🔻 I ዬርገን ክሎፕ በጭንቅት የሚሰቃይ ለአንድ ታዳጊ ደጋፈ የፃፈዉ ደብዳቤ 👇
"ንግግሬን በሚስጥር ልጀምር? እኔ ፈሪ ነኝ። እዉነቱን ለመናገር ፈሪ ባልሆን ኖሮ ይጨንቀኝ ነበረ ምክንያቱም ይህን ፍርሀት እና ጭንቀት ወደ ጥሩ እና አዎንታዊ ነገር መለወጥ እችላለሁኝ። በአንተ እድሜ ላይ ያለ ልጅ የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ እንደዚህ ይሰማዋል ብሎ ማሰብ እንግዳ ሊሆንብክ እንደሚችል አዉቃለሁ።
በላክልኝ ደብዳቤ ላይ በጣም ሀሳቢ ፣ ሩህሩህ እንደሆንክ እና እነዚህን ፀባይ አቅፈክ ከጭንቀት ወይንም ፍርሀት መዉጣት ከባድ እንደሆነ እረዳለሁ። ተጫዋቾቼ እንደዚህ ሲሰማቸዉ ምን እንደማድረግ ጠይቀከኝ ነበረ እና ይህን ለመመለስ ቀላል ነዉ ፣ እነሱ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆኑ እና በእነሱ ላይ ምን ያህል እምነት እንዳለኝ እነግራቸዋለሁ ፣ በአንተ በኩል ቤተሰቦችክ ይህን እንደሚያደርጉልክ ምንም ጥርጥር የለኝም።
መጥፎ ነገር ይፈጠራል ብለክ እንዳትጨነቅ። እንደምታዉቀዉ ከአንድ በላይ የፍፃሜ ጨዋታዎችን ተሸንፊያለሁ እናም ጥሩ ስሜት አይደለም ነገር ግን በቤተሰብ እና በጓደኞቼ እገዛ ምክንያት ጉዞዬን መቀጠል ጀመርኩኝ እና አንዳንድ ጥሩ ጊዜያቶችን ማሳለፍ ችለናል። ከመጥፎ ሁኔታዎች ጋር ብጋተት ኖሮ እኚህ ነገሮች መቼም እንደማይፈጠሩ አዉቃለሁ ፣ ስለዚህ እባክህን እራስክን በአዉንታዊ መንገድ ማየት አለብክ እና ወደፊት እያደግ ስትሄድ ጥሩ ነገሮች ስለሚያጋጥምክ እነሱን እያሰብክ ጉዞክን ቀጥል።
የሊቨርፑል ቤተሰብ መሆንክን እንዳትረሳ እናም ብዙ ሰዎች እንዳንተ ደስተኛ መሆን የሚፈልጉ ሰዎች አሉ። ድጋፍክ ለእኔ እና በክለቡ ዉስጥ ለሚገኙ ሰዎች በሙሉ ትልቅ ጥቅም አለዉ። ይህ ደብዳቤ እኛ አንተን እንደምንደግፍ እንደሆነ እወቅ።"
𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚|| ✨ @Et_Liverpool
𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚|| ✨ @et_Liverpool