#ትምህርተ_ፀሎት
ጸሎት ጽናት ይጠይቃል፤ የሚጸልዩ የሚቀጥሉ እንጂ የሚያቋርጡ መሆን የለባቸውም። "ሳይታክቱ ሁልጊዜ መጸለይ እንዲገባቸው" ጌታ ሲያስተምር የክፉውን ዳኛ ምሳሌ ነገራቸው። እርሱ መበለቲቱ ስላሰለቸችው ብቻ ፈረደላት፤ ለራሱ አስቦ ፍትሕን 'ፈጸመ'። ጌታም ስለ እንከን አልባው የሁሉ ዳኛ እንዲህ አለ፤ "እግዚአብሔርስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? : ከመጠን በላይስ ችላ ይላቸዋልን?" (ሉቃ 18፥7)። ነገር በከፋበት ጊዜ የፍትሕ ጩኸት አብዝቶ ይሰማል። ጩኸትን ማሻሻል ግን መፍትሔ ያመጣል፤ እግዚአብሔርን ታምኖና አምኖ መጮኽ!: በፀሎት የፀኑ በእምነታቸው የተመሠከረላቸው አባቶች አሉን ፤ ከእነርሱ በፀሎት መፅናትና አለመታከትን ልንማር ይገባል። ለብዞቻችን ፀሎት ያስፈልጋል፥ በፀሎት መካኒቱ ወልዳለች፣ በፀሎት ዳንኤል በአንበሳ ጉጉጓድ ውስጥ አድሮአል፣ ለአንበሳ ምግብ መሆኑ ሲጠበቅ እርሱ ግን በደህና አድሯል "እነ አብድናጎ ሰድያቅ ምስያቅ በፀሎት እሳት ውስጥ አምላካቸው አሳይተዋል: ባያድነንም ላቆምከው ለወርቁ ምስል አናመልክም ብሎ በፀሎት የመታመንን ውጤት አሳይተዋል ። በትጋት ያለመታከት የሚፀልይ ሰው ለቤተሰብ ለአገር መፍትሔ ይሆናል።
Luke 18:7
❝And will not God bring about justice for his chosen ones, who cry out to him day and night? Will he keep putting them off? ❞
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይሄንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351