ለሁሉም ተማሪዎች ዩኒፎርም ተሰርቶ ያለቀ ስለሆነ በሚከተሉት አድራሻዎች በመሄድ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን::
1. የቡልቡላ ቅርንጫፍ ተማሪዎች በሙሉ 93 ማዞሪያ ወይም ቦሌ ሚካኤል ያለው ኃይሉ ጋርመንት በመሄድ መዉሰድ ትችላላችሁ
2. የሳሪስ ቅርንጫፍ ተማሪዎች በሙሉ ሳሪስ ዋናው ግቢ ዉስጥ እየመጣችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን::
3. ዩኒፎርም ከሌላ ቦታ ያሰራችሁ የተማሪ ወላጆች የትምህርት ቤታችን አርማ መደረግ ስላለበት በሚቀርባችሁ የሀይሉ ጋርመንት በመሄድ የትምህርት ቤቱን አርማ ማስደረግ አለባችሁ ::
ማሳሰቢያ
ከሰኞ ማለትም ጥቅምት 4/2017 ዓ. ም ጀምሮ ዩኒፎርም ሳይለብስ የመጣ ወይም አርማ የሌለው ዩኒፎርም ለብሶ የመጣ ማንኛውም ተማሪ የማናስገባ መሆኑን እናሳዉቃለን::