳይሆን በደከማችሁም ቀን የማይለያችሁ
:-ሊጠቀምባችሁ ብቻ ሳይሆን ሊጠቅማችሁ የሚፈልጋችሁ
:-በጠላቶቻችሁ ፊት በአደባባይ ስለ እናንተ የሚሟገትላችሁ፣ ስለ እናንተ በላላችሁበት ስማችሁ ሲነሳ የሚያስቆም
:-በጥቅም የማይሸጣችሁ የማይለውጣችሁ
:-በሰላም ጊዜ ያወራችሁትን የሰራችሁትን በተጣላችሁ ቀን ሚስጢር የሚጠብቅ ፣መልሶ እናንተን ለመጉዳት የማይጠቀምን
:-እውነትን በፍቅር ለራሳችሁ ቀርቦ የሚነግራችሁ
:-የሚፀልይላችሁ ፣የሚያበረታታችሁ ፣ በግል ሚገስፃችሁ
:-በደስታችሁ የሚደሰት ፣በሀዘናችሁ ቀን የሚያዝን
:-አምሮባችሁ ሲያይ ደስ ብሎት የሚያደንቃችሁ ማይቀናባችሁ
:-ሀሳባችሁን የሚረዳችሁ ፣ለመፍረድ የማይቸኩልባችሁ
:-ሌሎች ስለ እናንተ ከሚነግሯቸው ይልቅ እናንተ የነገራችኀቸውን የሚያምኑ
:- ለቁም ነገር፣ለጫወታም፣ ለመንፈሳዊም ነገር የሚመች
🙏 እንዲህ አይነት #የልብ ወዳጅ #ሁን !#ሁኚ #እንሁን !!
እንደ #ይሁዳ ያልሆነ.. ጥቅም የማይለውጠው
እንደ #ጴጥሮስ .በክፉ ቀን እንደማያውቃችሁ ማይከዳ
እንደ ደሊላ የማይላጭ ፣ለጠላት ሚስጢራችሁን ማያወጣ
:-ነገር ግን እንደ ዮናታን ያለ ወዳጅ ይስጠንም እንሁንም!
ፓስተር ውብሸት ነኝ
focus /solas international
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

29 Aug, 09:00


እባካችሁን በቸርነቱ የተሰጠንን :- #እድሜ #ፀጋ #አእምሮ #ገንዘብ #አንደበት #ስልጣን #እድል #ጥበብ #ሚዲያ አናባክን ፤#በማስተዋል ፣#እግዚአብሔርን #በመፍራት #ለመልካም #አላማ #እንጠቀም።ህይወት #አጭርና #በሀላፊነት የተሞላች ናት #ነገ #እንጠየቅባታለን።🙏😭
" ኢየሱስም መልካምን እያደረገ ዞረ " ሐዋ10፤38
"በክርስቶስ መልካሙን ለማድረግ ተፈጠርን" ኤፌ2፤10

👉እባካችሁን ከእግዚአብሔር በቸርነቱ የተሰጠንን ሁሉ:-

1:- #እግዚአብሔርን ለማክበር for the glory of God ፣ መንግስቱን ለማስፋት ፣ ለወንጌል ተልእኮ እንጠቀም
2:- #ሌሎች ሰዎችን ለማነፅ፣ለመጥቀም፣ፀጋን ልንጨምርላቸው ፣ ለመለወጥ ፣ለማዳን ፣ ነፃ ለማውጣት እንጠቀም። ለማዋረድ፣ ለማሸማቀቅ፣ተስፉ ለማስቆረጥ፣
ሳይሆን።
3:- #ሀገርን ለመገንባት ፣ ትውልድን በመልካም ስብእና፣ አስተሳሰብ ለማነፅ እንጠቀም እንጂ፤ለመለያየት ፣ ለመከፉፈል፣ አይሁን።
4:-#ለራሳችንም የሚጠቅመውን ፣ነገ በጌታ ፊት የሚያሸልመንን፣ በእድሜአችን ፍፃሜ ዞር ብለን ስናይ የማንፀፀትበትን፣ህሊናችንን የማይከሰንን ሰርተን እንለፍ።
"የተፈቀደ ነገር ፣ማድረግ የቻልነው ነገር ሁሉ አይጠቅምምና ፤በማስተዋል እንኑር ፣እንናገር፣ እንፃፍ።
ታናሽ ወንድማችሁ ፓስተር ውብሸት ነኝ 🙏
ከጠቀማችሁ ለሌሎች ማጋራትን አትርሱ
focus/solas international ministry USA
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

22 Aug, 09:28


. "#ሀሳብ #ቶሎ #ካልነገስክባት #ትነግስብሀለች "
. " ሀጢአት በደጅህ ታደባለች ንገስባት ሳትነግስብህ"
ሀጢአትን ፣ጥላቻን፣ ቅንአትን፣ ትእቢትን ፣ በሀሳብ ደረጃ ገና ስትመጣ ቶሎ አንተ ካልገደልካት እርስዋ ቆይታ አንተን ትገልሀለች !
የሰይጣን ዋናው ትኩረት ሐሳባችንን ማበላሸት ነው 2ቆሮ11፤3። አእምሮአችንን አናከራየው !!
የተበላሸ ሀሳብ ማሰላሰል ፣የሚገልህን አውሬ ማሳድግ ነው፤ ወይም መርዝ እየጠጡ አልሞትም የማለት ያህል ትልቅ ድድብና ነው። wake up .
:- ሀሳብ እንደ መርዝ ነው ይመርዛል ፣ይበክላል ፣ያበላሻል ያረክሳል
:- ሀሳብ እንደ መሪ ነው ወደ ወደደው ይመራሀል፣
:- ሀሳብ እንደ በር ነው ሰይጣንን ያስገባብሀል
:- ሀሳብ እንደ አይን ነው ነገሮችን ስሎ ያሳይሀል
:- ሀሳብ ቦታ ፣ጊዜ ፣ደረጃ አይመርጥም የትም ፣ሁሉም በየትኛውም ሰአት ይመጣል
:- ሀሳብ እንደ ዘር ነው አንድ ተዘርቶ ብዙ ያፈራል
:- ሀሳብ ምንጭ ነው የምናየው ነገር፣ የተግባር ፣የንግግር የባህርይ ሁሉ ምንጭ ነው
:-ሀሳብ ገዢ ነው ሁለመናን መቆጣጠር ይችላል
"አጥብቀህ ልብህን(ሀሳብህን) ጠብቅ የህይወት መውጫ ነውና"
:- ሀሳብ ፈሪ ያደርጋል ፣በመሀል ያስቆማል እንዲሁም ሀሳብ ያጀግናል ያስቀጥላል
:- ሀሳብ የድህነትም የብልጥግናም መጀመሪያ ነው
በሀሳቡ የደሄዬ በተግባሩና በኑሮው አይበለጥግም።
:-ሰውን በሀሳባችንን እየጠላነው በተግባራችን መውደድ አንችልም። ሀሳባችንን እንለውጥ ተግባራችን እንዲለወጥ።
:- ፍቅርም ጥላቻም፣ትህትናም ትእቢትም፣ መድሀኒትም መርዝም መስራት ፣በሀሳባችን ውስጥ ነው የሚጀምሩት
:- ሰው በሀሳቡን ለሊት ያሰበውን በቀን ከማድረግ አይመለስም ፤ስለዚህ ሀሳባችንን እንለውጥ።

። ። የሰይጣን ጥይቱ ሀሳብ ነው
:- ሰው አስተሳሰቡ ከተበላሸ ሁሉም ነገሩ ነው የሚበላሸው
:-ወደ አእምሮአችሁ ለሚገቡ ሐሳቦች ጥንቃቄ አድርጉ
የምታሰላስሏቸውን ሀሳቦች ቆም ብላችሁ አጣሩ መርምሩ በቃሉ ብርሀን !? ፊሊ4፤8

አእምሮአችሁን የምንለውጥባቸው ሁለቱ መንገዶች
1:- ነፃ ማውጣት ወይም መማረክ 2ቆሮ10፤5 ፊሊ4፤8 2ቆሮ2፤11 2ቆሮ11፤3
:- ከአለማዊ የተበላሸ ፣የረከሰ፣የተጣመመ ሀሳብ ፣ ነፃ አውጡ
:- እግዚአብሔር ከካደ የሰይጣን ሀሳብ ፣
:- በአለማመን ፣ በአመፅ፣ በውሸት ፣ በትእቢት ፣ በክፉ ሀሳብ ፣ ከተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- ሌሎች ሰዎችን በሚጎዳ ፣ በተንኮልና በራስ ወዳድነት ብቻ ላይ ካተኮረ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- በጭንቀት ፣በፍርሀት ፣ በተስፉ መቁረጥ ፣ በሁከት ከተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- በስንፍና፣ በማጉረም፣ በማያመሰግን ፣ በሚኮንንና በክስ በተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ

2:- ማደስ :- በእውነት እውቀት መሙላት ሮሜ12፤2, ምሳ19፤2 ቆላ3፤10 ,,16
:-በክርሰቶስ የተሰራልንን ስራ በማወቅ በዚያ ውስጥ ብቻ ማንነታችንን ማወቅ IDENTITY
:- ቃሉ እንደሚለው ብቻ ማሰብ ፣በቃሉ መርህ መሞላትና መኖር PRINCEPLE
:- እንደቃሉ ብቻ መናገር .CONFESION...SPEAKING ....
P woubshet
Focus/solas international 🇪🇹🇪🇷🇺🇸

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

21 Aug, 12:45


መንፈሳዊ ወጣት
ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት እንደ ዮሴፍ የሚሸሽ ነው

ዛሬ ላይ ሆኖ ለነገ ህልም ያለው ፣ በከንቱ የማይባዝን ፣በአላማ የሚማር የሚሰራ ነው።

የዘመኑን የአለባበስ ፣ አነጋገር እስታይል አሳዳጅ ሳይሆን እግዚአብሔርን በመምሰል ፣ በጭምትነትና ራሱን በመግዛት ፣ ለፉሺን ደንታ የሌለው ነው

የቤተሰቡን፣የሀገሩን የድህነት ቀንበር ለመስበር ተግቶ ዝቅ ብሎ የሚሰራ እንጂ የወጣት ጡረተኛ ፣የቤተሰቡንና የሀገሩን ሀብት አባካኝ አይደለም

በወሬና በአሉባልታ መንደር በየሚዲያው ተጥዶ እየዋለ ፣ጊዜውን ፣ውስጡ ያለውን እምቅ አቅም የማያባክን አስተዋይና እራሱን ከአልባሌ ሱሶች የሚጠብቅ ነው።

ከቤተክርስትያን የማይቀር ፣በትጋትና በታማኝነት ፣ቃሉን የሚማር፣ የሚፀልይ፣ መሪዎቹን የሚታዘዝ፣ለወንጌል ስርጭት ያለመታከት የሚተጋ ነው

በትምህርት ቤት፣በስራው ስፍራ፣ ኑሮው የሚናገርለት፣ሁሉም የጌታ ስለመሆኑ ( አይጠጣም፣ዘፈን አይሰማም፣ ጭፈራ ቤት አይሔድም፣አያጨስም፣ አይሰርቅም እያሉ ፣የሚመሰክሩለት ፤ የጌታ በመሆነኑ የማያፍር ነው።

እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ ከሚወዱት ጋር፣ ፍቅርን፣ፅድቅን፣ ሰላምን የሚከታተል፣በንፁህ ልብ የጌታን
ስም ከሚጠሩት ጋር መንፈሳዊ ህብረት የሚያደርግ ፣ ከአመፅ ሁሉ የሚሸሽ ነው።

ስለ ሀገሩ የሚፀልይ፣ለሀገሩ መሪዎች እና ህግ የሚገዛ፣በአመፅ ህብረት ውስጥ ፣በጥላቻና ዘረኝነት ስብሰባዎችና ተግባሮች መሀል የሚይሳተፍ፤ በሀገሩ ላይ የልማት፣የለውጥ ፣መምጣትን የሚመኝና ለዚያ የተቻለውን ሁሉ ሀላፊነት የሚወጣ፤ ልማት እንጂ ጥፉት መንደር የማይገኝ ፣አስተሳሰቡ የታደሰ ፣ ብዙ የፈጠራ ሀሳቦች የሚያመነጭ ፣ በስሜት ብቻ ሳይሆን በአላማ፣ በእውቀት ፣ በመርህ የሚመላለስ ነው።
ይህ ነው መንፈሳዊ ወጣት
ውብሸት ነኝ
FOCUS /SOLAS INTERNATIONAL

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Aug, 08:29


ዋጋችን!
እኛ ስህተታችን፣ ሰዎችና ሰይጣንም ያሉንን አይደለንም።
:- የእኛ ዋጋ እኛ የተሰራንበት እቃ ልክ ነው። ለእኛ በተከፈለው መስዋእትነት ፣እኛን ለመስራት በዋለው እቃ ልክ ነው።

:- ለአንድ ነገር ትክክለኛ ዋጋው የሚተመነው በሰሪው እንጂ በገዢው አይደለም። የእኛም ትክክለኛ ዋጋ የሚተመነው በሰሪአችን ነው። ወይም የሚያውቀው ባለቤቱ ሰሪው ነው። ማንም እየተነሳ ተመን /ስም እንዲሰጣች አትፍቀዱም አትቀበሉም።

:- ማንኛውም የከበረ እቃ ምንም ያህል የከበረ ቢሆንም ፣የእቃውን ክብር በማያውቁት ሰዎች መሀል እስከተቀመጠ ድረስ የረከሰ ፣ዋጋ ቢስ
እንዲሁም ተፈላጊነት የሌለው ነው የሚሆነው። የት እንደምንገኝ እንምረጥ። ዋጋችንን በማያውቁ መሀል ከተገኘህ ርካሽ እንሆናለን።
በማይመጥነን ቦታ ፣ ለማንነታችን ትክክለኛ ክብር በማይሰጡን መሀከል አንቀመጥ

:- የከበረ ውድ እቃ መጠቅለያው የማያምር ወይም በአቧራና በጭቃ የተሸፈነ ከሆነ ፤ምንም የከበረ እቃ ቢሆንም ተፈላጊነቱ ይቀንሳል። አንዋዋራችን ፣ባህርያችን፣አነጋገራችን ፣ተግባራችን ዋጋችንን እንዳያራክስብን እንጠንቀቅ።
:- የከበረ ነገር አቧራ ስለሸፈነው፣ ዋጋውን አይቀንስም፣አቧራውን አጥበን አንፅተን ብናየው የተሰራበት ማንነቱ ዛሬም ያው ነው። በተለያዩ ፈተናዎች ፣ማጣቶች ፣ ውድቀቶች ውስጥ መገኘታችን ለጊዜው ተፈላጊነታችንን ቢገዳደሩትም ፣ ማንነታችን ግን አይቀየርም። እኛ ስህተታችንን አይደለንም። ማንነት በድካም፣ በማጣት፣ በልብስ አይለካም። ሰዎችን ከውጪ አይተን ፣ከስህተታቸው ተነስተን አንናቃቸው።
don’t judge the book by its cover መፅሀፉን በውጫዊ ሽፉኑ አትመዝነው
p woubshet
FOCUS /SOLAS INTERNATIONAL USA
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Jul, 09:29


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

18 Jul, 12:44


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Jul, 13:09


ለወንዶች እንፀልይ እንዲሁም ወንዶች እንንቃ !!!
ONE OF JEZEBEL & FARON SPIRIT FOCUS IS MAN !
አንዱ የኤልዛቤል እና የፈርኦን መንፈስ ትኩረት ወንድ ላይ ነው !?
1ነገ20፤25
በእግዚአብሔር ፊት ክፉት ለመስራት ራሱን እንደ ሸጠ ፣ሚስቱም ኤልዛቤል እንደ ነዳችው ፣ እንደ አክአብ ያለ ሰው አልነበረም
ዘፀ1፤ 16 ,22
እናንተ የእብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፣ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፤ወንድ ቢሆን ግደሉት እና ወደ ወንዝ ጣሉት ሴት ብትሆን ግን በህይወት ትኑር

WHY ? ለምን ? እርሱ ወንድ
BECAUSE HE IS :-
THE HEAD OF THE HOUSE
THE LEADER OF THE HOUSE
THE PROVIDER OF THE HOUSE
THE PROTECTOR OF THE HOUSE
THE SOURCE OF GENERATION
GOD ASSIGNED OR ORDEND REPRESENTATIVE OF GOD
THE DELIVERER AND LEADER TO PROMIS LAND

THIS BOTH SPIRIT WANT :-
ይህ መንፈስ የሚፈልፈው ?
TO DESTROY HIS VISION AND CALLING
TO CONTROL HIM AND HIS POSITION
TO MAKE AND FEEL HIM WORTHLESS
TO DESTROY HIS FELLOWSHIP WITH GOD /SPIRITUAL LIFE
TO DISCONNECT HIM FROM HIS WIFE AND HIS CHILDREN
TO KILL HIM EARLY
👇
MAN LET US WAKE UP AND
FOCUS ON :-
FIXING OUR SPIRITUAL LIFE
TAKE BACK GOD GIVEN VISION
TAKE BACK OUR MAN POSITION OR ROLL OF LEADERSHIP
TAKE BACK OUR RESPONSIBILITY AS A FATHER AND MODEL
LET US BE A LOVING ,CARRING ,PROTECTIVE HOUSBAND FOR OUR WIFE

ዛሬ በአቋም ፣በአላማ የጨከኑትን ፣ትልቅ ራእይ ሰንቀው የሚነሱ ወንዶች ላይ ያተኮረ
የሚያስጨንቅ፣ባሪያ ያደረገ ፣ የሚያስፈራራ
ስልጣኑን ፣መሪነቱን ለመቆጣጠር የሚተጋ አመፀኛ መንፈስ
የሚያሳድድ ፣ከቤቱ፣ከራእዩ፣ከልጆቹ የሚያለያይ
እንዲሁም ራእዩንም እሱንም በስጋ ጭምር ያለ ጊዜው የሚገል መንፈስ
በኢየሱስ ስም የተመታ ይሁን
P WOUBSHET
FOCUS/SOLAS INTERNATIONAL
https://t.me/focusinternationalministry